Telegram Web Link
Forwarded from HEY Online Market
•PlayStation 5
•Playstaion 5 Slim

•PlayStation 4 Slim
•PlayStation 4 Pro

•Playstaion portal
•PlayStation VR

Contact
0953964175 @heymobile

@heyonlinemarket
ሽመልስ በቀለ 1⃣8⃣ ገስት ሀውስ

በውቢቷ ሀዋሳ ቆይታዎ የት ለማረፍ አስበዋል ? ንፁህ እና በደንበኞቻችን ተወዳጅ በሆነው የእንግዳ ማረፊያችን መጥተው የእረፍት ጊዜውን ያሳልፉ።

እንግዶቻችንን ተቀበልን ለእይታ ሳቢ በሆነው የእንግዳ ማረፊያችን ማስተናገድ ከጀመርን አመታትን አስቆጥረናል።

አድራሻችን :- ሀዋሳ አርቴፍሻል ስታዲየም መንገድ ላይ ያገኙናል።

ለተጨማሪ መረጃ እና ለትዕዛዝዎ ይደውሉልን :- 0928684848

#ShemelesBekele18
የዛሬ ተጠባቂ ጨዋታዎች !

9:00 ኢትዮጵያ ቡና ከ ሀምበሪቾ

12:00 ሀድያ ሆሳዕና ከ ሀዋሳ ከተማ

1:00 ናፖሊ ከ ሊቼ

3:45 ኢምፖሊ ከ ሮማ

3:45 ሄላስ ቬሮና ከ ኢንተር ሚላን

4:00 ሲቪያ ከ ባርሴሎና

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ሲቲ የጎዳና ላይ ክብረበዓል ያዘጋጃሉ !

የእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ ዋንጫን አሸናፊው ማንችስተር ሲቲ የዋንጫ ድሉን ከደጋፊዎቻቸው ጋር በጎዳና ላይ እንደሚያከብሩ ተገልጿል።

ማንችስተር ሲቲዎቹ የጎዳና ላይ ክብረበዓሉን በዛሬው ዕለት በማንችስተር ከተማ የተለያዩ ቦታዎች በክፍት ባስ እየተዟዟሩ እንደሚያከብሩ አሳውቀዋል።

በአሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ የሚመራው ማንችስተር ሲቲ ለአራት ተከታታይ አመታት ፕርሚየር ሊጉን በማሳካት ደማቅ ታሪክ መፃፋቸው ይታወቃል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
" ማርቲኔዝ የጨዋታው ልዩነት ፈጣሪ ነበር " ጋርዲዮላ

የማንችስተር ሲቲው ዋና አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ የማንችስተር ዩናይትድ ተከላካይ ሊሳንድሮ ማርቲኔዝ በትላንትናው ጨዋታ ልዩነት ፈጣሪ እንደነበር ገልጸዋል።

" ሊሳንድሮ ማርቲኔዝ ከአለም ምርጥ አምስት የመሐል ተከላካዮች አንዱ ነው " በማለት የገለፁት አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ በትላንቱ ጨዋታ ልዩነት ፈጣሪው ተጨዋች እሱ ነበር።"ብለዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ምባፔ ከቀናት በኋላ ማረፊያውን ያሳውቃል !

ፈረንሳዊው የፊት መስመር ተጨዋች ኪሊያን ምባፔ ቀጣይ ማረፊያው የሚሆነው ክለብ ከተወሰኑ ቀናት በኋላ በይፋ እንደሚያሳውቅ ገልጿል።

በቅርቡ ከፒኤስጂ ጋር እንደሚለያይ ያስታወቀው ኪሊያን ምባፔ ሪያል ማድሪድን እንደሚቀላቀል የሚጠበቅ ቢሆንም እስካሁን በይፋ አላረጋገጠም።

ተጨዋቹ ትላንት ምሽት የፒኤስጂ የመጨረሻ ጨዋታውን አድርጎ ክለቡን በተሰናበተበት ጨዋታ በሰጠው አስተያየት " ቀጣይ ክለቤን በትክክለኛው ሰዓት አሳውቃለሁ ጥቂት ቀናቶች ይቀራሉ " በማለት ተናግሯል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
Forwarded from WANAW SPORT
📢 #የዋናውን አዲስ ብስራት እናስታውስዎ!

👉🏾 በፕሪሚየር ሊግ የጥራት ደረጃ የተዘጋጁ፣ በፈለጉት ዲዛይንና ቀለም የሚሰሩ ውብና ልዩ ማሊያዎች ለእናንተ።

👉🏾 ከ20 ብዛት ጀምሮ በ1400 ብር ብቻ እንደምርጫዎ ማዘዝ ይችላሉ።

🔥 ይፍጠኑ፣ ይዘዙን፣ በፍጥነት ሰርተን ባሉበት በነፃ እናደርሳለን!

📍አድራሻችን:- ገርጂ መብራት ሃይል የካቲት ወረቀት ፊትለፊት፣ አለም ገብሬ ህንፃ፣ 2ተኛ ፎቅ።

📌 ለበለጠ መረጃና ትዕዛዝ 📲 09011382830910851535 እና 0913586742 ላይ ይደውሉ።

👉🏾 እንዲሁም በቴሌግራም @Wanawsales ላይ የሽያጭ ሰራተኞቻችንን በቀጥታ በማናገር ወይም በቴሌግራም ቦት @WANAWSbot በኩል ይዘዙን።

Instagram | Facebook | TikTok

🏅 ዋናው ወደፊት...

@wanawsportwear
የኢትዮጵያ  ቡና ይፋዊ አጋር የሆነው ቤቲካ - የኢትዮጵያ ቡናን  21ኛ የጨዋታ ቀን የዲጂታል መፅሄት ይዞ ቀርቧል።
በመፅሄቱ ላይ የዕለቱ ጨዋታን የተመለከቱና ሌሎች የተለያዩ መረጃዎች የሚቀርቡ ይሆናል፡፡

መፅሄቱን ለማግኘት ሊንኩን ይጫኑ https://www.tg-me.com/betikaethiopia/5293

የጨዋታ መፅሄት ቁጥር 21
ኢትዮጵያ ቡና ከሀምበሪቾ ዱራሜ
ዛሬ 09:00

ቤቲካ - የኢትዮጵያ ቡና ይፋዊ አጋር
ፒኤስጂ በዝውውር መስኮቱ በትኩረት ይሳተፋል !

ከፈረንሳዊው ተጨዋች ኪሊያን ምባፔ ጋር የሚለያየው ፒኤስጂ በሚቀጥለው ክረምት የተጨዋቾች የዝውውር መስኮት ንቁ ተሳትፎ እንደሚያደርግ አሰልጣኝ ሉዊስ ኤንሪኬ ገልጸዋል።

ኪሊያን ምባፔን የሚተካላቸው ተጨዋቾች ፈፅሞ ማግኘት እንደማይቻል የገለፁት አሰልጣኝ ሉዊስ ኤንሪኬ ከእሱ የተለየ ተጨዋች ለማስፈረም እንጥራለን ብለዋል።

አሰልጣኙ ሲናገሩም በዝውውር መስኮቱ ፒኤስጂ #ስድስት የሚደርሱ ጥራት ያላቸው ተጨዋቾች ለማስፈረም የተቻለውን ጥረት እንደሚያደርግ ጠቁመዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
#TkvahGoal

አርጀንቲናዊው የማንችስተር ዩናይትድ የፊት መስመር ተጨዋች አሌሀንድሮ ጋርናቾ ኤቨርተን ላይ ያስቆጠረው የመቀስ ምት ግብ የእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ የአመቱ ምርጥ ግብ በመሆን መመረጥ ችሏል።

ግቡን በጎል ቻናላችን በቪዲዮ መመልከት ይችላሉ።

የጎል ቻናላችን 👉 https://www.tg-me.com/+rbdEU4UaEdQxYWFk

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ሊዮናርዶ ቦኑቺ ጫማውን ሰቀለ !

ጣልያናዊው የቀድሞ ጁቬንቱስ አንጋፋ የተከላካይ ስፍራ ተጨዋች ሊዮናርዶ ቦኑቺ በአመቱ መጨረሻ ራሱን ከፕሮፌሽናል እግርኳስ እንደሚያገል በይፋ አስታውቋል።

የ 37ዓመቱ ተከላካይ ሊዮናርዶ ቦኑቺ አሁን ላይ ለቱርኩ ክለብ ፌነርባቼ እየተጫወተ የሚገኝ ሲሆን ዛሬ የሊግ የመጨረሻ ጨዋታውን ያደርጋል።

ሊዮናርዶ ቦኑቺ ለቀድሞ ክለቡ ጁቬንቱስ ሶስት መቶ ሀምሳ አምስት ጨዋታዎች ላይ ተሰልፎ መጫወት የቻለ ሲሆን ሀያ ሰባት ግቦችንም ማስቆጠር ችሏል።

ሊዮናርዶ ቦኑቺ በእግር ኳስ ህይወቱ ከጁቬንቱስ ጋር #ስምንት የጣሊያን ሴርያ እንዲሁም አንድ የአውሮፓ ዋንጫን ጨምሮ አስራ ስምንት ዋንጫዎችን ማሳካት ችሏል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ቡናማዎቹ በሰፊ የግብ ልዩነት አሸነፉ !

በኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ የሀያ ስድስተኛ ሳምንት መርሐ ግብር ኢትዮጵያ ቡና ከሀምበሪቾ ዱራሜ ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 6ለ1 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችለዋል።

የቡናማዎቹን የማሸነፊያ ግቦች መሐመድ ናስር 2x ፣ አማኑኤል ዮሀንስ ፣ አማኑኤል አድማሱ ፣ ጫላ ተሺታ እና ምንታምር መለሰ በራሱ ግብ ላይ አስቆጥረዋል።

የሀምበሪቾ ዱራሜን ብቸኛ ግብ አላዛር አድማሱ ማስቆጠር ችሏል።

በአሰልጣኝ ነፃነት ክብሬ የሚመራው ኢትዮጵያ ቡና ሶስተኛ ተከታታይ ድሉን ማስመዝገብ ችሏል።

ሀምበሪቾ ዱራሜ በውድድር አመቱ ሀያኛ ሽንፈቱን አስተናግዷል።

የሊጉ ደረጃ ሰንጠረዥ ምን ይመስላል ? 

4️⃣ ኢትዮጵያ ቡና :- 44 ነጥብ

1️⃣6️⃣ ሀምበሪቾ ዱራሜ :- 8 ነጥብ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
#Tecno #Camon30Pro5G

ልዩ ዲዛይን እና ቴክኖሎጂ አጣምሮ የቀረበዉ Tecno Camon30 Pro 5G ምርጫዎ ያድርጉ!

#Camon30Et #Camon30Pro5GEt #Camon30 #Camon30Pro5G #TecnoEt
ባየር ሊቨርኩሰን የዋንጫ ድሉን በማክበር ላይ ነው !

የጀርመን ቡንደስሊጋ እና የጀርመን ፖካል ካፕ ዋንጫዎችን በማሳካት ጥሩ የውድድር አመት ማሳለፍ የቻለው ባየር ሊቨርኩሰን የሁለት ዋንጫ ድሉን በስታዲየም ከደጋፊው ጋር በማክበር ላይ ነው።

ባየር ሊቨርኩሰን ሁለቱንም ውድድሮች ምንም ጨዋታ ሳይሸነፍ በማሳካት ደማቅ ታሪክ መፃፉ አይዘነጋም።

በጎል ቻናላችን በቪዲዮ መመልከት ይችላሉ።

የጎል ቻናላችን 👉 https://www.tg-me.com/+rbdEU4UaEdQxYWFk

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
2024/10/04 17:14:56
Back to Top
HTML Embed Code: