Telegram Web Link
" ክሎፕ እንግሊዝን ከተረከበ ካቆምንበት እንቀጥላለን " አርኖልድ

የሊቨርፑሉ የመስመር ተጨዋች አሌክሳንደር አርኖልድ አሰልጣኝ የርገን ክሎፕ ስማቸው እየተያያዘ የሚገኘውን የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን ከተረከቡ እንደሚደሰት ተናግሯል።

" ከክሎፕ ጋር በሰራሁበት ጊዜ በጣም ደስተኛ ነበርኩ ፣ ከእሱ ጋር ጥሩ ትዝታዎችን አሳልፈናል ሁልጊዜ ጥሩ ግንኙነት ነበረን እንግሊዝን ከተረከበ ካቆምንበት እንቀጥላለን።" ሲል አርኖልድ ተናግሯል።

የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን ከአሰልጣኝ ጋሪዝ ሳውዝጌት ጋር ከተለያየ በኋላ አዲስ አሰልጣኝ በሀላፊነት ለመሾም እያፈላለገ ይገኛል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
" አምራባት በዩናይትድ መቆየት ይፈልጋል " ሞሮኳዊው የመሐል ሜዳ ተጨዋች ሶፍያን አምራባት በቀጣይ በማንችስተር ዩናይትድ ቤት መቆየት እንደሚፈልግ የፊዮሬንቲና ዳይሬክተር ፕሬድ ገልጸዋል። ዳይሬክተሩ በንግግራቸውም " ሶፍያን አምራባት ፕርሚየር ሊግ ውስጥ መቆየት ይፈልጋል ማንችስተር ዩናይትድ ምንም ነገር አልነገሩንም ከፊዮሬንቲና ጋር እንዲቆይ እንፈልጋለን ነገርግን እሱ ሌላ አቅም ያለው ይመስለኛል።"ብለዋል።…
የሶፍያን አምራባት የማንችስተር ዩናይትድ ቆይታ ?

ማንችስተር ዩናይትድ ሞሮኳዊውን የመሐል ሜዳ ተጨዋች ሶፍያን አምራባት ለማስፈረም በውሰት ውሉ የተቀመጠውን የመግዛት አማራጭ እንደማይጠቀሙ ተገልጿል።

በተጨዋቹ የውስት ውል ውስጥ በ20 ሚልዮን ዩሮ የመግዛት አማራጭ የተካተተ ሲሆን ቀያዮቹ ሴጣኖች መክፈል እንደማይፈልጉ ለፊዮረንቲና ማሳወቃቸው ተገልጿል።

ማንችስተር ዩናይትድ ተጫዋቹን ማቆየት እንደሚፈልግ ሲገለፅ በቀጣይ በሌላ የዝውውር ሂደት የማቆየት ፍላጎት እንዳላቸው ተዘግቧል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
አርሰናል ወደ አሜሪካ የሚጓዘውን ስብስብ አሳውቋል !

የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል ለቅድመ ውድድር ዝግጅት ወደ አሜሪካ የሚያመራውን የተጨዋቾች ስብስብ ይፋ አድርገዋል።

በስብስቡ ውስጥ ታኬሂሮ ቶሚያሱ እና ኬራን ቴርኒ በጉዳት ምክንያት አለመካተታቸውን ክለቡ አሳውቋል።

መድፈኞቹ በአሜሪካ ቆይታቸው ከበርንማውዝ ፣ማንችስተር ዩናይትድ እና ሊቨርፑል ጋር በተከታታይ የወዳጅነት ጨዋታዎች ያደርጋል።

*የተጨዋቾች ዝርዝር ከላይ በምስሉ ተያይዟል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
" ማሬስካ በጣም ጥሩ ሀሳብ ይዞ መጥቷል " ንኩንኩ

የምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ የፊት መስመር ተጨዋች ክርስቶፈር ንኩንኩ አዲሱ አሰልጣኝ ኢንዞ ማሬስካ ወደ ቡድኑ አዲስ ሀሳብ ይዘው መምጣታቸውን ገልፀዋል።

" አሰልጣኝ ኢንዞ ማሬስካ ወደ ቡድኑ በጣም ጥሩ የሆነ የጨዋታ ሀሳብ ይዘው መጥተዋል " የሚለው ክርስቶፈር ንኩንኩ በአሁን ሰዓት ሁላችንም በመማር ላይ ነን ብሏል።

ክርስቶፈር ንኩንኩ ቀጥሎም ሁሉም ተጨዋቾች የአዲሱን አሰልጣኝ ኢንዞ ማሬስካ ሀሳብ የሚከተሉ ከሆነ በቀጣዩ አመት የሚያምር እግርኳስ እንደምንጫወት እርግጠኛ ነኝ በማለት ተናግሯል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
ቢኒያም ግርማይ ለሶስተኛ ጊዜ አሸናፊ ሆነ ! ኤርትራዊው ብስክሌተኛ ቢኒያም ግርማይ በታላቁ የቱር ደ ፍራንስ ውድድር በአስራ ሁለተኛው ቀን ውድድር ቀድሞ በመግባት ለሶስተኛ ጊዜ የውድድሩ አሸናፊ መሆን ችሏል። በመጨረሻዎቹ መቶ ሜትሮች የነበረውን ከባድ ፉክክር መርታት የቻለው ቢኒያም ግርማይ በቱር ደ ፍራንስ በርካታ ነጥብ በመሰብሰብ አረንጓዴ ማሊያውን ( Green Jersey ) አስጠብቋል። ቢኒያም…
ቢኒያም ግርማይ ወርቃማ ታሪክ ፃፈ !

ኤርትራዊው ብስክሌተኛ ቢኒያም ግርማይ የታላቁን የቱር ደ ፍራንስ ውድድር " Points Classification " አሸናፊ ሆኖ በማጠናቀቅ ወርቃማ ታሪክ መፃፍ ችሏል።

ቢኒያም ግርማይ የቱር ደ ፍራንስ ውድድር አረንጓዴ ማሊያ ( Green Jersey ) ያሸነፈ የመጀመሪያው አፍሪካዊ በመሆን አዲስ ታሪክ ፅፏል።

ቢኒያም ግርማይ በ2024 ቱር ደ ፍራንስ ውድድር የ3ኛ ፣ 8ኛ እና 12ተኛ ደረጃ ውድድሮችን በማሸነፍ የመጀመሪያው ጥቁር አፍሪካዊ መሆን ችሏል።

ቢኒያም ግርማይ አረንጓዴ ማልያውን ካረጋገጠበት ከዛሬው የመጨረሻ ውድድር በኋላ በሰጠው አስተያየት “ ምን ልል እችላለሁ ? በቃ የህይወቴ ምርጡ ቀን ነው “ ሲል ተደምጧል።

“ ወደዚህ የመጣሁት መጥፎ ብስክሌተኛ እንዳልሆንኩ ብቻ ለማሳየት እንጂ ይህንን ድል አልሜ አልነበረም የሚደነቅ ነው “።ሲል ቢኒያም ግርማይ ተናግሯል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ማድሪድ ለዴቪስ ስንት መክፈል ይፈልጋል ?

ሪያል ማድሪድ ካናዳዊውን የባየር ሙኒክ የመስመር ተጨዋች አልፎንሶ ዴቪስ ለማስፈረም ከተጨዋቹ ጋር በግል ስምምነት እንዳላቸው ሲገለፅ ነበር።

ሎስ ብላንኮዎቹ አልፎንሶ ዴቪስን በዚህ ክረምት የሚያስፈርሙ ከሆነ ከ25 ሚልዮን ዩሮ በላይ መክፈል እንደማይፈልጉ ተገልጿል።

ሪያል ማድሪድ ባየር ሙኒክ 25 ሚልዮን ዩሮ የማይቀበል ከሆነ በሚቀጥለው አመት ውሉ ሲጠናቀቅ በነፃ ማስፈረም እንደሚመርጡ ተነግሯል።

ባየር ሙኒክ በበኩሉ የተጫዋቹን ውል ማራዘም እንደሚፈልጉ ተዘግቧል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
መልካም ዕድል!
ከፍ የተደረጉ ኦዶችን አይተዋል ? እንግዲያውስ ተወራረዱባቸው!
Lyngby - FC Copenhagen
GAIS - AIK
ለተሻለ ውርርድ ቤቲካን ይጠቀሙ! አሁኑኑ Betika.et ላይ /በቴሌግራም ቦታችን - @BetikaETBot ይወራረዱ!
Forwarded from HEY Online Market
•Macbook PRO 512GB/18GB
M3 Pro Chip 275,000 Birr

•Macbook PRO 512/8GB
M3 Chip 185,000 Birr

Contact Us
0953964175 @heymobile
@heyonlinemarket
ሀሜስ ሮድሪጌዝ ክለቡን ሊለቅ ነው !

የኮፓ አሜሪካ የውድድሩ ምርጥ ተጨዋች የነበረው ኮሎምቢያዊው አማካይ ሀሜስ ሮድሪጌዝ ከብራዚሉ ክለብ ሳኦ ፓውሎ ጋር ለመለያየት መወሰኑ ተገልጿል።

በኮፓ አሜሪካው ሀገሩ ለፍፃሜ ስትደርስ ድንቅ ጊዜን ማሳለፍ የቻለው ሀሜስ ሮድሪጌዝ በቀጣይ ወደ አውሮፓ መመለስ እንደሚፈልግ ተነግሯል።

የ 33ዓመቱ የመሐል ሜዳ ተጨዋች ሀሜስ ሮድሪጌዝ በቀጣይ በነፃ ዝውውር ወደ ሌላ ክለብ ሲያመራ ፖርቶ ተጫዋቹን ለማስፈረም ፈላጊ መሆናቸው ተዘግቧል።

ሀሜስ በኮፓ አሜሪካ ካደረጋቸው አምስት ጨዋታዎች በአራቱ የጨዋታው ኮከብ ተብሎ ሲመረጥ በአንድ የኮፓ አሜሪካ ስድስት ለግብ የሆኑ ኳሶች አመቻችቶ በማቀበል በሜሲ ተይዞ የነበረውን ሪከርድ መስበሩ አይዘነጋም።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ዩናይትድ ተጨማሪ ተጨዋቾች ያስፈርማል !

ማንችስተር ዩናይትድ የክረምቱ የተጨዋቾች የዝውውር መስኮት ሳይጠናቀቅ ቡድኑን ለማጠናከር ተጨማሪ ዝውውሮችን ለማካሄድ መዘጋጀታቸው ተገልጿል።

ማንችስተር ዩናይትድ ተጨማሪ ዝውውሮችን ለማድረግ ተጨዋቾችን በመሸጥ ገንዘብ ማግኘት እንዳለበት አሰልጣኝ ኤሪክ ቴንሀግ ተናግረዋል።

ክለቡ ውስጥ በአሁን ሰዓት ለመልቀቅ የተቃረበ ተጨዋች ባይኖርም በዚህ ሳምንት ተጨዋቾች ሊሸጡ እንደሚችሉ ተጠቁሟል።

ቀያዮቹ ሴጣኖች እስካሁን ጆሽዋ ዚርኪዜን ከቦሎኛ እንዲሁም ሌኒ ዮሮን ከሊል በማስፈረም ትልቅ ዝውውሮችን መፈፀማቸው ይታወሳል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
" ሳውዲ ከአውሮፓ ጋር ትወዳደራለች ብዬ እጠብቃለሁ " ኦዚል

ጀርመናዊው የቀድሞ የአርሰናል እና ሪያል ማድሪድ አማካይ ሜሱት ኦዚል ሳውዲ አረቢያ በቀጣይ ወጣቶችን ካስፈረመች ተፎካካሪ እንደምትሆን ተናግሯል።

ሜሱት ኦዚል በንግግሩም " ሳውዲ አረቢያ በዚህ አመት የዝውውር መስኮት ወጣቶች ላይ ትኩረት አድርገው የሚያስፈርሙ ከሆነ ከአውሮፓ ጋር ይወዳደራሉ ብዬ እጠብቃለሁ " ሲል ተደምጧል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ሪያል ማድሪድ ለናቾ ይፋዊ ሽኝት ያዘጋጃል !

ሪያል ማድሪድ ከሀያ ሶስት አመታት በኋላ ክለቡን ለለቀቀው ስፔናዊው የተከላካይ ስፍራ ተጨዋች ናቾ ፈርናንዴዝ ይፋዊ ሽኝት እንደሚያዘጋጁ ተገልጿል።

ሎስ ብላንኮዎቹ የፊታችን እሮብ በልምምድ ማዕከላቸው ቫልዴቤባስ ፕሬዝዳንት ፍሎሬንቲኖ ፔሬዝ በተገኙበት ለታሪካዊ ተጨዋቻቸው ናቾ ሽኝት እንደሚያደርጉ ተነግሯል።

ናቾ በሪያል ማድሪድ ቤት ሶስት መቶ ስልሳ አራት ጨዋታዎች ሲያደርግ #ስድስት የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫዎችን ጨምሮ አጠቃላይ ሀያ ስድስት ዋንጫዎች አሳክቷል።

ናች ፈርናንዴዝ ከሪያል ማድሪድ ጋር በመለያየት የሳውዲ አረቢያውን ክለብ አል ቃዲሲያ በይፋ መቀላቀሉ ይታወቃል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
የፓሪስ ኦሎምፒክ ትኬቶች ተሸጠው አልተጠናቀቁም !

ከአራት ቀናት በኃላ የሚጀምረው የ2024ቱ ፓሪስ ኦሎምፒክ ውድድር መመልከቻ መግቢያ ትኬቶች እስካሁን ተሽጠው አለመጠናቀቃቸውን አዘጋጆቹ ገልጸዋል።

ውድድሩ ሊጀመር የቀናት እድሜ ቢቀረውም የ 100ሜትር ፍፃሜ እና የመክፈቻ ዝግጅቱን ጨምሮ በሺዎች የሚቆጠሩ ትኬቶች ተሸጠው አለማጠናቀቃቸው ተገልጿል።

የውድድሩ አዘጋጅ ኮሚቴ አሁን ላይ ከ500,000 እስከ 600,000 የሚደርሱ የመግቢያ ትኬቶች ሳይሸጡ በገበያ ላይ እንደሚገኙ አረጋግጧል።

ይሁን እንጂ አዘጋጆቹ 8.8 ሚሊየን የመግቢያ ትኬቶች አስቀድሞ እንደተሸጠ በመግለፅ የኦሎምፒክ ትልቅ ቁጥር መሆኑን ጠቁመዋል።

አንድ ሚሊየን የመግቢያ ትኬቶች ያልተሸጡበት የ2016ቱ ሪዮ ኦሎምፒክ ከዚህ በፊት በነበሩ የኦሎምፒክ ውድድሮች በርካታ ትኬቶች ያልተሸጡበት ውድድር እንደነበር ተነግሯል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
#Update አርሰናሎች ጣልያናዊውን የተከላካይ ስፍራ ተጨዋች ሪካርዶ ካላፊዮሪ ማስፈረም ከጣልያኑ ክለብ ቦሎኛ ጋር ከስምምነት መድረሳቸው ተገልጿል። መድፈኞቹ ተጫዋቹን 38 ሚልዮን ፓውንድ በሚደርስ የዝውውር ሒሳብ ለማስፈረም ከቦሎኛ ጋር መስማማታቸው ተነግሯል። ተጨዋቹ ከእረፍት በተመለሰ በኋላ ለክለቡ ቦሎኛ ሀላፊዎች አርሰናልን በመቀላቀል ህልሙን እንዲያሳካ እንዲለቁት ጥያቄ ማቅረቡ ተዘግቧል።…
ቦሎኛ ካላፊዮሪን ለልምምድ አልጠራም !

ቦሎኛ ለቅድመ ውድድር ዝግጅት ከእረፍት ወደ ልምምድ የሚመለሱ ተጨዋቾችን ሲያሳውቅ ጣልያናዊው ተከላካይ ሪካርዶ ካላፊዮሪ ሳይካተት ቀርቷል።

ጣልያናዊው ተከላካይ ሪካርዶ ካላፊዮሪ የሰሜን ለንደኑን ክለብ አርሰናል ለመቀላቀል ሙሉ ስምምነት ላይ መድረሳቸው ይታወሳል።

ተጨዋቹ በዚህ ሳምንት የህክምና ምርመራውን አጠናቆ ወደ አርሰናል የሚያደርገውን ዝውውር ያጠናቅቃል ተብሎ ይጠበቃል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
" ያቀድነውን ሳናሳካ እረፍት አይኖረንም " ዳን አሽዎርዝ

አዲሱ የማንችስተር ዩናይትድ ስፖርቲንግ ዳይሬክተር ዳን አሽዎርዝ ለክለቡ ደጋፊዎች ባስተላለፉት መልዕክት " ለክለቡ ስኬት ሳናመጣ እረፍት አይኖረንም " ሲሉ ተናግረዋል።

“ ዩናይትድ አሁንም አንዱ የአለማችን ትልቅ ክለብ ነው " የሚሉት ዳን አሽዎርዝ " ይህ ግን የስኬት መለኪያ አይደለም በሜዳው ላይ ስኬት ማምጣት አለብን " ብለዋል።

" አላማችን ዩናይትድን በድጋሜ በሜዳ ላይ ከአለም ምርጥ ክለቦች አንዱ ማድረግ ነው ፣ በአንድ ቀን የሚመጣ አይደለም በጋር ሆነን አላማችንን ሳናሳካ እረፍት አይኖረንም " ሲሉ ሀላፊው ተናግረዋል።

ዳን አሽዎርዝ አክለውም ክለቡ ከፉልሀም ጋር በሚያደርገው የውድድር ዘመኑ የመጀመሪያ ጨዋታ ከደጋፊው ጋር ለመገናኘት መጓጓታቸውን ገልጸዋል።

አዲሱ የስፖርቲንግ ዳይሬክተር ዳን አሽዎርዝ ወደ ክለቡ ከመጡ በኃላ ሊኒ ዮሮን እና ጆሽዋ ዚርክዜን በዝውውሩ መስኮቱ የመጀመሪያ ሳምንታት ማስፈረማቸው አይዘነጋም።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ሮማ እና ባስል በካላፊዮሪ ዝውውር ለምን ተካሰሱ ?

ሮማ የቦሎኛው ተከላካይ ሪካርዶ ካላፊዮሪ ወደ አርሰናል በሚያደርገው ዝውውር ደስተኛ አለመሆናቸው እና የጥቅም ይገባኛል ጥያቄ ማንሳታቸው ተገልጿል።

ሮማ ተጫዋቹን ከሁለት አመታት በፊት ለባስል በሸጠበት ወቅት ከወደፊት ሽያጭ 40% ክፍያ የማግኘት መብት በውሉ ውስጥ እንዳላቸው ተገልጿል።

በዚህም ምክንያት ባስል ባለፈው አመት ተጫዋቹን ለቦሎኛ በ4 ሚልዮን ዩሮ ሲሸጥ አርባ በመቶውን ለሮማ መክፈላቸው ተነግሯል።

ባስል በበኩሉ ተጫዋቹን ለቦሎኛ ሲሸጥ ከወደፊት ሽያጭ 50% የማግኘት መብት ማካተታቸውን ተከትሎ አርሰናል ከሚከፍለው የዝውውር ሒሳብ ላይ ሀምሳ በመቶ ያገኛሉ።

ሮማ በበኩሉ ባለን ውል መሰረት አሁንም ባስል ከሚያገኘው ሀምሳ በመቶ ክፍያ 40% ይገባኛል በሚል ወደ ክስ ማምራታቸው ተገልጿል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
ቼልሲ ተጨዋች ለማስፈረም ተስማማ ! የምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ አሜሪካዊውን የአትላንታ ዩናይትድ ወጣት የግራ መስመር ተጨዋች ካሌብ ዊሌይ ለማስፈረም ከስምምነት መድረሳቸው ተገልጿል። ሰማያዊዎቹ ተጫዋቹን እስከ 2031 በሚቆይ የሰባት አመት ኮንትራት በ8.5 ሚልዮን ፓውንድ የዝውውር ሒሳብ ለማስፈረም ከስምምነት መድረሳቸው ተዘግቧል። የ 19ዓመቱ የመስመር ተጨዋች ካሌብ ዊሌይ በቀጣይ የውድድር…
ቼልሲ በይፋ ተጨዋች አስፈረመ !

የምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ አሜሪካዊውን ወጣት የግራ መስመር ተጨዋች ካሌብ ዊሌይ ከአትላንታ ዩናይትድ ማስፈረማቸውን ይፋ አድርገዋል።

ሰማያዊዎቹ ተጫዋቹን 8.5 ሚልዮን ዶላር የዝውውር ሒሳብ በማውጣት እስከ 2031 በሚቆይ የሰባት አመት ኮንትራት ማስፈረማቸው ተገልጿል።

የ 19ዓመቱ የመስመር ተጨዋች ካሌብ ዊሌይ በቀጣይ የውድድር አመት በውሰት ወደ ስትራስቡርግ ያመራል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተነግሯል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
አስቶን ቪላ አማዱ ኦናናን ሊያስፈርም ነው ! በአሰልጣኝ ኡናይ ኤምሬ የሚመራው አስቶን ቪላ ቤልጂየማዊውን የመሐል ሜዳ ተጨዋች አማዱ እናና ከኤቨርተን ለማስፈረም መቃረባቸው ተነግሯል። የ 22ዓመቱ የመሐል ሜዳ ተጫዋች አማዱ ኦናና በአስቶን ቪላ ቤት የረጅም ጊዜ ኮንትራት ለመፈረም ከስምምነት መድረሳቸው ተገልጿል። የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ተሳታፊው ክለብ አስቶን ቪላ አማዱ ኦናናን በ50 ሚልዮን…
አስቶን ቪላ አማዱ ኦናናን አስፈረመ !

በአሰልጣኝ ኡናይ ኤምሬ የሚመራው አስቶን ቪላ ቤልጂየማዊውን የመሐል ሜዳ ተጨዋች አማዱ ኦናና ከኤቨርተን ማስፈረማቸውን ይፋ አድርገዋል።

የ 22ዓመቱ የመሐል ሜዳ ተጫዋች አማዱ ኦናና በአስቶን ቪላ ቤት የረጅም ጊዜ ኮንትራት መፈረሙ ተገልጿል።

የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ተሳታፊው ክለብ አስቶን ቪላ አማዱ ኦናናን በ50 ሚልዮን ፓውንድ የዝውውር ሒሳብ ማስፈረማቸው ተገልጿል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
" የዩናይትድ ተጨዋች መሆን ህልሜ ነበር " ሌኒ ዮሮ

ፈረንሳዊው የተከላካይ ስፍራ ተጨዋች ሌኒ ዮሮ የማንችስተር ዩናይትድ ተጨዋች መሆን የልጅነት ህልሙ እንደነበር በሰጠው አስተያየት ተናግሯል።

" የዩናይትድ ተጨዋች መሆን የልጅነት ህልሜ ነበር እዚህ በመሆኔ በጣም ደስተኛ ነኝ " ሲል የሚናገረው ሌኒ ዮሮ ዩናይትድ የአለም ትልቁ ክለብ ነው ለእሱ መጫወት ሁልጊዜም ህልም ነው ብሏል።

" አሰልጣኙ ማሸነፍ ብቻ የሚፈልግ ተጨዋች የሚወድ ሰው ነው እሱ እንደሚፈልገው ለመጫወት እዚህ ነኝ ፣ ለክለቡ ሁሉንም ለማድረግ ዝግጁ ነኝ።" ሌኒ ዮሮ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
Forwarded from WANAW SPORT
🇪🇹 #ዋናው በዩናይትድ ኪንግደም 🇬🇧

📸 ተጨማሪ ምስሎች ከ12ኛው ዓመታዊ የስፖርትና የባህል ፌስቲቫል! 📸

🏅 ዋናው ወደፊት...

@wanawsportwear
2024/10/04 07:28:14
Back to Top
HTML Embed Code: