Telegram Web Link
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA (Tsegab Wolde)
#ShuraKitata

“ለዚህ ሩጫ አትሌት ቀነኒሳ ሲረዳኝ ነበር፡፡ እንዴት መሮጥ እንዳለብኝ መክሮኛል ፤ በዚሁ መንገድ ተለማምጄ በማሸነፌ በጣም ደስተኛ ነኝ” - አትሌት ሹራ ቂጣታ (ከውድድሩ በኃላ የተናገረው-AlAin)

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA (Tsegab Wolde)
ዩኒቨርስቲዎችን መልሶ ለመክፈት የሚያስችል የዝግጅት ምዕራፍ ግምገማ በሁሉም ዩኒቨርስቲዎች እየተካሄደ ነው!

በሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር የተቋቋመ ግብረ ኃይል ዩኒቨርስቲዎቹ ያሉበት የዝግጅት ሁኔታ በመገምገም ቀጣይ አቅጣጫ ለማስቀመጥ እንዲቻል የመስክ ግምገማ እያካሄደ ይገኛል።

ግብረኃይሉ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከጤና ሚኒስቴር ጋር ሆኖ ባዘጋጀው የዝግጅት ፕሮቶኮል መሰረት የዩኒቨርስቲዎቹን የዝግጁነት ሁኔታ ይገመግማል፡፡

ማንኛውም ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች መቀበል የሚያስችል ሁኔታ ላይ መሆን አለመሆኑ የሚታወቀው በመስክ ግምገማው በተጠናቀረው መረጃ መሰረት ሲሆን ውጤቱ ግምገማው ከተጠናቀቀ በኃላ በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በኩል ይገለጻል።

የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር
መስከረም 24/2013 ዓ/ም

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA (Tsegab Wolde)
#ShuraKitata

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ አትሌት ሹራ ቂጣታ ባስመዘገበው ድል የተሰማቸውን ደስታ ገለፁ ፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለአትሌት ሹራ እንኳን ደስ አለህ የሚል መልዕክት አስተላልፈዋል።

በተጨማሪ ጠ/ሚ ዶ/ር አብይ፥ "የሀገራችንን ሰንደቅ ዓላማ ከፍ አድርጋችሁ የምታውለበልቡ ጀግኖች ሯጮቻችን ሁሉ አድናቆቴ ይድረሳችሁ። ሀገራችን ትኮራባችኋለች።" ብለዋል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA (Tsegab Wolde)
የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ቦርድ ለፕ/ር ክንደያ የእውቅናና ምሥጋና ሰርተፊኬት አበረከተ !

ዛሬ የመቐለ ዩኒቨርስቲ ቦርድ ለቀድሞ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ፕ/ር ክንደያ ገብረህይወት በአገልግሎት ዘመናቸው ለሰሯቸው ተግባራት የእውቅናና የምስጋና ሰርተፍኬት አበርክቷል።

በተጨማሪ የEITM ስታፍ ፕ/ር ክንደያ ገብረህይወት በስራ ዘመናቸው ላከረከቱት አስተዋፅኦ ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን ልዩ ስጦታም አበርክተውላቸዋል።

በሌላ በኩል የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ በቀጣይ 2 ሳምንት ውስጥ ለፕሮፌሰር ክንደያ ገብረህይወት የምስጋና ፕሮግራም እንደሚያዘጋጅ ተገልጿል።

Via Mekelle University
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA (Tsegab Wolde)
#COVID19Ethiopia

በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዓት በተደረገው 8,101 የላብራቶሪ ምርመራ 959 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ሲረጋገጥ የ8 ሰዎች ህይወት አልፏል። በተጨማሪ በትላንትናው ዕለት 735 ሰዎች አገግመዋል።

በአጠቃላይ በሀገራችን በኮቪድ-19 የተያዙ ሰዎች 78,819 የደረሱ ሲሆን የሟቾች ቁጥር 1,222 ደርሷል ፤ ከበሽታው ያገገሙ አጠቃላይ ሰዎች ቁጥር ደግሞ 33,060 ደርሷል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA (Tsegab Wolde)
የፕ/ር መስፍን የቀብር ስነ-ሥርዓት ማክሰኞ ይፈፀማል!

የታዋቂው ምሁር እና የሰብዓዊ መብት ተሟጋች የፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማርያም የቀብር ስነ-ሥርዓት ማክሰኞ መስከረም 26/ 2013 ዓ/ም በቅድስት ስላሴ ካቴድራል እንደሚፈፀም ተገልጿል።

ከቀብር ስነ-ስርዓቱ አስቀድሞ ጠዋት ከ2:30 እስከ 5:00 ሰዓት ድረስ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ስድስት ኪሎ ካምፓስ ልደት አዳራሽ የሽኝት ዝግጅት ይደረጋል።

ከሽኝቱ ዝግጅት በኃላ ከቀኑ 6:30-7:30 ባለው ጊዜ ስርዓተ - ቀብራቸው የሚፈጸም መሆኑን የቀብራቸው አስፈፃሚ ኮሚቴ አሳውቋል። (Ahadu Radio)

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA (Tsegab Wolde)
በአ/አ የኮድ 2 እና ኮድ 3 ተሽከርካሪዎች በስራ መውጫና መግቢያ ሰዓት የጣምራ አገልግሎት እንዲሰጡ የሚያዝ አሰራር ሊዘረጋ ይችላል ተብሏል !

በአዲሰ አበባ ከተማ የትራፊክ መጨናነቅ ለማቃለል የተለያዩ እቅዶችን አቅዶ ወደ ተግባር ለመግባት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እየተወያየ መሆኑን የከተማ ትራፊክ ማኔጅመንት ኤጀንሲ አስታውቋል።

የኤጀንሲው ዋና ዳሬክተር ጅሬኛ ሄርጳ #ለFBC (ኤፍቢሲ) ተከታዩን ብለዋል ፦

- የኮድ 2 እና ኮድ 3 ተሽከርካሪዎች በስራ መውጫ እና መግቢያ ሰዓት የጣምራ ማለትም 3 ሰውና ከዚያ በላይ የመጫን አቅም ያላቸው አሸከርካሪዎች የጣምራ ትራንሰፖርት ካልሰጡ ጠዋት ከ1 እሰከ 3 ሰዓት እና ምሸት ከ11 እሰከ ምሽት 1 ሰዓት ባለው ጊዜ ውስጥ መንቀሳቀስ አይችሉም።

- የጣምራ ትራንስፖርት አገልግሎት የኮድ 2 እና ኮድ 3 ተሽከርካሪዎች የትራፊክ መጨናነቁን ለመቀነስ በፈቃደኝነት ለሌሎች ተሳፋሪዎች አገልግሎት የሚሰጡበት መንገድ ነው።

- ህብረተሰቡ የብዙሃን ትራንሰፖርትና የጣምራ ትራንሰፖርትን በመጠቀም የመዲናዋን የትራፊክ መጨናነቅ እንዲቀንስ የበኩሉን አሰተዋጾ ሊያደርግ ይገባል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA (Tsegab Wolde)
ፋና ብሮድካስቲንግ ቀደም ብሎ የአ/አ ከተማ ትራፊክ ማኔጅመንት ኤጀንሲ ዋና ዳሬክተር ጅሬኛ ሄርጳን አናግሮ ያወጣውን ዘገባ ከይፋዊ የፌስቡክ ገፁ ላይ አንስቶታል።

ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ለምን / በምን ምክንያት መረጃውን ከገፁ ላይ እንዳነሳው ምንም የገለፀው ነገር የለም።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA (Tsegab Wolde)
#UPDATE

የአ/አ ከተማ ትራፊክ ማኔጅመንት ኤጀንሲ ዋና ዳሬክተር ጅሬኛ ሄርጳ 'ከኢትዮጵያ ቼክ' ጥያቄዎች ቀርበውላቸው ምላሽ ሰጥተዋል።

ኢትዮጵያ ቼክ : ይህ የአሰራር ሀሳብ እንዴት መጣ ?

አቶ ጅሬኛ : ዋናው ሀሳቡ ትራፊክ በሚጨናነቅባቸው ሰአቶች ፍሰቱን ማቃለል ነው፣ በተለይ አሁን ትምህርት ለመጀመር እንቅስቃሴዎች ስላሉ እንደ ምክረ ሀሳብ የቀረበ ነው ፣ ግን ገና ህግ ሆኖ አልወጣም፣ ብዙ ውይይት ይደረግበታል።

ኢትዮጵያ ቼክ : በአሁን ሰአት ካለው የኮሮና ቫይረስ እና የፀጥታ ስጋት (በተለይ ከመኪና ዝርፊያ ጋር) ይህ እንዴት ይታያል?

አቶ ጅሬኛ : እኛ እንደ ትራፊክ ማኔጅመንት ፅህፈት ቤት ምን ብናደርግ ችግሩ ሊቃለል ይችላል ብለን ነው ያሰብነው ፣ በዚህ ላይ ከኮሮና ቫይረስ ስጋት አንፃር እና ከፀጥታ ሁኔታ ጋር ገና ውይይት እና ምክክር ይደረግበታል። እኛ ህግ ማውጣት አንችልም፣ አሰራሩን ገና እንደ ምክረ ሀሳብ ብቻ ነው ያቀረብነው።

ኢትዮጵያ ቼክ : አሽከርካሪዎች ተጨማሪ ሰው ከየት አግኝተው እና በምን መልኩ ሊጭኑ እንደሚችሉ አስባችሁበታል?

አቶ ጅሬኛ : ለምሳሌ ተማሪዎች ወደ ት/ቤት ሲሄዱ በአንድ ቤተሰብ መኪና ቢሄዱ ፣ ሰራተኞች ወደ አንድ ስፍራ ሲሄዱ ትርፍ ቦታ ካለ ቦታ ቢጋሩ የሚል ሀሳብ አለ። ካልሆነ ግን ወይ ከጠዋት 1 ሰአት በፊት ወይም ምሽት ከ1 ሰአት በሗላ እንዲንቀሳቀሱ ነው። ግን ቅድም እንዳልኩት ይህ ገና ምክረ ሀሳብ ነው።

ኢትዮጵያ ቼክ : ከዚህ ውጪ የቀረቡ ሌሎች ምክረ ሀሳቦች አሉ?

አቶ ጅሬኛ : አዎ ፣ ለምሳሌ ብዙ ሰው የጫኑ ተሽከርካሪዎች ቅድሚያ አግኝተው እንዲጓዙ የሚል ሌላ ሀሳብ አለ ፣ ይህ ውጪም የተለመደ ነው።

[የኢንተርኒውስ ፕሮጀክት-ኢትዮጵያ ቼክ]
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA (Tsegab Wolde)
ትራምፕ ነገ ከሆስፒታል ሊወጡ ይችላሉ ተብሏል!

ፕሬዜዳንት ትራምፕ ከሆስፒታል ወጥተው በዋይት ሀውስ ሆነው ህክምናቸውን ሊከታተሉ እንደሚችሉ ሃኪሞቻቸው መግለፃቸውን #ቪኦኤ ዘግቧል።

የፕሬዚደንት ትራምፕ ዋናው ሃኪማቸው ዶክተር ሻን ኮንሊ ዛሬ በነበረ መግለጫ ላይ "እንደዕውነቱ ከሆነ በጣም በጎ ናቸው" ብለዋል።

የመተንፈሻ አካላት አጠቃላይ ጤና ሃኪም የጦር ሰራዊቱ ኮሎኔል ዶ/ር ሻን ዱድሊ የዛሬ ጠዋት የፕሬዚደንቱ የጤና ይዞታ ምልክቶች (የደም ግፊት ፥ የልብ ምት ፥ የሰውንት ሙቀት እና አተነፋፈስ) በደህና ሁኔታ ላይ እንዳሉ ገልጸዋል።

"ወዲያ ወዲህ ይራመዳሉ ፥ የትንፋሽ ማጠርም ይሰማኛል አላሉም ፥ ሌላ የመተንፈሻ አካላት ችግር አልታየባቸውም" ሲሉ አብራርተዋል።

ዶክተር ብራያን ጋሪባልዲ (ከJHU)፥ "እንደ ዛሬ ይዞታቸው ከቀጠሉ እና ደህንነት ከተሰማቸው ነገም ቢሆን ከሆስፒታሉ ወጥተው ዋይትሃውስ ሆነው ህክምናቸውን የሚቀጥሉበትን ዕቅድ ማዘጋጀት እንችላለን ብለን ተስፋ እናደርጋለን" ብለዋል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA (Tsegab Wolde)
#UPDATE

ዛሬ በ8:00 ሰዓት 5ኛው የሕዝብ ተወካዮች እና የፌዴሬሽን ምክር ቤቶች 5ኛ የፓርላማ ዘመን 6ኛ ዓመት የሥራ ጊዜ የመክፈቻ ሥነ-ስርአት ጉባኤ ይካሄዳል።

ጉባኤው በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት በሚገኘው የስብስባ አዳራሽ የሚካሄደው ሲሆን የኢፌዲሪ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ይገኛሉ።

የ2ቱ ምክር ቤቶችን የጋራ ስብሰባ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በሚያደርጉት ንግግር ይከፈታል።

በፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ የመክፈቻ ንግግር በ2013 በጀት ዓመት የፌደራል መንግስት ትኩረት ሰጥቶ የሚያከናውናቸው ተግባራት ይፋ ይደረጋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ከኤፍ ቢ ሲ የተገኘው መረጃ ያሳያል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA (Tsegab Wolde)
ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በቅርቡ ተማሪዎቹን እንደሚጠራ አስታወቀ!

የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ኮቪድ-19ን በመከላከል ዩኒቨርሲቲዎች ትምህርት የሚጀምሩበትን ቁመና የሚገመግም ቡድን ወደየተቋማቱ መላኩ ይታወቃል፡፡

የግምገማ እና ክትትል ቡድኑ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ዝግጁነት በተለያዩ መለኪያዎች መዝኖ ግብረ መልሱን ለመካከለኛና ከፍተኛ አመራሮች ዛሬ አቅርቦ በስጋትና መልካም አጋጣሚዎች ውይይት እና ምክክር ተደርጓል፡፡

የዓለም የጤና ድርጅትና የጤና ሚኒስቴርን መመሪያ በተገቢው መንገድ ተግባራዊ በማድረግ ጎንደር ዩኒቨርሲቲ መማር ማስተማሩን እንደገና ለማስቀጠል የሚያስችል አቋም ላይ እንደሚገኝ በቡድኑ ግምገማ ውጤት #ተረጋግጧል፡፡

ዩኒቨርሲቲው በቅርቡ ተማሪዎችን ተቀብሎ መደበኛ ትምህርቱን የሚያስቀጥል ይሆናል፡፡

ጎንደር ዩኒቨርሲቲ
መስከረም25/2013 ዓ.ም
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA (Tsegab Wolde)
ከዛሬ ጀምሮ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ዝግጁነት ይገመገማል ተብሏል !

(በSHEGER FM 102.1 የቀረበ)

የከፍተኛ ትምህርት ጥራት አግባብነት ኤጀንሲ ከዛሬ ጀምሮ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን እንደሚጎበኝ አሳውቋል።

ጉብኝቱ ተቋማቱ ትምህርት ለማስጀመር ዝግጁ ስለመሆናቸው ምልከታ የሚደረግበት እንደሆነ ተገልጿል።

በጉብኝቱ ወቅት የኤጀንሲው ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ተሳታፊ እንደሚሆኑ ተነግሯል።

የተቋማቶቹን ዝግጅት ለመገምገም የሚያስችል ስልሳ (60) መስፈርቶች ያሉት መጠይቅ በMoSHE ተዘጋጅቷል።

በተቋማቱ ጉብኝት ወቅት ዋነኛው ትኩረት የሚሰጣቸው ነጥቦች ተለይተዋል። እነዚህም፦

• የአመራርና የሰው ኃይል አደረጃጀት ዝግጅት
• በመማር ማስተማር በኩል በቂ የመሰረተ ልማት አገልግሎት ግብዓት ዝግጅት
• የህግና እቅድ ማዕቀፍ ዝግጅት ናቸው።

ግምገማው ሲጠናቀቅ በግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመማር ማስተማር ስራ እንደሚጀመር ይጠበቃል።

ኤጀንሲው 250 በሚደርሱ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ክትትል እና ቁጥጥር የሚያደርግ ይሆናል።

ተቋማቱ በአጠቃላይ ከ1,000 በላይ ቅርንጫፎች አሏቸው በሁሉም የተቋማቱ ቅርንጫፎች በመገኘት ግምገማው እንደሚካሄድ ተገልጿል። በ10 ቀናት ውስጥ የግማሾቹን ግምገማ ለማጠናቀቅ ታቅዷል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA (Tsegab Wolde)
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ትራምፕ ከሆስፒታል ወጣ ብለው መታየታቸው አግራሞትን ፈጥሯል !

ከሰዓታት በፊት ዶናልድ ትራምፕ ባልተጠበቀ ሁኔታ በጥቁር መኪናቸው የኋላ መቀመጫ ሆነው ከሆስፒታል ውጭ ታይተዋል፡፡

ፕሬዜዳንት ትራምፕ ከሆስፒታል የወጡት ጤና እንዲሆኑ የሚመኙላቸው ደጋፊዎቻቸውን ሰላም ለማለትና አድናቆታቸው ለመግለጽ ነው ተብሏል።

ይህ የዶናልድ ትራምፕ ያልተጠበቀ ድርጊታቸው አንዳንድ ተቺዎቻቸውን አስቆጥቷል፡፡

ዶናልድ ትራምፕን ከሆስፒታል በመኪና ይዘዋቸው የወጡት ሾፌራቸው እና ጠባቂዎቻቸው ሁሉም ራሳቸውን ማግለል ይኖርባቸዋል ተብሏል፡፡

ትራምፕ ዛሬ ሰኞ ማምሻውን ድረስ ሙሉ በሙሉ ከተኙበት ከዋልተር ሪድ ሆስፒታል ወጥተው ወደዋይት ሐውስ ቤታቸው ሊያመሩ እንደሚችሉ BBC አስነብቧል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA (Tsegab Wolde)
#ATTENTION

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ከ100 ሺህ እስከ 1.5 ሚሊዮን ብር ቅያሬ ጥቅምት 6/2013 ዓ/ም እንደሚጠናቀቅ አሳውቋል።

በቀሩት 11 ቀናት ውስጥ ህብረተሰቡ በአቅራቢያው በሚገኝ ባንክ የብር ቅያሬውን እንዲፈጽም የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ጥሪ አቅርቧል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA (Tsegab Wolde)
#UPDATE

የትምህርት ሚኒስትር ዶ/ር ኢ/ር ጌታሁን መኩሪያ ትምህርት ሚኒስቴርን የ3 ወር የስራ አፈፃፀም በተመለከተ ለጋዜጠኞች በሰጡት ማብራሪያ ተከታዩን ብልዋል ፦

- መንግስት ለተማሪዎች የአፍና የአፍንጫ መሸፈኛ ጭንብል የማቅረብ ስራ እየሰራ ነው።

- ትምህርት ሲጀመር ማስክ ያላደረገ ማንኛውም ተማሪ ወደ ትምህርት ቤት አይገባም።

- የኮሮና ቫይረስ መከሰቱን ተከትሎ ለኮሮና ቫይረስ ህሙማን ማቆያ ጥቅም ላይ ሲውሉ የነበሩ ትምህርት ቤቶች የኬሚካል ርጭት ሳይደረግላቸው ትምህርት አይጀምሩም።

- በትምህርት ቤቶቹ ውስጥ የኬሚካል እርጭቱን ለማካሄድ አስፈላጊው ዝግጅት ተጠናቋል፤ በቀጣይ ሳምንታት ርጭቱ ይከናወናል።

- ይህንን አስቸጋሪ ወቅት በድል ለመወጣት መምህራን እና ወላጆች ርብርብ ሊያደርጉ ይገባል።

#MoE
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
2024/09/22 14:34:22
Back to Top
HTML Embed Code: