Telegram Web Link
Forwarded from HEY Online Market
•PlayStation 5, 73,000 Birr
•Playstaion 5 Slim, 78,000 Birr

•PlayStation 4 Slim, 35,000 Birr
•PlayStation 4 Pro, 43,000 Birr

•Playstaion portal, 35,000 Birr
•Meta Quest 2, 55,000 Birr
•Meta Quest 3, 83,000 Birr

Contact
0953964175 @heymobile

@heyonlinemarket
Forwarded from WANAW SPORT
📢 ውብ ማልያዎች በተመጣጣኝ ዋጋ!

👉🏾 #ያናግሩን፣ ምርጫዎን ይዘዙን!

📌 ለበለጠ መረጃና ትዕዛዝ 📲 09011382830910851535 እና 0913586742 ላይ ይደውሉ።

👉🏾 እንዲሁም በቴሌግራም @Wanawsales ላይ የሽያጭ ሰራተኞቻችንን በቀጥታ በማናገር ወይም በቴሌግራም ቦት @WanawSportBot ይዘዙን።

🏅 ዋናው ወደፊት...

@wanawsportwear
TIKVAH-SPORT
አርሰናል ተጫዋቹን በውሰት ሊሰጥ ነው ! የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል የመሐል ሜዳ ተጨዋቹ ሳምቢ ሎኮንጋ በውሰት የላሊጋውን ክለብ ሲቪያ ለመቀላቀል ከጫፍ መድረሱ ተገልጿል። ሲቪያ የተጫዋቹን ሙሉ ደሞዝ ለመክፈል ከስምምነት መድረሳቸው ሲገለፅ እንዲሁም በሚቀጥለው አመት በ12 ሚልዮን ዩሮ የመግዛት አማራጭ እንደሚካተትላቸው ተነግሯል። ቤልጂየማዊው ተጨዋች ሎኮንጋ በቀጣይ የህክምና ምርመራውን በማድረግ…
አርሰናል ተጫዋቹ በውሰት አመራ !

የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል የመሐል ሜዳ ተጨዋች ሳምቢ ሎኮንጋ በውሰት የላሊጋውን ክለብ ሲቪያ መቀላቀሉ ይፋ ተደርጓል።

ሲቪያ ቤልጂየማዊውን የመሐል ሜዳ ተጨዋች ሎኮንጋ በሚቀጥለው አመት በ12 ሚልዮን ዩሮ የመግዛት አማራጭ እንዳላቸው ተገልጿል።

ሲቪያ በውሰት ቆይታው የተጫዋቹን ሙሉ ደሞዝ እንደሚከፍሉ ተነግሯል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ሮናልድ አራውሆ ቀዶ ጥገና ሊያደርግ ይችላል !

የባርሴሎና እና ዩራጓይ ብሔራዊ ቡድን የመሐል ተከላካይ ሮናልድ አራውሆ ባጋጠመው ጉዳት ምክንያት የቀዶ ጥገና ህክምና ሊደረግለት እንደሚችል ተገልጿል።

ተጨዋቹ ዩራጓይ ከብራዚል ባደረገችው የኮፓ አሜሪካ የምድብ ጨዋታ ወቅት ጉዳት አስተናግዶ በመጀመሪያው አጋማሽ ተቀይሮ ለመውጣት ተገዶ ነበር።

ሮናልድ አራውሆ ቀዶ ጥገናውን የሚያደርግ ከሆነ እስከ ታህሳስ ወር ከሜዳ ሊርቅ እንደሚችል ሲገለፅ የመጀመሪያው የኤል ክላሲኮ ጨዋታም ያመልጠዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ጆርዳን ሻኪሪ ከብሔራዊ ቡድኑ ራሱን አገለለ !

የስዊዘርላንድ ብሔራዊ ቡድን የመሐል ሜዳ ተጨዋች ጆርዳን ሻኪሪ በ31ዓመቱ ራሱን ከብሔራዊ ቡድኑ ማግለሉን በይፋ አስታውቋል።

" በብሔራዊ ቡድኑ በነበረኝ የአስራ አራት አመታት ቆይታ የማይረሱ ቅፅበቶች አልፈዋል፣ አሁን ጊዜው የመሰናበቻ ነው ጥሩ ትዝታዎች አሁንም ይኖራሉ ሁሉንም አመሰግናለሁ።" ሲል ጆርዳን ሻኪሪ ተናግሯል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
አልቫሮ ሞራታ ኤሲ ሚላንን ለመቀላቀል ተስማማ !

የስፔን ብሔራዊ ቡድን አምበል አልቫሮ ሞራታ አትሌቲኮ ማድሪድን በመልቀቅ የሴርያውን ክለብ ኤሲ ሚላን ለመቀላቀል ከስምምነት መድረሱ ተገልጿል።

ተጨዋቹ በኤሲ ሚላን ቤት የአራት አመታት ኮንትራት ለመፈረም በቃል ደረጃ ከስምምነት መድረሱ ተነግሯል።

ኤሲ ሚላን አልቫሮ ሞራታን የውል ማፍረሻውን 13 ሚልዮን ዩሮ ከፍለው እንደሚያስፈርሙት ተዘግቧል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
ዩናይትድ የግብ ጠባቂ አሰልጣኝ ሊቀጥር ነው ! ማንችስተር ዩናይትድ ያለፈውን የውድድር አመት በበርንሌይ ቤት ያሳለፉትን የግብ ጠባቂዎች አሰልጣኝ ጄሌ ቴን ሮዌላርን በሀላፊነት ሊሾሙ መሆኑ ተገልጿል። የግብ ጠባቂዎች አሰልጣኙ በቅርቡ ከበርንሌይ ጋር ከተለያዩ በኋላ አያክስን የተቀላቀሉ ቢሆንም ማንችስተር ዩናይትድ ካሳ ከፍሎ ለመውሰድ እየሰራ መሆኑ ተገልጿል። ያለፉትን አምስት አመታት በማንችስተር…
ዩናይትድ የግብ ጠባቂ አሰልጣኝ ሾመ !

ማንችስተር ዩናይትድ ያለፈውን የውድድር አመት በበርንሌይ ቤት ያሳለፉትን የግብ ጠባቂዎች አሰልጣኝ ጄሌ ቴን ሮዌላርን በሀላፊነት መሾማቸውን ይፋ አድርገዋል።

የግብ ጠባቂዎች አሰልጣኙ በቅርቡ ከበርንሌይ ጋር ከተለያዩ በኋላ አያክስን የተቀላቀሉ ቢሆንም ማንችስተር ዩናይትድ ካሳ ከፍሎ እንዳስፈረማቸው ተገልጿል።

" እሱ በእንግሊዝ እግርኳስ ጥሩ ልምድ አለው ቡድኑን እንደሚያግዝ እርግጠኛ ነኝ በተለይ ግብ ጠባቂዎች ከሌሎች ጋር እንዲዋሀድ ይረዳል።"ሲሉ ኤሪክ ቴንሀግ ስለ አሰልጣኙ ተናግረዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
ፉልሀም ስሚዝ ሮውን ማስፈረም ይፈልጋል ! ፉልሀም እንግሊዛዊውን የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል የመሐል ሜዳ ተጨዋች ኤሚል ስሚዝ ሮው የማስፈረም ፍላጎት እንዳላቸው ተገልጿል። አሰልጣኝ ማርኮ ሲልቫ በቀጣይ የፊት መስመራቸውን ለማጠናከር ከሚመለከቷቸው ተጨዋቾች ቀዳሚው ኤሚል ስሚዝ ሮው እንደሚሆን ተዘግቧል። ፉልሀም ተጨዋቹን ለማስፈረም የዝውውር መስኮቱ ሲከፍት ጥያቂያቸውን ሊያቀርቡ እንደሚችሉ ተነግሯል።…
አርሰናል ለተጫዋቹ የቀረበውን ጥያቄ ውድቅ አደረገ !

የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል ክሪስታል ፓላስ እና ፉልሀም ስሚዝ ሮውን ለማስፈረም ያቀረቡትን የዝውውር ጥያቄ ውድቅ ማድረጉ ተገልጿል።

መድፈኞቹ ሁለቱ ክለቦች የዝውውር ሒሳቡን አሻሽለው እንዲቀርቡ በንግግር ላይ መሆናቸው ሲገለፅ ተጨዋቹ በበኩሉ ሁሉንም አማራጮች መመልከት እንደሚፈልግ ተነግሯል።

እንግሊዛዊው የመሐል ሜዳ ተጨዋች ኤሚል ስሚዝ ሮው በመድፈኞቹ ቤት ብዙም የጨዋታ ሰዓት ባለማግኘቱ ምክንያት ክለቡን ሊለቅ እንደሚችል ሲገለፅ እንደነበር ይታወሳል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
የኤደርሰን የማንችስተር ሲቲ ቆይታ ? ብራዚላዊው የማንችስተር ሲቲ ግብ ጠባቂ ኤደርሰን ከሳውዲ አረቢያው ክለብ አል ኢትሀድ የዝውውር ጥያቄ እንደቀረበለት እና እያሰበበት እንደሚገኝ ተገልጿል። ኤደርሰን በክረምቱ የተጨዋቾች የዝውውር መስኮት ጥሩ የዝውውር ጥያቄዎች ከቀረቡለት ማንችስተር ሲቲን ለመልቀቅ ሊያስብ እንደሚችል መገለፁ ይታወቃል። ማንችስተር ሲቲ በበኩሉ ተጫዋቹ በክለቡ እንዲቀጥል እንደሚፈልጉ…
አል ናስር ለኤደርሰን የዝውውር ጥያቄ አቀረበ !

የሳውዲ አረቢያው ክለብ አል ናስር ብራዚላዊውን ግብ ጠባቂ ኤደርሰን ለማስፈረም ለማንችስተር ሲቲ ይፋዊ የዝውውር ጥያቄ ማቅረባቸው ተገልጿል።

አል ናስር ለዝውውሩ 30 ሚልዮን ዩሮ የሚደርስ የዝውውር ሒሳብ ሲያቀርቡ ማንችስተር ሲቲ በበኩሉ ውድቅ ማድረጉ ተነግሯል።

ማንችስተር ሲቲ ኤደርሰንን ከለቀቀው ከ 50 ሚልዮን ዩሮ በላይ እንደሚፈልግ የተገለፀ ሲሆን ተጨዋቹ ከአል ናስር ጋር በግል ከስምምነት ደርሰዋል ተብሏል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ዩናይትድ በወዳጅነት ጨዋታ ተሸነፈ !

ለሚቀጥለው የውድድር ዘመን የሚያደርገውን ዝግጅት የጀመረው ማንችስተር ዩናይትድ ከደቂቃዎች በፊት የመጀመሪያ የወዳጅነት ጨዋታውን አድርጓል።

ወደ ኖርዌይ በማምራት ከሮዘንቦርግ ጋር የወዳጅነት ጨዋታቸውን ያደረጉት ቀያዮቹ ሴጣኖች በጨዋታው መጠናቀቂያ ደቂቃ በተቆጠረባቸው ግብ 1ለ0 ተሸንፈዋል።

ማንችስተር ዩናይትድ በጨዋታው ከእረፍት በፊት የዋናውን ቡድን ተጨዋቾች ከታዳጊዎች ሲያጣምሩ ከእረፍት መልስ ታዳጋዎችን አሰልፈው አጫውተዋል።

ቀያዮቹ ሴጣኖች ሁለተኛ የወዳጅነት ጨዋታቸውን የፊታችን ቅዳሜ ከሬንጀርስ ጋር ያደርጋሉ።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
" ያሳየነው እንቅስቃሴ ለክለቡ አይመጥንም " ቴንሀግ

የማንችስተር ዩናይትድ ዋና አሰልጣኝ ኤሪክ ቴንሀግ ቡድናቸው ከደቂቃዎች በፊት የተሸነፈው ምንም እንኳን በወዳጅነት ጨዋታ ቢሆንም የተሻለ መንቀሳቀስ እንዳለበት አሳስበዋል።

" የተመለከትነው የትልቅ እግርኳስ ደረጃ አይነት አይደለም እንደ ማንችስተር ዩናይትድ ያለ ቡድን የተሻለ መንቀሳቀስ አለበት " ሲሉ ኤሪክ ቴንሀግ ተናግረዋል።

" የወዳጅነት ጨዋታ ቢሆንም ማንችስተር ዩናይትድ ማሸነፍ አለበት ማሸነፍ ባይችል እንኳን መሸነፍ የለበትም።"ቴንሀግ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
" ደጋፊው ግሪንውድን ከፈለገ ገንዘብ ያዋጣ "

የጣልያኑ ክለብ ላዝዮ ፕሬዝዳንት የሆኑት ክላውዲዮ ሎቲቶ የክለቡ ደጋፊ ለተጨዋች ፊርማ ገንዘብ መክፈል እንዳለበት ገልጸዋል።

ግሪንውድን ከማንችስተር ዩናይትድ ለማስፈረም እያደረጉ ስለሚገኙት ጥረት የተናገሩት ክላውዲዮ ሎቲቶ " ደጋፊዎች ግሪንውድን ማስፈረም ከፈለጉ ገንዘብ መክፈል አለባቸው " ሲሉ ተናግረዋል።

ፕሬዚዳንቱ አያይዘውም ለግሪንውድ ዝውውር 25 ሚልዮን ዩሮ እና ከወደፊት ሽያጭ 50% የሚያስገኝ የዝውውር ጥያቄ ለማንችስተር ዩናይትድ ማቅረባቸውን ገልጸዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
Forwarded from HEY Online Market
•PlayStation 5, 73,000 Birr
•Playstaion 5 Slim, 78,000 Birr

•PlayStation 4 Slim, 35,000 Birr
•PlayStation 4 Pro, 43,000 Birr

•Playstaion portal, 35,000 Birr
•Meta Quest 2, 55,000 Birr
•Meta Quest 3, 83,000 Birr

Contact
0953964175 @heymobile

@heyonlinemarket
መልካም ዕድል!
ከፍ የተደረጉ ኦዶችን አይተዋል ? እንግዲያውስ ተወራረዱባቸው!
Modern Sport - Al Ahly
ለተሻለ ውርርድ ቤቲካን ይጠቀሙ! አሁኑኑ Betika.et ላይ /በቴሌግራም ቦታችን - @BetikaETBot ይወራረዱ!
ኢትዮጵያ የምታዘጋጀው የሴቶች ሻምፒየንስ ሊግ ማጣሪያ መቼ ይካሄዳል ?

በሀገራችን ኢትዮጵያ የሚካሄደው የዘንድሮው የሴካፋ ሀገራት የካፍ ሴቶች ሻምፒየንስ ሊግ ማጣሪያ ውድድር የሚደረግበት ቀን እና ተሳታፊ ክለቦች ይፋ ተደርገዋል።

ውድድሩ ከነሐሴ 11/2016 ዓ.ም እስከ ነሐሴ 29/2016 ዓ. ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል።

በውድድሩ ዘጠኝ ክለቦች ተካፍለው አሸናፊው ክለብ ምስራቅ አፍሪካን ወክሎ በካፍ ሻምፒየንስ ሊግ ውድድሮች የሚሳተፍ ይሆናል።

በውድድሩ እነማን ይሳተፋሉ ?

- የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ( ኢትዮጵያ )

- ካዋምፔ ሙስሊም ( ዩጋንዳ )        

- ሲምባ ኪውንስ ( ታንዛኒያ )

- ኬንያ ፖሊስ ቡሌት ( ኬንያ ) 

- ዋርየርስ ክዊንስ ( ዛንዚባር )

- ፋድ ጅቡቲ ( ጅቡቲ )           

- ዬ ጆይንት ስታርስ ( ደቡብ ሱዳን )

- PVP ቡየንዚ ( ቡሩንዲ )                       

- ራዮን ስፖርት ( ሩዋንዳ )

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
" ህልሜን አሳክቻለሁ " ምባፔ

ፈረንሳዊው የሎስ ብላንኮዎቹ የፊት መስመር ተጨዋች ኪሊያን ምባፔ በክለቡ የህክምና ምርመራውን ለማድረግ በማድሪድ ተገኝቷል።

ሪያል ማድሪድን በመቀላቀሉ ስለተሰማው ስሜት ከጋዜጠኞች ጥያቄ የቀረበለት ኪሊያን ምባፔ " ህልሜን ነው ያሳካሁት " ሲል ምላሽ ሰጥቷል።

ሪያል ማድሪድ በዛሬው ዕለት ከሰዓታት በኋላ በሳንቲያጎ በርናቦ ስታዲየም 80,000 ደጋፊዎች በተገኙበት ለኪሊያን ምባፔ ይፋዊ አቀባበል ያደርጋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
አሰልጣኝ ጋሪዝ ሳውዝጌት ከሀላፊነታቸው ለቀቁ !

የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን ወሠና አሰልጣኝ ጋሪዝ ሳውዝጌት ከብሔራዊ ቡድኑ ሀላፊነት መልቀቃቸውን በይፋ አስታውቀዋል።

አሰልጣኝ ጋሪዝ ሳውዝጌት የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን ላለፉት ስምንት አመታት በሀላፊነት ሲመሩ በአለም ዋንጫ ግማሽ ፍፃሜ እንዲሁም በተከታታይ በአውሮፓ ዋንጫ ፍፃሜ ተፋላሚ መሆን ችለዋል።

አሰልጣኙ ከሀላፊነታቸው ከለቀቁ በኋላ " እንግሊዝን ማሰልጠን ለእኔ ሁሉም ነገር ነው ፣ በነበረው ቆይታ ያለኝን ሁሉ ሰጥቻለሁ አሁን ደግሞ ለሌላ ምዕራፍ ጊዜው ነው " ብለዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
" ማራቶን ካቋረጥሽ ፈርሚ ከተባለ እጅግ የሚያሳዝን ነው " ኃይሌ ገብረ ሥላሴ

ሻለቃ አትሌት ኃይሌ ገብረ ሥላሴ በፓሪስ ኦሎምፒክ ማራቶን ውድድር " አላቋርጥም ብለሽ ፈርሚ " የተባለ አትሌት አለ መባሉን " እውነት ከሆነ እጅግ የሚያሳዝን " ሲል ገልፆታል።

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ረ/ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉ ስለ ጉዳዩ ከቀናት በፊት ተጠይቃ "  በፍጹም ልክ አይደለም ቅር ብሎኛል ግን ደግሞ ልጅቷ በራሷ ተማምና ሄዳ መፈረሟ በእሷ እንድደሰት አድርጎኛል።"ብላለች።

ከብሔራዊ ቴሌቪዥን ጋር በነበራቸው ቆይታ በጉዳዩ ላይ ማብራሪያ የሰጡት የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ የቴክኒክ እና ህዝብ ግንኙነት ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ቢልልኝ መቆያ " አሉባልታ ነው " ሲሉ የገለፁ ሲሆን " አልተባለም " በማለት ማረጋገጫ ሰጥተዋል።

አቶ ቢልልኝ አያይዘውም " መረጃው አትሌቷን የሚጎዳ እና ለሌሎች ሀገራት ሞራል የሚሰጥ ነው ፣ የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ የሚሰራውን ያውቃል " ብለዋል።

ሻለቃ አትሌት ኃይሌ ገብረ ሥላሴ በበኩሉ " ስሰማው በጣም ደንግጫለሁ አይደለም ማስፈረም በቃልም አላቋርጥም በይ ካሏት ተገቢ አይደለም ሊታሰብም አይገባም " ሲል ከሸገር ኤፍ ኤም ስፖርት ጋር በነበረው ቆይታ ተናግሯል።

ይህንን የተባለችው አትሌት ትግስት " ካሸነፈችው የአለም ሪከርድ ወይም ኦሎምፒክን ብታስመርጣት ኦሎምፒክን የምትመርጥ ነች " ሲል ሻለቃ አትሌት ኃይሌ ገብረ ሥላሴ ገልጿል።

የአለም የማራቶን ሪከርድ ባለቤቷ አትሌት ትግስት አሰፋ ለማራቶን ከፍተኛ ዝግጅት ላይ ስትገኝ ሙሉ ወጪ በመሸፈን የህክምና ባለሙያና አሰልጣኟን ወደ ፓሪስ ይዛ በመሄድ የፓሪስ ማራቶን የሚደረግበት ቦታን መመልከት መቻሏ ተገልጿል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
2024/10/03 17:26:37
Back to Top
HTML Embed Code: