Telegram Web Link
Forwarded from WANAW SPORT
🎁 #ይገምቱ#ይሸለሙ!

🏆  በዛሬው ምሽት የ2024 አውሮፓ ዋንጫ መክፈቻ ጨዋታ ማን ያሸንፍ ይሆን?

🇩🇪 ጀርመን ወይስ ስኮትላንድ 🇸🇪

💬 ግምትዎን #በቴሌግራም ገፃችን (https://www.tg-me.com/wanawsportwear) ኮሜንት ላይ ብቻ ያስቀምጡልን!

⚠️ የውድድሩ ህጎች፦
👉🏾 የጨዋታውን አሸናፊ ሀገር እስከ የግብ መጠኑ #በትክክል ቀድመው የሚገምቱ #2 ተከታታዮቻችን የዋናውን የጂም ማልያዎች ይሸለማሉ።
👉🏾 የዋናውን ማህበራዊ ገፆች መከተል፣ መወዳጀትና ማጋራት አይዘንጉ።
👉🏾 የተስተካከሉ መልሶች በፍፁም ተቀባይነት የላቸውም።

Instagram | Facebook | TikTok

🏅 ዋናው ወደፊት...

@wanawsportwear
ድሬዳዋ ከተማ ድል አድርጓል !

በ2016 የኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ ሀያ ሰባተኛ ሳምንት መርሐ ግብር ድሬዳዋ ከተማ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 1ለ0 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችለዋል።

የድሬዳዋ ከተማን የማሸነፊያ ግብ ተመስገን ደረሰ ከመረብ ማሳረፍ ችሏል።

የአምናው የሊጉ አሸናፊ ቅዱስ ጊዮርጊስ በውድድር አመቱ #ስምንተኛ ሽንፈቱን አስተናግዷል።

ፈረሰኞቹ ካለፉት ዘጠኝ የሊግ ጨዋታዎች ማሸነፍ የቻሉት በአንዱ ነው በአምስቱ ሲሸነፍ በሶስቱ አቻ ተለያይተዋል።

የሊጉ ደረጃ ሰንጠረዥ ምን ይመስላል ? 

5️⃣ ቅዱስ ጊዮርጊስ :- 43 ነጥብ

8️⃣ ድሬዳዋ ከተማ  :- 40 ነጥብ

ቀጣይ መርሐ ግብር ምን ይመስላል ?

- ቅዱስ ጊዮርጊስ ከ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ

- ድሬዳዋ ከተማ ከ ሀድያ ሆሳዕና

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
" እዚህ የመጣነው ጥሩ ውጤት ለማስመዝገብ ነው " ሞድሪች

የክሮሽያ ብሔራዊ ቡድን የመሐል ሜዳ ተጨዋች ሉካ ሞድሪች ቡድናቸው በአውሮፓ ዋንጫ ውድድር ትልቅ ውጤት ለማስመዝገብ መዘጋጀቱን ተናግሯል።

ነገ ከስፔን ጋር ከሚያደርጉት ጨዋታ በፊት አስተያየቱን የሰጠው ሉካ ሞድሪች " በአለም ዋንጫ እንዳደረግነው ጥሩ ውጤት ማስመዝገብ እንፈልጋለን ወደዚህ የመጣነው ትልቅ ውጤት አልመን ነው " ብሏል።

በአውሮፓ እና አለም ዋንጫ ውድድሮች ዙሪያ እየተሰጡ ስለሚገኙ አስተያየቶች የተጠየቀው ሞድሪች " ሁለቱን ላወዳድር አልፈልግም ነገርግን አለም ዋንጫ ከባድ ይመስለኛል አለም ዋንጫ የአለም ምርጥ ቡድኖችን የሚያገናኝ ብቸኛው ውድድር ነው።"ብሏል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
አዳም ላላና ወደ ሳውዝሀምፕተን ሊያመራ ነው ! እንግሊዛዊው የብራይተን የመሐል ሜዳ ተጨዋች አዳም ላላና በቀጣይ ወደ ቀድሞ ክለቡ ሳውዝሀምፕተን ሊያመራ መሆኑ ተገልጿል። በብራይተን ቤት ስድስት አመታትን ያሳለፈው አዳም ላላና በዚህ ክረምት ውሉ ሲጠናቀቅ ክለቡን እንደሚለቅ ማሳወቁ ይታወቃል። የቀድሞ የሊቨርፑል የመሐል ሜዳ ተጨዋች አዳም ላላና አሁን ላይ ዝውውሩ ባይጠናቀቅም የቀድሞ ክለቡን ሳውዝሀምፕተን…
አዳም ላላና ሳውዝሀምፕተንን ተቀላቀለ !

እንግሊዛዊው የመሐል ሜዳ ተጨዋች አዳም ላላና የቀድሞ ክለቡ ሳውዝሀምፕተንን ለአንድ የውድድር አመት መቀላቀሉ ይፋ ተደርጓል።

አዳማ ላላና በቅርቡ አራት አመታትን ካሳለፈበት ብራይተን ኮንትራቱ መጠናቀቁን ተከትሎ መለያየቱ ይታወሳል።

የቀድሞ የሊቨርፑል የመሐል ሜዳ ተጨዋች አዳም ላላና የቀድሞ ክለቡን ሳውዝሀምፕተን ከአስር አመታት በኋላ በድጋሜ ተቀላቅሏል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
የጨዋታ አሰላለፍ !

4:00 ጀርመን ከ ስኮትላንድ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
#EURO2024

11 '  ጀርመን 1 - 0 ስኮትላንድ

ቨርትዝ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
19 '  ጀርመን 2 - 0 ስኮትላንድ

ቨርትዝ
ሙሲያላ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
45+1 '  ጀርመን 3 - 0 ስኮትላንድ

ቨርትዝ
ሙሲያላ
ሀቨርትዝ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
እረፍት |  ጀርመን 3 - 0 ስኮትላንድ

ቨርትዝ
ሙሲያላ
ሀቨርትዝ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
67 '  ጀርመን 4 - 0 ስኮትላንድ

    ቨርትዝ
    ሙሲያላ
    ሀቨርትዝ
ፉልክሩግ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
86 '  ጀርመን 4 - 1 ስኮትላንድ

    ቨርትዝ ሩዲገር ( በራስ ላይ )
    ሙሲያላ
    ሀቨርትዝ
    ፉልክሩግ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
90 '  ጀርመን 5 - 1 ስኮትላንድ

    ቨርትዝ         ሩዲገር ( በራስ ላይ )
    ሙሲያላ
    ሀቨርትዝ
    ፉልክሩግ
ኤምሪ ቻን

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ጀርመን ውድድሯን በድል ጀምራለች !

የጀርመን ብሔራዊ ቡድን የአውሮፓ ዋንጫ የመክፈቻ ጨዋታውን ከስኮትላንድ አቻው ጋር አድርጎ 5ለ1 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችሏል።

ለጀርመን ብሔራዊ ቡድን ግቦችን ፍሎሪያን ቨርትዝ ፣ ጀማል ሙሲያላ ፣ ካይ ሀቨርትዝ ፣ ኒክላስ ፉልክሩግ እና ኤምሪ ቻን ሲያስቆጥሩ የስኮትላንድን ብቸኛ ግብ ሩዲገር በራሱ ግብ ላይ ከመረብ አሳርፏል።

የ 21ዓመቱ የፊት መስመር ተጨዋች ፍሎርያን ቨርትዝ በአውሮፓ ዋንጫው ለጀርመን ብሔራዊ ቡድን ግብ ያስቆጠረ በእድሜ ትንሹ ተጨዋች በመሆን አዲስ ታሪክ ፅፏል።

የ 36ዓመቱ የጀርመን ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ጁሊያን ኔግልስማን በውድድሩ ታሪክ ብሔራዊ ቡድን የመራ በእድሜ ትንሹ አሰልጣኝ መሆን ችሏል።

ኒክላስ ፉልክሩግ ለጀርመን ብሔራዊ ቡድን ባደረጋቸው አስራ ሰባት ጨዋታዎች አስራ ሁለት ግቦችን ማስቆጠር ችሏል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
Play More and Spend less!

•PS4 Slim, 34,999 Birr
•PS4 PRO, 41,999 Birr
•Original Controller 6,499 Birr

Contact Us
0953964175 @heymobile

@heyonlinemarket
ሽመልስ በቀለ 1⃣8⃣ ገስት ሀውስ

በውቢቷ ሀዋሳ ቆይታዎ የት ለማረፍ አስበዋል ? ንፁህ እና በደንበኞቻችን ተወዳጅ በሆነው የእንግዳ ማረፊያችን መጥተው የእረፍት ጊዜውን ያሳልፉ።

እንግዶቻችንን ተቀበልን ለእይታ ሳቢ በሆነው የእንግዳ ማረፊያችን ማስተናገድ ከጀመርን አመታትን አስቆጥረናል።

አድራሻችን :- ሀዋሳ አርቴፍሻል ስታዲየም መንገድ ላይ ያገኙናል።

ለተጨማሪ መረጃ እና ለትዕዛዝዎ ይደውሉልን :- 0928684848

#ShemelesBekele18
TIKVAH-SPORT
ኢትዮጵያን በኦሎምፒክ የሚወክሉ አትሌቶች ዛሬ ይለያሉ ! ዛሬ ምሽት በስፔን ኔርጃ ሀገራችን ኢትዮጵያን በቀጣዩ የፓሪስ ኦሎምፒክ ውድድር በ10,000 ሜትር የሚወክሉ አትሌቶችን ለመለየት የመምረጫ ውድድር እንደሚደረግ ተገልጿል። ከምሽቱ የመምረጫ ውድድር በኋላ ኢትዮጵያን በፓሪስ ኦሎምፒክ ውድድር 10,000 ሜትር የሚወክሉ አትሌቶች ተለይተው ይታወቃሉ ተብሎ ይጠበቃል። ከዚህ በተጨማሪም ዛሬ ምሽት…
ኢትዮጵያን በኦሎምፒክ የሚወክሉ አትሌቶች ተለይተዋል !

ኢትዮጵያን በቀጣዩ የፓሪስ ኦሎምፒክ ውድድር በ10,000 ሜትር የሚወክሉ አትሌቶችን ለመለየት እንዲሁም የኦሎምፒክ ሚኒማ ለማሟላት የሙከራ ውድድሮች በስፔን ኔርጃ ተካሂደዋል።

በ800ሜ ወንዶች በተደረገው የኦሎምፒክ ሚኒማ ማሟያ ውድድር ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች 1:44:70 የሆነውን የኦሎምፒክ ሚኒማ ማሟላት ሳይችሉ ቀርተዋል።

በኦሎምፒክ 10000ሜ ሴቶች ኢትዮጵያን የሚወክሉ አትሌቶችን ለመለየ በተደረገው ውድድር ፎትዬን ተስፋይ ፣ ፅጌ ገብረሰላማ እና እጅጋየሁ ታዬ ተከታትለው በመግባት ማሸነፍ ችለዋል።

በወንዶች 10000ሜ ውድድር ዮሚፍ ቀጄልቻ ፣ በሪሁ አረጋዊ እና ሰለሞን ባረጋ ተከታትለው በመግባት ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ያለውን ደረጃ ይዘው ማጠናቀቅ ችለዋል።

በ1500ሜ ወንዶች ሚኒማ ማሟያ ውድድር አትሌት አበዲሳ ፈይሳ እና ሳሙኤል ተፈራ 3:33:50 የሆነውን የኦሎምፒክ ሚኒማ በሟሟላት አንደኛ እና ሁለተኛ ሆነው አጠናቀዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
" ጠንካራ ቡድን መሆናችንን እናውቃለን " ሉዊስ ዴ ላ ፉንቴ

የስፔን ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ሉዊስ ዴ ላ ፉንቴ ቡድናቸው ጠንካራ መሆኑን ዛሬ ከክሮሽያ ጋር ከሚያደርጉት ጨዋታ በፊት በሰጡት አስተያየት ተናግረዋል።

" በርካታ ባለ ጥሩ ተሰጥኦ ተጨዋቾችን ይዘናል "  ያሉት አሰልጣኝ ሉዊስ ዴ ላ ፉንቴ አንድ ላይ የምንጫወት ከሆነ ትልቅ ጥንካሬ ይሰጠናል በማለት ተናግረዋል።

አሰልጣኝ ሉዊስ ዴ ላ ፉንቴ ቀጥለውም ቡድናቸው ጥሩ መጫወት የሚችል ጠንካራ መሆኑን ገልፀው ሌሎች ሀገራትም በተመሳሳይ ደረጃ ስለሚሆኑ መጠንቀቅ አለብን ብለዋል።

የስፔን ብሔራዊ ቡድን ከክሮሽያ ብሔራዊ ቡድን ጋር ምሽት 1:00 ሰዓት በግዙፉ የበርሊን ኦሎምፒያስታድዮን ስታዲየም ይጫወታሉ።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
የሚል ዋል ቁጥር አንድ ግብ ጠባቂ ህይወቱ አለፈ !

የእንግሊዝ ሻምፒዮን ሺፑ ክለብ ሚል ዋል እና ምንቴኔግሮ ብሔራዊ ቡድን ግብ ጠባቂ ማቲሀ ሳርኪች በ 26ዓመቱ ህይወቱ ማለፉ ተገልጿል።

የሻምፒዮን ሺፑ ክለብ የሚል ዋል የግብ ጠባቂው ህይወት ማለፉን በይፋ ከማረጋገጥ ውጪ አሁን ላይ ተጨማሪ አስተያየት መስጠት እንደማይፈልጉ ገልፀዋል።

ግብ ጠባቂው ከአስር ቀናት በፊት የምንቴኔግሮ ብሔራዊ ቡድን በቤልጅየም በተሸነፈበት የወዳጅነት ጨዋታ ተሰልፎ መጫወት ችሎ ነበር።

ባለፈው አመት ከዎልቭስ ሚል ዋልን ተቀላቅሎ የክለቡ ቁጥር አንድ ግብ ጠባቂ መሆን ችሎ የነበረው ማቲሀ ሳርኪች በተጠናቀቀው አመት ካደረጋቸው ሳላሳ ሶስት ጨዋታዎች በአስራ ሁለቱ ግብ ሳይቆጠርበት መውጣት ችሏል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
የቀድሞ የአርሰናል ተጨዋች ህይወቱ አለፈ !

እንግሊዛዊው የቀድሞ የአርሰናል እና ኤቨርተን የፊት መስመር ተጨዋች ኬቪን ካምቤል በ54ዓመቱ ህይወቱ ማለፉ ተገልጿል።

በተንታኝነት እያገለገለ የነበረው የቀድሞ ተጨዋቹ ከሳምንት በፊት ከባድ ህመም አጋጥሞት ሆስፒታል ገብቶ እንደነበር ተዘግቧል።

የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል እንዲሁም ኤቨርተን በቀድሞ ተጨዋቻቸው ህልፈተ ህይወት የተሰማቸውን ሀዘን በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ገልፀዋል።

ኬቪን ካምቤል በአርሰናል ቤት ባሳለፋቸው አመታት ሁለት መቶ አስር ጨዋታዎች ሲያደርግ ሀምሳ አምስት ግቦችንም ማስቆጠር ችሏል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
2024/10/05 17:35:31
Back to Top
HTML Embed Code: