Telegram Web Link
👋🏾 ሰላም! ለታማኝነትዎ እንሸልምዎ!

🤩 የቤቲካ ታማኝ ደንበኞች በየቀኑ እስከ 5000 ነጥቦችን ይሰበስባሉ።

👉🏾 እርሶም Betika.et ላይ ተቀላቀሏቸው።

ቤቲካ የአሸናፊዎች ቤት!
Forwarded from WANAW SPORT
📢 ልዩ ቅናሹ 5 ቀናት ቀሩት!

📌 እሰከ ሐምሌ 1 ብቻ በዋናው አዲስ የቴሌግራም ቦት የስፖርት ትጥቆችን በማዘዝ ልዩ የ5% ቅናሽን ያግኙ።

👉🏾 @WanawSportBot 👈🏾

📌 #እንዳያመልጥዎ፣ ይዘዙን!

🏅ዋናው ወደፊት...

@wanawsportwear
" ቡድኑን ለማጠናከር እየሰራን ነው  " አርቴታ

የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል በቀጣይ በሁሉም የሜዳ ክፍሎች ቡድኑን ለማጠናከር እየተንቀሳቀሰ እንደሚገኝ አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ ገልጸዋል።

" ልናጠናክራቸው የሚገቡ ነገሮች አሉን " ያሉት አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ እየተመለከትን እንገኛለን በሁሉም ቦታዎች ላይ ህጉን አክብረን ቡድኑን ለማጠናከር ጥረት እናደርጋለን ብለዋል።

" በኮንትራት ማራዘም ዙሪያ የምናገረው አዲስ ነገር የለም ያልተቀየረ ነገር ቢኖር እዚህ በመሆኔ ደስተኛ መሆኔ እና አርሰናልን ማሰልጠኔን ምን ያህል እንደምወደው ነው።" አርቴታ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ጁድ ቤሊንግሀም ቅጣት አይጣልበትም !

የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን ተጨዋች ጁድ ቤሊንግሀም ቡድኑ ስሎቫኪያን ባሸነፈበት ምሽት የተጋጣሚ የቡድን አባላት ላይ ያነጣጠረ ያልተገባ ድርጊት አሳይቷል በሚል ምርመራ ተደርጎበት ነበር።

አሁን ላይ የአውሮፓ እግርኳስ ማህበር ጁድ ቤሊንግሀም ላይ የቅጣት ውሳኔ እንደማይጥል እና ለስዊዘርላንዱ የሩብ ፍፃሜ ጨዋታ ዝግጁ እንደሚሆን ተገልጿል።

ጁድ ቤሊንግሀም በሰዓቱ ያደረገው ነገር የተጋጣሚ አባላትን ክብር ለመንካት እና እነሱ ላይ ያነጣጠረ እንዳልሆነ እና ትልቅ ክብርም እንዳለው በማህበራዊ ትስስር ገፁ ገልፆ ነበር።

እንግሊዝ ቅዳሜ ምሽት 1:00 ከስዊዘርላንድ አቻዋ ጋር የሩብ ፍፃሜ ጨዋታዋን የምታደርግ ይሆናል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ኢትዮጵያ የምድብ ተጋጣሚዎቿን አውቃለች !

የ2025 የሞሮኮ አፍሪካ ዋንጫ ውድድር ማጣሪያ ምድብ ድልድል ከደቂቃዎች በፊት በደቡብ አፍሪካ ጁሀንስበርግ በተደረገ የእጣ ማውጣት ስነ-ስርዓት ይፋ ተደርጓል።

በዚህም መሰረት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በምድብ ስምንት

- #ታንዛኒያ

- #ጊኒ እና

- #ኮንጎ ጋር ተደልድሏል።

በደርሶ መልስ በሚደረግ ጨዋታ የምድቡን አንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ይዘው የሚያጠናቅቁ ብሔራዊ ቡድኖች ለአፍሪካ ዋንጫው ያልፋሉ።

የማጣሪያ ጨዋታዎቹ ከሚቀጥለው አመት መስከረም ወር ጀምሮ መካሄዳቸውን ይጀምራሉ ተብሎ ይጠበቃል።

*ሙሉ የምድብ ድልድሉ ከላይ በምስሉ ላይ ተያይዟል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
" አንቶኒዮ ሩዲገር አያስፈራንም "  ፔድሪ

የስፔን ብሔራዊ ቡድን የመሐል ሜዳ ተጨዋች ፔድሪ የነገ ተጋጣሚያቸው ጀርመን ተከላካይ አንቶኒዮ ሩዲገር እንደማያስፈራቸው ገልጿል።

ፔድሪ በንግግሩም " አንቶኒዮ ሩዲገር ጠንካራ እና ምርጥ ተከላካይ ነው " ሲል የተደመጠ ሲሆን " ነገርግን እሱ እኛን አያስፈራንም " በማለት ገልጿል።

ስፔን ከጀመርን ጋር ነገ ምሽት 1:00 ሰዓት የሩብ ፍፃሜ ጨዋታቸውን የሚያደርጉ ይሆናል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ፈረሰኞቹ አመቱን በድል አጠናቀዋል !

በኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ የመጨረሻ ሳምንት መርሐ ግብር ቅዱስ ጊዮርጊስ ከፋሲል ከነማ ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 4ለ0 በሆነ ውጤት አሸንፈዋል።

የፈረሰኞቹን የማሸነፊያ ግቦች አማኑኤል ኤርቦ 2x ፣ ተገኑ ተሾመ እና ዳዊት ተፈራ ከመረብ ማሳረፍ ችለዋል።

ቅዱስ ጊዮርጊስ በውድድር ዘመኑ አስራ ሶስት ጨዋታ አሸንፎ ዘጠኝ አቻ ወጥቶ ስምንት ተሸንፎ አጠናቋል።

ፋሲል ከነማ በበኩሉ አስራ አንድ አሸንፎ አስራ አንድ አቻ ተለያይቶ በስምንቱ ተሸንፎ አጠናቀዋል።

የቅዱስ ጊዮርጊሱ የፊት መስመር አጥቂ አማኑኤል ኤርቦ በክለቡ የመጀመሪያ አመት ቆይታው አስራ ሶስት የሊግ ግቦችን በማስቆጠር አጠናቋል።

የሊጉ ደረጃቸው ምን ይመስላል ? 

5️⃣ ቅዱስ ጊዮርጊስ :- 48 ነጥብ

6️⃣ ፋሲል ከነማ :- 44 ነጥብ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
አርሰናል ዴቪድ ራያን በቋሚነት አስፈርሟል ! የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል በውሰት ከብሬንትፎርድ ያስፈረሙትን ስፔናዊ ግብ ጠባቂ ዴቪድ ራያ ኮንትራት የመግዛት አማራጫቸውን ተጠቅመው ቋሚ ማድረጋቸው ተገልጿል። መድፈኞቹ ለግብ ጠባቂው የዝውውር ሒሳብ በውሉ ውስጥ ተካቶ የነበረውን የመግዛት አማራጭ ሒሳብ 27 ሚልዮን ፓውንድ መክፈላቸው ተነግሯል። የእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ የወርቅ ጓንት አሸናፊው…
ዴቪድ ራያ በይፋ የአርሰናል ተጨዋች ሆኗል !

የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል ስፔናዊውን ግብ ጠባቂ ዴቪድ ራያ ከብሬንትፎርድ በቋሚነት ማስፈረማቸውን ይፋ አድርገዋል።

ዴቪድ ራያ በአርሰናል ቤት የረጅም ጊዜ ኮንትራት መፈረሙ ሲገለፅ " እዚህ መሆኔ ህልሜን እውን አድርጎልኛል ለተደረገልኝ ድጋፍ ሁሉ አመሰግናለሁ።"ሲል ከፊርማው በኋላ ተናግሯል።

ሚኬል አርቴታ በበኩላቸው " ዴቪድ ራያ ባለፈው አመት የእኛ አስፈላጊ ተጨዋች መሆኑን አሳይቷል ለቡድኑ ትልቅ ዜና ነው ከእሱ ጋር በመስራታችን ደስተኞች ነን።"ብለዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
" ሮናልዶን ባደንቅውም ነገ እንዲደሰት አልፈልግም " ምባፔ

የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን አምበል ኪሊያን ምባፔ ወደ ሪያል ማድሪድ የሚያመራው የሮናልዶን ቀጣይ ታሪክ ለማስቀጠል ሳይሆን የራሱን ታሪክ ለመፃፍ መሆኑን ተናግሯል።

ኪሊያን ምባፔ ከነገው የፖርቹጋል የአውሮፓ ዋንጫ ሩብ ፍፃሜ ጨዋታ በፊት ከጋዜጠኞች ጋር ቆይታ አድርጎ ነበር።

ኪሊያን ምባፔ በቆይታው ምን አለ ?

- " በሪያል ማድሪድ የመጫወት ህልሜን የማሳካበት እድል አግኝቻለሁ በማድሪድ ቤት የራሴን ታሪክ መፃፍ እፈልጋለሁ።

- ሮናልዶ በሪያል ማድሪድ ደማቅ ታሪክ አለው እኔም የራሴን መፃፍ እፈልጋለሁ ለእሱ አድናቆት አለኝ ከእሱ ጋር ግንኙነት አለን አሁንም ቢሆን በየጨዋታው ኮከብ ነው።

- ለክርስቲያኖ ሮናልዶ ትልቅ ክብር አለኝ ነገርግን በነገው ጨዋታ ደስተኛ እንዲሆን አልፈልግም ምክንያቱም እኛ ግማሽ ፍፃሜ መድረስ እንፈልጋለን።

- ፔፔን መጋፈጥ ቀላል አለመሆኑን እናውቃለን በማድሪድ እና ፖርቹጋል ላለው አስደናቂ ታሪክ ክብር አለኝ ከእነደሱ አይነት ተጨዋች ጋር መጫወት ክብር ነው።"ሲል ተደምጧል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ሲዳማ ቡና አመቱን በድል አጠናቀዋል !

በኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ የመጨረሻ ሳምንት መርሐ ግብር ሲዳማ ቡና ከባሕር ዳር ከተማ ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 2ለ1 በሆነ ውጤት አሸንፈዋል።

የሲዳማ ቡናንን የማሸነፊያ ግቦች ይገዙ ቦጋለ ከመረብ ማሳረፍ ሲችል ለባሕር ዳር ከተማ ፍፁም ጥላሁን አስቆጥሯል።

ባሕር ዳር ከተማ መሸነፉን ተከትሎ ኢትዮጵያ ቡና የዘንድሮውን የኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ ሶስተኛ ደረጃን ይዘው ማጠናቀቃቸው ተረጋግጧል።

የሊጉ ደረጃቸው ምን ይመስላል ? 

4️⃣ ባሕር ዳር ከተማ :- 50 ነጥብ

1️⃣1️⃣ ሲዳማ ቡና :- 40 ነጥብ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
" ቶኒ ክሩስን አርብ ወደ ጡረታው እንሸኘዋለን " ሆሴሉ የስፔን ብሔራዊ ቡድን የፊት መስመር ተጨዋች ሆሴሉ ቶኒ ክሩስ አርብ የመጨረሻ ጨዋታውን እንደሚያደርግ በሰጠው አስተያየት ተናግሯል። " ከክሩስ ጋር መጫወት ለእኔ ክብር ነው የመልበሻ ቤት ጓደኛዬ ነበር ብዙ ነገሮችን አግዞኛል ብዙ ምክረም ሰጥቶኛል እሱን ማመስገን እፈልጋለሁ።"ሲል ሆሴሉ ተናግሯል። " እሱ የማድሪድም ሆነ የጀርመን ቁልፍ ተጨዋች…
" ነገ የክሩስ መጨረሻ ጨዋታ እንዳይሆን የቻልነውን እናደርጋለን " ጉንዶጋን

የጀርመን ብሔራዊ ቡድን አምበል ኢልካይ ጉንዶጋን በነገው የሩብ ፍፃሜ ጨዋታ ቡድናቸው ስፔንን ለማሸነፍ የቻለውን ሁሉ እንደሚያደርግ ተናግሯል

" የነገው የስፔን ጨዋታ የቶኒ ክሩስ የመጨረሻ ጨዋታ አይሆንም " የሚለው ኢልካይ ጉንዶጋን ይህ እንዳይሆን በጨዋታው የቻልነውን ሁሉ እናደርጋለን በማለት ተናግሯል።

" ለነገው ጨዋታ ጓጉተናል ከከባድ ጨዋታዎች አንዱ ነው ፣ ሁሉም ጨዋታ እንደ ፍፃሜ ነው ባለፉት ጨዋታዎች ቁጥሮች ካየን ስፔን ከእኛ ይሻላሉ ነገ መቀየር አለብን።" ጉንዶጋን

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
ቶተንሀም ከተጫዋቹ ጋር በይፋ ተለያየ ! ቶተንሀም ከፈረንሳዊው የመሐል ሜዳ ተጨዋች ታንጎይ ንዶምቤሌ ጋር ያላቸውን ኮንትራት በስምምነት ማቋረጣቸውን ይፋ አድርገዋል። ያለፈውን የውድድር አመት በውሰት በቱርኩ ክለብ ጋላታሳራይ ቤት ያሳለፈው ታንጎይ ንዶምቤሌ በቶተንሀም ቤት የአንድ አመት ውል ይቀረው ነበሩ። የ 27ዓመቱ ተጨዋች ታንጎይ ንዶምቤሌ ከአምስት አመታት በፊት ከፈረንሳዩ ክለብ ሊዮን በ55…
ታንጎይ ንዶምቤሌ አዲስ ክለብ ተቀላቅሏል !

በቅርቡ ከቶተንሀም ጋር የተለያየው ፈረንሳዊው የመሐል ሜዳ ተጨዋች ታንጎይ ንዶምቤሌ ኒስን በነፃ ዝውውር መቀላቀሉ ይፋ ተደርጓል።

የ 27ዓመቱ የመሐል ሜዳ ተጨዋች ታንጎይ ንዶምቤሌ በፈረንሳዩ ክለብ ኒስ ቤት እስከ 2026 የሚያቆየውን የሁለት አመት ኮንትራት መፈረሙ ተገልጿል።

ያለፈውን የውድድር አመት በውሰት በቱርኩ ክለብ ጋላታሳራይ ቤት ያሳለፈው ታንጎይ ንዶምቤሌ ከአምስት አመታት በፊት ከፈረንሳዩ ክለብ ሊዮን በ55 ሚልዮን ፓውንድ ቶተንሀምን መቀላቀሉ አይዘነጋም።

@tikvahethsport      @kidusyoftahe
ዩናይትድ የግብ ጠባቂ አሰልጣኝ ሊቀጥር ነው !

ማንችስተር ዩናይትድ ያለፈውን የውድድር አመት በበርንሌይ ቤት ያሳለፉትን የግብ ጠባቂዎች አሰልጣኝ ጄሌ ቴን ሮዌላርን በሀላፊነት ሊሾሙ መሆኑ ተገልጿል።

የግብ ጠባቂዎች አሰልጣኙ በቅርቡ ከበርንሌይ ጋር ከተለያዩ በኋላ አያክስን የተቀላቀሉ ቢሆንም ማንችስተር ዩናይትድ ካሳ ከፍሎ ለመውሰድ እየሰራ መሆኑ ተገልጿል።

ያለፉትን አምስት አመታት በማንችስተር ዩናይትድ የግብ ጠባቂዎች አሰልጣኝ ሆነው ያገለገሉት ሪቻርድ ሀርቲስ ክለቡን እንደሚለቁ ተዘግቧል።

አሰልጣኝ ኤሪክ ቴንሀግ በበኩላቸው አሰልጣኙ በግብ ጠባቂዎች በኩል ከሚፈልጉት የጨዋታ እቅድ ጋር የሚስማሙ ናቸው የሚል እምነት እንዳላቸው ተነግሯል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
Forwarded from HEY Online Market
Stock Clearance Discount 2

📞 0925927457 @eBRO4
📞 0953964175 @heymobile

•iP 7+, Black, 128GB, 99% 12K
•iP X, Black, 256 GB, 100%,12K ⚠️
•iP XS, White, 64 GB, 100% 19K
•iP XS Max, Gold, 64GB, 83%, 25K
•iP XS Max, Gold, 256GB, 88% 29K
•iP 11, Red, 64GB, 100% 28K ⚠️
•iP 11, Black, 128GB, 85%, 33K
•iP 11, Purple, 128GB, 88% 33K
•11 Pro, Black, 64GB, 100% 39K ⚠️
•11 Pro, White, 64GB, 87% 36K
•11 Pro Max, Black, 64GB, 86%, 46K

•11 Pro Max, Black, 256GB, -% 40⚠️
•iP 12, Red, 128GB, 88%, 42K
•iP 12, White, 128GB, 88% 42K
•iP 12, Green, 128GB, 86% 42K
•12 Pro, Blue, 128GB, 89% 49K
•12 Pro Max, Blue, 512GB, 84% 64K
•iP 13 Min, Pink, 256GB, 92% 34K
•iP 13, Blueback, 128GB, 90% 56K
•iP 13, Black, 128GB, 92% 49K ⚠️

•iP 13, Red, 128GB, 86%, 56K
•iP 13, Black, 128GB, 89%, 58K
•13 Pro, Golden, 256GB, 87% 69K
•13 Pro, Blue, 512GB/88% 69K ⚠️
•13 ProMax, Black, 128 GB, 87% 74K
•13 ProMax, 256GB, 86%, 64K⚠️
•13 ProMax, 256GB, 85%, 74K⚠️
•13 ProMax, Gold, 256GB, 86%, 79K
•13 Pro Max, Gold, 256 GB,88% 79K
•13 Pro Max, Blue, 256GB, 94% 79K
•13 Pro Max, 1TB, 88%, 69K ⚠️
•13 Pro Max, Blu, 256GB/ -% 70K ⚠️

Exchange Available!
Free Delivery 🚚

@heyonlinemarket
https://heymobile.store/catalogue
ሽመልስ በቀለ 1⃣8⃣ ገስት ሀውስ

በውቢቷ ሀዋሳ ቆይታዎ የት ለማረፍ አስበዋል ? ንፁህ እና በደንበኞቻችን ተወዳጅ በሆነው የእንግዳ ማረፊያችን መጥተው የእረፍት ጊዜውን ያሳልፉ።

እንግዶቻችንን ተቀበልን ለእይታ ሳቢ በሆነው የእንግዳ ማረፊያችን ማስተናገድ ከጀመርን አመታትን አስቆጥረናል።

አድራሻችን :- ሀዋሳ አርቴፍሻል ስታዲየም መንገድ ላይ ያገኙናል።

ለተጨማሪ መረጃ እና ለትዕዛዝዎ ይደውሉልን :- 0928684848

#ShemelesBekele18
#CopaAmerica2024

በኮፓ አሜሪካ ሩብ ፍፃሜ ጨዋታ አርጀንቲና ከኢኳዶር ጋር ያደረገችውን ጨዋታ በመለያ ምት 4ለ2 በማሸነፍ ግማሽ ፍፃሜውን ተቀላቅላለች።

ሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች መደበኛውን የጨዋታ ክፍለጊዜ 1ለ1 በሆነ አቻ ውጤት ሲያጠናቅቁ ግቦቹን ለአርጀንቲና ሊሳንድሮ ማርቲኔዝ ለኢኳዶር ሮድሪጉዌዝ አስቆጥረዋል።

የአርጀንቲና ግብ ጠባቂ ኤሚሊያኖ ማርቲኔዝ ሁለት የመለያ ምቶችን ማዳን ሲችል ሊዮኔል ሜሲ የመጀመሪያውን የአርጀንቲና መለያ ምት ማስቆጠር ሳይችል ቀርቷል።

አርጀንቲና በግማሽ ፍፃሜው ዛሬ ሌሊት 10:00 ሰዓት ከሚጫወቱት ካናዳ እና ቬንዙዌላ አሸናፊ ጋር የምትጫወት ይሆናል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
" ሮናልዶ ለጨዋታው ዝግጁ ነው " ሮቤርቶ ማርቲኔዝ

የፖርቹጋል ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ሮቤርቶ ማርቲኔዝ ከዛሬ ምሽቱ የፈረንሳይ የአውሮፓ ዋንጫ ሩብ ፍፃሜ ጨዋታ በፊት አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

ሮቤርቶ ማርቲኔዝ ካነሷቸው ሀሳቦች መካከልም :-

- " በስሎቬንያ ጨዋታ የተፈጠረው ተፈጥሯል ሮናልዶ የመጀመሪያውን መለያ ምት ሀላፊነት በመውሰድ አስቆጥሯል ያለውን ብስለትም አሳይቷል።

- የቡድኑ አምበል ክርስቲያኖ ሮናልዶ ለዛሬው የፈረንሳይ ጨዋታ ዝግጁ በደንብ ዝግጅት አድርጓል ለጨዋታው ዝግጁ ነው።

- በጨዋታው ወሳኙ ነገር በመልሶ ማጥቃት ሲጫወቱ መጠንቀቅ ነው ፈረንሳይ ምባፔ ብቻ አይደለም ያላት ሌሎች ከባድ አጥቂዎች አሏቸው እነሱን ማስቆም አለብን።

- ለፈረንሳይ ክብር አለን በጥሩ መልኩ ይከላከላሉ ጥሩ ያጠቃሉ እኛ እንደ ቡድን ጥሩ አቋም ማሳየት አለብን በሜዳ ክፍላችን ላይ ጠንክረን መከላከል አለብን ለአንድ ተጨዋች እቅድ የለንም።"ሲሉ ተደምጠዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
" ተጋጣሚ ሲያጠቃ መከላከል ሳይሆን የበለጠ ማጥቃት አለብን " ሉዊስ ዴ ላ ፉንቴ

የስፔን ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ሉዊስ ዴ ላ ፉንቴ በምሽቱ የጀርመን ብሔራዊ ቡድን ጨዋታ ቡድናቸው የትኛውንም ስህተት ከመስራት እንዲጠነቀቅ አሳስበዋል።

" ተጋጣሚ አጥቅቶ ሲጫወት ምላሽ ለመስጠት ትክክለኛው መንገድ የበለጠ አጥቅቶ መጫወት ነው " የሚሉት ሉዊስ ዴ ላ ፉንቴ በዚህ ጨዋታ ምንም አይነት ስህተት መስራት የለብንም በማለት ተናግረዋል።

" ጀርመን ጠንካራ የሚባል ቡድን ይዛ ትገባለች እኛም ይህንኑ ለማድረግ እንሞክራለን ፣ የራሳችንን አቅም እናውቃለን የእነሱንም አቅም እናውቃለን እርስበርስ እንከባበራለን።" ሉዊስ ዴ ላ ፉንቴ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ኢኳዶር ከአሰልጣኟ ጋር ተለያይታለች !

ከኮፓ አሜሪካ የተሰናበተው የኢኳዶር ብሔራዊ ቡድን ከስፔናዊው አሰልጣኝ ፌሊክስ ሳንቼዝ ጋር መለያየቱ ተገልጿል።

አሰልጣኝ ፌሊክስ ሳንቼዝ ከሀላፊነታቸው የተነሱት ኢኳዶር በአርጀንቲና በመለያ ምት ተሸንፋ ከኮፓ አሜሪካ ውድድር ውጪ መሆኗን ተከትሎ እንደሆነ ተገልጿል።

በቡድኑ የሁለት አመት ኮንትራት የነበራቸው አሰልጣኝ ፌሊክስ ሳንቼዝ ቡድኑን ለኮፓ አሜሪካ ሩብ ፍፃሜ ሲያደርሱ በአለም ዋንጫ ማጣሪያ መሳተፍ በሚያስችላቸው ደረጃ ላይ ይገኛሉ።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
ሳሙኤል ኤቶ ክስ ላይ እንደሚገኝ ተገለፀ ! የካሜሮን እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት እና የቀድሞ ታሪካዊ ተጨዋች ሳሙኤል ኤቶ ክስ ቀርቦበት በአፍሪካ እግርኳስ ኮንፌዴሬሽን ( ካፍ ) እና ፊፋ ምርመራ እየተካሄደበት እንደሚገኝ ተገልጿል። ሳሙኤል ኤቶ በጨዋታ ማጭበርበር ፣ አካላዊ ጥቃት በማድረስ ፣ ሁከት በማነሳሳት እና የተሳሳተ መረጃ በማሰራጨት ተከሶ ምርመራ ላይ መሆኑ ተዘግቧል። ክሶቹን የሚያስረዱ…
ሳሙኤል ኤቶ በሀላፊነቱ ይቀጥላል !

የካሜሮን እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት እና የቀድሞ ታሪካዊ ተጨዋች ሳሙኤል ኤቶ ቀርቦበት በነበረው ክስ በአንዱ ጥፋተኛ ሆኖ መገኘቱ ተገልጿል።

የካፍ ዲሲፕሊን ኮሚቴ ሳሙኤል ኤቶ የቀረበበትን የጨዋታ ማጭበርበር እና በስፖርት ስነምግባር ጥሰት ክስ ምርመራ ሲያደርግ እንደነበር ይታወሳል።

አሁን ላይ ካፍ ይፋ ባደረገው መረጃ ሳሙኤል ኤቶ የተከሰሰበትን የጨዋታ ማጭበርበር ጥፋት የሚያረጋግጥ ማስረጃ ማግኘት እንዳልቻለ አሳውቋል።

ይሁን እንጂ ሳሙኤል ኤቶ የሀገሪቱ እግርኳስ ፌዴሬሽን ሀላፊ ሆኖ ሳለ ከስፖርት ውርርድ ተቋም ጋር በገባው የአምባሳደርነት ስምምነት ምክንያት 200,000 ዶላር ቅጣት ተጥሎበታል።

ሳሙኤል ኤቶ በቀረቡበት ክሶች ጥፋተኛ የሚሆን ከሆነ ከእግርኳስ ሊታገድ እንደሚችል ሲገለፅ የነበረ ቢሆንም አሁን ላይ በሀላፊነት እንደሚቀጥል ካፍ አሳውቋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
2024/10/02 22:37:17
Back to Top
HTML Embed Code: