Telegram Web Link
በርካታ የጣልያን ክለቦች በአውሮፓ መድረክ ይሳተፋሉ !

በሚቀጥለው የውድድር አመት የአውሮፓ እግርኳስ ማህበር በሚያዘጋጃቸው ውድድሮች ላይ ዘጠኝ የጣልያን ሴርያ ክለቦች ተሳታፊ እንደሚሆኑ ተገልጿል።

በሴርያው የሻምፒየንስ ሊግ ቦታን የያዘው አታላንታ የዩሮፓ ሊግ ዋንጫ ማሸነፉን ተከትሎ አንድ ተጨማሪ የሴርያ ክለብ በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ እንደሚሳተፍ ተነግሯል።

ይህንንም ተከትሎ በሚቀጥለው የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ውድድር #ስድስት የጣልያን ሴርያ ክለቦች ተሳታፊ የሚሆኑ ይሆናል።

በወቅታዊ ደረጃ በአውሮፓ መድረክ እነማን ሊሳተፉ ይችላሉ ?

- ሻምፒየንስ ሊግ :- ኢንተር ሚላን ፣ ኤሲ ሚላን ፣ ቦሎኛ ፣ ጁቬንቱስ ፣ አታላንታ እና ሮማ

- ዩሮፓ ሊግ :- ላዝዮ እና ፊዮሬንቲና

- ኮንፈረንስ ሊግ :- ቶሪኖ ( ባለበት ደረጃ ካጠናቀቀ )

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
ፓርቴ በአርሰናል መቀጠል እንደሚፈልግ ገለጸ ! ጋናዊው የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል የመሐል ሜዳ ተጨዋች ቶማስ ፓርቴ በአርሰናል ቤት መጫወት መቀጠል እንደሚፈልግ ተናግሯል። " ስለእኔ የወደፊት ቆይታ ብዙ እንደሚባል አውቃለሁ ነገርግን እኔ እዚህ በመሆኔ ደስተኛ ነኝ ፣ አርሰናልን እወደዋለሁ እዚህ መጫወት መቀጠል እፈልጋለሁ።"ሲል ቶማስ ፓርቴ ተናግሯል። @tikvahethsport     @kidusyoftahe
ቶማስ ፓርቴ ከአርሰናል ጋር ሊለያይ ነው !

ጋናዊው የመሐል ሜዳ ተጨዋች ቶማስ ፓርቴ ከሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል ጋር ሊለያይ እንደሆነ ተገልጿል።

ተጨዋቹ በቅርቡ በሰጠው አስተያየት በአርሰናል ቤት ደስተኛ እንደሆነ እና በክለቡ መጫወት መቀጠል እንደሚፈልግ ተናግሮ ነበር።

መድፈኞቹ አዲስ የመሐል ሜዳ ተጨዋች ለማስፈረም የተለያዩ አማራጮችን መመልከታቸው የተገለፀ ሲሆን በቀጣይ እንቅስቃሴ እንደሚጀምሩ ተዘግቧል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
አሰልጣኝ ኬራን ማክኬና ወዴት ሊያመሩ ይችላሉ ? ከአሰልጣኝ ሮቤርቶ ዲዘርቢ ጋር የተለያየው ብራይተን ኢፕስዊች ታውንን ወደ እንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ ማሳደግ የቻሉትን አሰልጣኝ ኬራን ማክኬናን ለመሾም ጥያቄ ማቅረባቸው ተገልጿል። በቼልሲ አሰልጣኝ ዝርዝር ውስጥ የሚገኙት አሰልጣኝ ኬራን ማክኬና አሁን ላይ የሰማያዊዎቹን የመጨረሻ ውሳኔ መጠበቅ እንደሚፈልጉ ተነግሯል። አሰልጣኙ በተጨማሪም ከኢፕስዊች…
ዩናይትድ አሰልጣኝ ኬራን ማክኬናን አነጋገሩ !

ማንችስተር ዩናይትዶች የኢፕስዊች ታውኑን አሰልጣኝ ኬራን ማክኬናን ተወካዮች አግኝተው ማነጋገራቸው ተገልጿል።

ማንችስተር ዩናይትድ ከነገው የኤፌ ካፕ ፍፃሜ በኋላ ከአሰልጣኝ ኤሪክ ቴንሀግ ጋር የሚለያዩ ከሆነ አሰልጣኝ ኬራን ማክኬናን በተተኪነት ለመሾም ማነጋገራቸው ተገልጿል።

አሰልጣኝ ኬራን ማክኬና በተጨማሪም ከአሰልጣኞቻቸው ጋር በተለያዩት በብራይተን እና ቼልሲ እየተፈለጉ እንደሚገኙ ይታወቃል።

አሰልጣኙ ከዚህ በፊት በማንችስተር ዩናይትድ ቤት በምክትል አሰልጣኝነት ማገልገላቸው አይዘነጋም።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ብሩኖ ፈርናንዴዝ ለደጋፊው ጥሪ አቀረበ !

የማንችስተር ዩናይትዱ አምበል ብሩኖ ፈርናንዴዝ በመላው አለም የሚገኙ የክለቡ ደጋፊዎች በነገው የኤፌ ካፕ የፍፃሜ ጨዋታ ከቡድኑ ጎን እንዲቆሙ ጠይቋል።

በመላው አለም ለምትገኙ የማንችስተር ዩናይትድ ደጋፊዎች ከፍፃሜው በፊት ልናገራቸው የምፈልጋቸው ቃላቶች አሉኝ በማለት ንግግሩን የጀመረው ብሩኖ ፈርናንዴዝ " ለእናንተ ቀላል አመት እንዳልነበረ አውቃለሁ።

የሚገባችሁ ደረጃ ላይ አልደረስንም ፣ ያደረጋችሁልንን ድጋፍ እንደ አምበል ከማንም በላይ ይሰማኛል ፣ ነገርግን አሁን ወደ ዌምብሌይ እናመራለን ለአንድ የመጨረሻ ጊዜ ከጎናችን ቁሙ።"ሲል ጠይቋል።

" በኦልድትራፎርድ ስታዲየም መጫወት በአለም ላይ ካለ ከየትኛውም ቦታ ጋር አወዳድሬ አላውቅም ማንችስተር ዩናይትድን መልቀቅ አልፈልግም ሁልጊዜም ብቸኛ ህልሜ ነው።" ፈርናንዴዝ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
የሴርያ የአመቱ ምርጥ አሰልጣኝ ታውቋል !

በኢንተር ሚላን አሸናፊነት የተጠናቀቀው የጣሊያን ሴርያ የ2023/24 የውድድር ዘመን የአመቱ ምርጥ አሰልጣኝ ይፋ ተደርጓል።

በዚህ መሰረት ከኢንተር ሚላን ጋር የሊጉን ዋንጫ ማሳካት የቻሉት አሰልጣኝ ሲሞን ኢንዛጊ የጣልያን ሴርያ የአመቱ ምርጥ አሰልጣኝ በመሆን መመረጥ ችለዋል።

አሰልጣኝ ሲሞን ኢንዛጊ ኢንተር ሚላንን እየመሩ እስካሁን ካደረጓቸው ሰላሳ ሰባት ጨዋታዎች ሀያ ዘጠኙን ሲያሸንፉ በስድስቱ አቻ ተለያይተው በሁለቱ ተሸንፈዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
ማድሪድ ተጨዋቹ ለፍፃሜ ላይደርስ ይችላል ! ለዘንድሮው የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ፍፃሜ ጨዋታ ማለፋቸውን ያረጋገጡት ሎስ ብላንኮዎቹ ወሳኝ ተጨዋቻቸው ለፍፃሜ መድረሱ አጠራጣሪ መሆኑ ተገልጿል። ፈረንሳዊው የመሐል ሜዳ ተጨዋች ኦርሊየን ቹዋሜኒ በትላንት ምሽቱ የባየር ሙኒክ ጨዋታ ያጋጠመው ጉዳት ከሀያ ሶስት ቀናት በኋላ ለሚደረገው የፍፃሜ ጨዋታ መድረሱን አጠራጣሪ እንዳደረገው ተነግሯል። ሎስ ብላንኮዎቹ…
ማድሪድ ተጨዋቹ ከሻምፒየንስ ሊግ ፍፃሜ ውጪ ሆነ !

የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ፍፃሜ ተፋላሚው ሪያል ማድሪድ ወሳኝ የመሐል ሜዳ ተጨዋቹ በጉዳት ምክንያት ለፍፃሜው እንደማይደርስ ተረጋግጧል።

ፈረንሳዊው የመሐል ሜዳ ተጨዋች ኦርሊየን ቹዋሜኒ ቀጣይ ሳምንት ለሚደረገው የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ፍፃሜ ጨዋታ እንደማይደርስ አሰልጣኝ ካርሎ አንቾሎቲ አረጋግጠዋል።

ሪያል ማድሪድ ከቦርስያ ዶርትመንድ ጋር የሚያደርጉት የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ፍፃሜ ጨዋታ ቀጣይ ሳምንት ቅዳሜ ግንቦት 24/2016 ዓ.ም በዌምብሌይ ስታዲየም ይደረጋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
#Tecno #Camon30Pro5G

ቴክኖ ሞባይል በአይነቱ የተራቀቀውን አዲሱን Tecno Camon 30 pro 5G ምርጫዎ ያድርጉ ሲል ይጋብዛል!

#Camon30Et #Camon30pro5GEt #Camon30 #Camon30Pro5G #TecnoEt
Forwarded from WANAW SPORT
📢 #ለቸኮሉ መፍትሔ ከ #ዋናው!

👉🏾#ዋናው ስፖርትን ለስፖርት አልባሳት ፈጣን አቅርቦት ችግርዎ ሁነኛ መፍትሔን እናስታውስዎ፣ አስቀድመው የተዘጋጁ ማልያዎች!

👉🏾 እርስዎ ብቻ አስቀድመን ካዘጋጀናቸው ዲዛይኖች የፈለጉትን በመምረጥ ትጥቅዎን ይውሰዱ!

🚀 ዛሬውኑ #ይምጡ፣ ቀላል አማራጩን ይጠቀሙ!

📍አድራሻችን:- ገርጂ መብራት ሃይል የካቲት ወረቀት ፊትለፊት፣ አለም ገብሬ ህንፃ፣ 2ተኛ ፎቅ።

📌 ለበለጠ መረጃና ትዕዛዝ 📲 0901138283፣ 0910851535 እና 0913586742 ላይ ይደውሉ።

👉🏾 እንዲሁም በቴሌግራም @Wanawsales ላይ የሽያጭ ሰራተኞቻችንን በቀጥታ በማናገር ወይም በቴሌግራም ቦት @WANAWSbot በኩል ይዘዙን።

Instagram | Facebook | TikTok

🏅 ዋናው ወደፊት...

@wanawsportwear
TIKVAH-SPORT
የአሰልጣኝ ዣቪ የባርሴሎና ቆይታ ? ስፔናዊው የካታላኑ ክለብ ባርሴሎና ዋና አሰልጣኝ ዣቪ ከክለቡ ሊሰናበቱ እንደሚችሉ የሀገሪቱ መገናኛ ብዙሃን በመዘገብ ላይ ናቸው። አሰልጣኝ ዣቪ ከቀናት በፊት ከጋዜጠኞች ጋር በነበራቸው ቆይታ የሰጡት አስተያየት ከባርሴሎናው ፕሬዝዳንት ሁዋን ላፖርታ ጋር አለመግባባት ውስጥ ሳይከታቸው እንዳልቀረ ተዘግቧል። ዣቪ ከቀናት በፊት ቡድናቸው ከሌሎች ክለቦች ጋር ለመፎካከር…
ባርሴሎና አሰልጣኝ ዣቪን አሰናበተ !

የካታላኑ ክለብ ባርሴሎና ስፔናዊውን አሰልጣኝ ዣቪ ሀርናንዴዝ በዛሬው ዕለት ከሀላፊነታቸው ማሰናበቱን ይፋ አድርጓል።

የባርሴሎናው ፕሬዝዳንት ሁዋን ላፖርታ በዛሬው እለት ከአሰልጣኝ ዣቪ ሀርናንዴዝ ጋር እንደተነጋገሩ እና ውሳኔውን እንዳሳወቁ ተዘግቧል።

አሰልጣኝ ዣቪ ከወራት በፊት በአመቱ መጨረሻ ባርሴሎናን እንደሚለቁ አሳውቀው የነበረ ቢሆንም በቅርቡ ክለቡ ሀሳባቸውን አስቀይሯቸው ለመቆየት ወስነው እንደነበር አይዘነጋም።

በቀጣይ ጀርመናዊው አሰልጣኝ ሀንሲ ፊሊክ ባርሴሎናን በሀላፊነት ይረከባሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ተነግሯል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
ባርሴሎና አሰልጣኝ ዣቪን አሰናበተ ! የካታላኑ ክለብ ባርሴሎና ስፔናዊውን አሰልጣኝ ዣቪ ሀርናንዴዝ በዛሬው ዕለት ከሀላፊነታቸው ማሰናበቱን ይፋ አድርጓል። የባርሴሎናው ፕሬዝዳንት ሁዋን ላፖርታ በዛሬው እለት ከአሰልጣኝ ዣቪ ሀርናንዴዝ ጋር እንደተነጋገሩ እና ውሳኔውን እንዳሳወቁ ተዘግቧል። አሰልጣኝ ዣቪ ከወራት በፊት በአመቱ መጨረሻ ባርሴሎናን እንደሚለቁ አሳውቀው የነበረ ቢሆንም በቅርቡ ክለቡ…
ዣቪ እሁድ የመጨረሻ ጨዋታቸውን ይመራሉ !

ስፔናዊው የካታላኑ ክለብ ባርሴሎና አሰልጣኝ ዣቪ በሚቀጥለው የውድድር አመት ከክለቡ ጋር እንደማይቀጥሉ በዛሬው ዕለት ይፋ ተደርጓል።

አሰልጣኝ ዣቪ ሀርናንዴዝ የባርሴሎና የመጨረሻ ጨዋታቸውን እሁድ ከሲቪያ ጋር በሚደረግ መርሐ ግብር እንደሚመሩ ተገልጿል።

ዣቪ ሀርናንዴዝ ባርሴሎናን በአሰልጣኝነት እየመሩ ባለፈው አመት የላሊጋውን ዋንጫ ማሳካት ችለዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
የዩናይትድ እና ሲቲን ጨዋታ ማን ይመራዋል ?

ማንችስተር ዩናይትድ ከ ማንችስተር ሲቲ ጋር በነገው ዕለት የሚያደርጉትን የእንግሊዝ ኤፌ ካፕ ፍፃሜ ጨዋታ የሚመሩት ዳኛ ታውቀዋል።

ዌምብሌይ ስታዲየም የሚደረገውን ተጠባቂ የማንቹንያን ደርቢ የኤፌ ካፕ ፍፃሜ ጨዋታ አንዲ ማድሌይ በመሐል ዳኝነት እንደሚመሩት ይፋ ተደርጓል።

ጨዋታውን ማይክል ኦሊቨር በቫር ዳኝነት እንደሚመሩት ተገልጿል።

ጨዋታውን ማን ያሸንፋል ?

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
" ወደዚህ የመጣሁት ዋንጫ ለማሸነፍ ነው " ቴንሀግ የማንችስተር ዩናይትድ ዋና አሰልጣኝ ኤሪክ ቴንሀግ ቡድናቸው ቅዳሜ ከማንችስተር ሲቲ ጋር ከሚያደርገው የኤፌ ካፕ ፍፃሜ ጨዋታ በፊት አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። አሰልጣኝ ኤሪክ ቴንሀግ ምን አሉ ? - " ወደዚህ የመጣሁት ዋንጫ ለማሸነፍ ነው ቅዳሜ ደግሞ የምናሸንፍበት እድል አለን እንደ ቡድን ለፍፃሜ መድረስ ይገባናል ዋንጫውን ማሸነፍ እንፈልጋለን።…
" የነገው ጨዋታ ከሊጉ የተለየ ነው " ጋርዲዮላ

የማንችስተር ሲቲው ዋና አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ ቡድናቸው ነገ ከማንችስተር ዩናይትድ ጋር ከሚያደርገው የኤፌ ካፕ ፍፃሜ ጨዋታ በፊት ከጋዜጠኞች ጋር ቆይታ አድርገዋል።

አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ ምን አሉ ?

" በፕርሚየር ሊጉ ከማንችስተር ዩናይትድ የተሻልን ነበርን ቀጣይነት ያለው አቋምም አሳይተናል የነገው ጨዋታ ግን የተለየ ነው የሚሆነው አንድ ጨዋታ ነው ዩናይትድ ያው ዩናይትድ ነው።

- ማንችስተር ዩናይትድ አሁን ላይ ያላቸው የቡድን ስብስብ ጥሩ እና የተለየ ነው።

- ባለፉት አስር አመታት ማንችስተር ሲቲ የተሻለ ክለብ ነበር ነገርግን በታሪክ ደረጃ ማንችስተር ዩናይትድ የእንግሊዝ ምርጡ ክለብ ነው ለእነሱ ትልቅ ክብር አለን።

- ኤሪክ ቴንሀግ ማንችስተር ዩናይትድ ውስጥ ለሰራው ነገር ክብር አለኝ ፣ ብዙ ጉዳቶች ነበሩበት ጥሩ ተጨዋቾች ቢኖሩትም ከተጎዱ መጠቀም አይችልም።

- አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ በቆይታቸው ወቅት ማንችስተር ሲቲ በጨዋታው ከኤደርሰን ውጪ ሁሉም ተጨዋቾቹ ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
ዣቪ እሁድ የመጨረሻ ጨዋታቸውን ይመራሉ ! ስፔናዊው የካታላኑ ክለብ ባርሴሎና አሰልጣኝ ዣቪ በሚቀጥለው የውድድር አመት ከክለቡ ጋር እንደማይቀጥሉ በዛሬው ዕለት ይፋ ተደርጓል። አሰልጣኝ ዣቪ ሀርናንዴዝ የባርሴሎና የመጨረሻ ጨዋታቸውን እሁድ ከሲቪያ ጋር በሚደረግ መርሐ ግብር እንደሚመሩ ተገልጿል። ዣቪ ሀርናንዴዝ ባርሴሎናን በአሰልጣኝነት እየመሩ ባለፈው አመት የላሊጋውን ዋንጫ ማሳካት ችለዋል። …
ባርሴሎና አዲስ አሰልጣኝ ሊሾም ነው !

ከአሰልጣኝ ዣቪ ሀርናንዴዝ ጋር እንደሚለያይ ያሳወቀው የካታላኑ ክለብ ባርሴሎና በምትካቸውም አዲስ አሰልጣኝ ለመሾም ከስምምነት መድረሱ ተገልጿል።

ባርሴሎና የቀድሞውን የጀርመን ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ሀንሲ ፍሊክ በሀላፊነት ለመሾም መቃረባቸው ተገልጿል።

አሰልጣኝ ሀንሲ ፍሊክ ባርሴሎናን ለሁለት የውድድር አመታት ለማሰልጠን ፊርማቸውን እንደሚያኖሩ ተዘግቧል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
ዩናይትድ አሰልጣኝ ኬራን ማክኬናን አነጋገሩ ! ማንችስተር ዩናይትዶች የኢፕስዊች ታውኑን አሰልጣኝ ኬራን ማክኬናን ተወካዮች አግኝተው ማነጋገራቸው ተገልጿል። ማንችስተር ዩናይትድ ከነገው የኤፌ ካፕ ፍፃሜ በኋላ ከአሰልጣኝ ኤሪክ ቴንሀግ ጋር የሚለያዩ ከሆነ አሰልጣኝ ኬራን ማክኬናን በተተኪነት ለመሾም ማነጋገራቸው ተገልጿል። አሰልጣኝ ኬራን ማክኬና በተጨማሪም ከአሰልጣኞቻቸው ጋር በተለያዩት በብራይተን…
ኤሪክ ቴንሀግ ከዩናይትድ ጋር ሊለያዩ ይችላሉ !

ማንችስተር ዩናይትድ ከነገው የእንግሊዝ ኤፌ ካፕ ፍፃሜ ጨዋታ በኋላ አሰልጣኝ ኤሪክ ቴንሀግን ከሀላፊነት ለማሰናበት ከውሳኔ መድረሳቸው እየተገለፀ ይገኛል።

ማንችስተር ዩናይትድ የነገውን የፍፃሜ ጨዋታ ማሸነፍ ቢችሉም አሰልጣኝ ኤሪክ ቴንሀግን ከመሰናበት እንደማያድናቸው በመዘገብ ላይ ነው።

ቀያዮቹ ሴጣኖች ለመሾም በዝርዝራቸው ውስጥ የያዟቸው አሰልጣኞች ኬራን ማክኬና ፣ ቱሄል ፣ ፖቼቲኖ ፣ ቶማስ ፍራንክ እና ግራም ፖተር እንደሚገኙበት ተገልጿል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
መቻል ከሻሸመኔ ከተማ ነጥብ ተጋራ !

በኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ የሀያ ስድስተኛ ሳምንት መርሐ ግብር መቻል ከሻሸመኔ ከተማ ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 2ለ2 በሆነ አቻ ውጤት አጠናቀዋል።

የመቻልን ግቦች በረከት ደስታ እና ምንይሉ ወንድሙ ከመረብ ሲያሳርፉ ለሻሸመኔ ከተማ አብዱልቃድር ናስር እና ሙሉጌታ ወልደ ጊዮርጊስ አስቆጥረዋል።

መቻል ነጥብ መጣሉን ተከትሎ ከሊጉ መሪ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ያለውን የነጥብ ልዩነት ማጥበብ የሚችልበትን እድል ሳይጠቀም ቀርቷል።

የሊግ ደረጃቸው ምን ይመስላል ?

2️⃣ መቻል :- 51 ነጥብ

1️⃣5️⃣ ሻሸመኔ ከተማ :- 14 ነጥብ

ቀጣይ ጨዋታ ምን ይመስላል ?

አርብ - ፋሲል ከነማ ከ መቻል

እሁድ - ሻሸመኔ ከተማ ከ ኢትዮጵያ መድን

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
🏆የዋንጫውን አሸናፊ ይገምቱ🏆

🔥 ማንቼስተሮቹ ለዚህ ዓመት ለመጨረሻ ጊዜ ለኤፍ ኤ ካፕ ዋንጫ ፍፃሜ ይገናኛሉ!

ቅዳሜ ፣ ግንቦት 17 ከሰዓት 11 ሰዓት ማን ሲቲ ከ ማን ዩናይትድ ጋር በዌንብሊ ለዋንጫው ይፋለማሉ!

የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫንያሸነፈው ማን ሲቲ ሁለተኛ ዋንጫውን ያሸንፋል?

👉 ይህንን ደማቅ ፍልሚያ በSS Football 225 በጎጆ ፓኬጅ እና በSS Football 222 በሜዳ ለመከታተል ዛሬውኑ ደንበኝነትዎን ያራዝሙ           

የዲኤስቲቪ አገልግሎቶችን ለማግኘት ከታች ያለውን የMyDStv Telegram bot ሊንክ ይጫኑ!
👇
https://mydstv.onelink.me/vGln/eth2

#PremierLeagueOnDStv #ሁሉምያለውእኛጋርነው #DStvEthiopia #DStvSelfServiceET
ሽመልስ በቀለ 1⃣8⃣ ገስት ሀውስ

በውቢቷ ሀዋሳ ቆይታዎ የት ለማረፍ አስበዋል ? ንፁህ እና በደንበኞቻችን ተወዳጅ በሆነው የእንግዳ ማረፊያችን መጥተው የእረፍት ጊዜውን ያሳልፉ።

እንግዶቻችንን ተቀበልን ለእይታ ሳቢ በሆነው የእንግዳ ማረፊያችን ማስተናገድ ከጀመርን አመታትን አስቆጥረናል።

አድራሻችን :- ሀዋሳ አርቴፍሻል ስታዲየም መንገድ ላይ ያገኙናል።

ለተጨማሪ መረጃ እና ለትዕዛዝዎ ይደውሉልን :- 0928684848

#ShemelesBekele18
ኢኳቶሪያል ጊኒ በፊፋ ቅጣት ተጣለባት !

የኢኳቶሪያል ጊኒ ብሔራዊ ቡድን በመጀመሪያ ሁለት የአለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታዎች ብሔራዊ ቡድኑን ለመወከል ብቁ ያልሆነውን ኤምሊዮ ኑስ በማሰለፉ ምክንያት በፊፋ ቅጣት እንደተጣለበት ተገልጿል።

ፊፋ ኢኳቶሪያል ጊኒ በመጀመሪያ እና ሁለተኛ የምድብ የአለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታዎች ያስመዘገበቻቸውን ድሎች ለተቃራኒ ቡድን በፎርፌ እንዲሰጡ መወሰኑን አሳውቋል።

የ 2023 አፍሪካ ዋንጫ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ኤምሊዮ ኑስ በበኩሉ ለስድስት ወራት ከኢንተርናሽናል እግርኳስ መታገዱ ተገልጿል።

ስፔን ውስጥ የተወለደው ኤምሊዮ ኑስ ለኢኳቶሪያል ጊኒ ብሔራዊ ቡድን አርባ ሶስት ጨዋታዎች አድርጎ ሀያ ሶስት ግቦችን በማስቆጠር የምንግዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ነው።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
የሴርያ የአመቱ ምርጦች እነማን ይሆናሉ ? በኢንተር ሚላን አሸናፊነት የተጠናቀቀው የጣልያን ሴርያ የዘንድሮው የ2023/24 የውድድር አመት በየዘርፉ የአመቱ ምርጥ እጩዎች ይፋ ተደርገዋል። በዚህም መሰረት :- - የአመቱ ምርጥ አጥቂ እጩዎች :- ፓብሎ ዲባላ ፣ ራፋኤል ሊያኦ እና ቭላሆቪች - የአመቱ ምርጥ አማካይ :- ካልሀኖግሉ ፣ ኮፕሜነርስ እና ክርስቲያን ፑልሲች - የአመቱ ምርጥ ተከላካይ…
የጣልያን ሴርያ የአመቱ ምርጦች ታውቀዋል !

በኢንተር ሚላን አሸናፊነት የተጠናቀቀው የጣልያን ሴርያ የዘንድሮው የ2023/24 የውድድር አመት በየዘርፉ የአመቱ ምርጥ ተጨዋቾች ይፋ ተደርገዋል።

በዚህም መሰረት የአመቱ ምርጥ የፊት መስመር አጥቂ በመሆን የጁቬንቱሱ ተጨዋች ዱሳን ቭላሆቪች በአብላጫ ድምፅ መመረጥ ችሏል።

እንዲሁም የአመቱ ምርጥ አማካይ በመሆን የኢንተር ሚላኑ ሀካን ካልሀኖግሉ ተመርጧል።

በተጨማሪም የአመቱ ምርጥ ተከላካይ በመሆን የኢንተር ሚላኑ አሌሳንድሮ ባስቶኒ ምርጥ ግብ ጠባቂ የሞንዛው ሚሼል ዲ ግሪጎርዮ ተመርጠዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
2024/10/05 01:20:47
Back to Top
HTML Embed Code: