Telegram Web Link
የቱርክ ደጋፊዎች የኔዘርላንድን ተጨዋቾች ለመረበሽ ሞክረዋል !

የአውሮፓ ዋንጫ ሩብ ፍፃሜ ጨዋታቸውን ከኔዘርላንድ ጋር የሚያደርጉት ቱርክ ብሔራዊ ቡድን ደጋፊዎች የተጋጣሚያቸውን ደጋፊዎች ለመረበሽ መሞከራቸው ተገልጿል።

የቱርክ ብሔራዊ ቡድን ደጋፊዎች ትላንት ሌሊት የኔዘርላንድ ተጨዋቾች ባረፉበት ሆቴል በማምራት ርችት እና ተቀጣጣይ ነገሮችን በማጮህ ለመረበሽ መሞከራቸው ተነግሯል።

የሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች ጨዋታ ዛሬ ምሽት 4:00 ሰዓት በርሊን በሚገኘው ግዙፉ ኦሎምፒያስታድዮን ስታዲየም ይደረጋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
Forwarded from WANAW SPORT
📢 #ዋናው የቴሌግራም ቦት እንዴት የስፖርት አልባሳትን ያዛሉ?

🤖 @WanawSportBot 🤖

🏅 ዋናው ወደፊት...

@wanawsportwear
TIKVAH-SPORT
ቶኒ ክሩስ ፔድሪን ይቅርታ ጠይቋል ! ጀርመናዊው የመሐል ሜዳ ተጨዋች ቶኒ ክሩስ ትላንት በስፔን በተሸነፉበት ጨዋታ ፔድሪ ላይ ለሰራው ጥፋት በማህበራዊ ትስስር ገፁ ተጫዋቹን ይቅርታ ጠይቋል። " ፔድሪ ጉዳት እንዲያጋጥመው ሆንብዬ አስቤ አልነበረም ጥፋቱን የሰራሁት " ያለው ቶኒ ክሩስ ይቅርታ ማለት እና ቶሎ እንድትመለስ መመኘት እፈልጋለሁ አንተ ምርጥ ተጨዋች ነህ።"ሲል ተናግሯል። በጨዋታው ፔድሪ…
ፔድሪ በብሔራዊ ቡድኑ ስብስብ ይቆያል !

የስፔን ብሔራዊ ቡድን የመሐል ሜዳ ተጨዋች ፔድሪ ባጋጠመው ጉዳት ምክንያት በቀጣይ በአውሮፓ ዋንጫው በሚኖሩ ጨዋታዎች መሳተፍ እንደማይችል ይፋ ሆኗል።

ይሁን እንጂ የባርሴሎናው የመሐል ሜዳ ተጨዋች ፔድሪ እስከ ውድድሩ መጨረሻ በስፔን ብሔራዊ ቡድን ስብስብ እንደሚቆይ ተገልጿል።

ፔድሪ ያጋጠመው የጉልበት ጉዳት እስከ አንድ ወር ከሜዳ ሊያርቀው እንደሚችል ተነግሯል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
የጨዋታ አሰላለፍ !

1:00 እንግሊዝ ከ ስዊዘርላንድ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሻምፒዮን ሆነ !

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከኢትዮጵያ መድን ጋር ያደረገውን የኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ የመጨረሻ ሳምንት መርሐ ግብር 2ለ0 በማሸነፍ ሻምፒዮን መሆናቸውን አረጋግጠዋል።

ንግድ ባንክ በውድድር ዘመኑ የሰበሰባቸውን ነጥቦች ስልሳ አራት በማድረስ ከመቻል በአንድ ነጥብ በልጠው የሊጉ አሸናፊ ሆነዋል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ወደ ኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ በመጣበት አመት በታሪኩ የመጀመሪያው የሆነውን የኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ ዋንጫ ማሳካት ችሏል።

ኤርትራዊው የሀዋሳ ከተማ የፊት መስመር ተጨዋች ዓሊ ሱሌይማን በውድድር ዘመኑ ሀያ የሊግ ግቦችን በማስቆጠር ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ በመሆን አጠናቋል።

ሀምበሪቾ ዱራሜ እና ሻሸመኔ ከተማ ከኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ ወደ ከፍተኛ ሊግ የወረዱ ክለቦች ናቸው።

ኢትዮ ኤሌክትሪክ እና አርባምንጭ ከተማ በበኩላቸው በሚቀጥለው አመት ወደ ኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ አድገዋል።

በተጨማሪም ከውድድር ውጪ የነበሩት የትግራይ ክልል ክለቦች መቐለ ሰባ እንደርታ ፣ ስሑል ሽረ እና ወልዋሎ አዲግራት ዩንቨርስቲ ቀጣይ አመት ወደ ሊጉ ይመለሳሉ።

በሚቀጥለው የ2017 የውድድር አመት የኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ በአስራ ዘጠኝ ክለቦች መካከል የሚደረግ ሲሆን አምስት ክለቦች ወደ ከፍተኛ ሊግ ይወርዳሉ።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
" የባንካችንን ስም የሚመጥን ቡድን በመሆኑ ተደስተናል " አቶ አቤ ሳኖ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዝዳንት አቶ ኤቤ ሳኖ ከሶስት አመታት በፊት በድጋሜ እንዲቋቋም ያደረጉት የባንኩ የእግርኳስ ቡድን ሻምፒዮን በመሆኑ መደሰታቸውን ገልጸዋል።

" ከፍተኛ ደስታ ነው የተሰማኝ ለንግድ ባንክ አዲስ ታሪክ ነው " ሲሉ የገለፁት ፕሬዝዳንቱ ክለቡ ረጅም ታሪክ ቢኖረውም በሶስት አመት ተሰርቶ ሻምፒዮን ሆኗል ፣ ባንካችንን ስሙን የሚመጥን ቡድን በመሆኑ ደስተኞች ነን ብለዋል።

ክለቡ ዋንጫውን ባያሳካም በድጋሜ በማቋቋማቸው እንደማይፀፀቱ የገለፁት ፕሬዝዳንት ኤቤ ሳኖ የሀገሪቱ ትልቅ ተቋም ስፖርቱ ላይ መስራት አለበት በቀጣይም እቅዶች አሉን ብለዋል።

ባንኩ ያለውን ስታዲየም ጥራት ያለው አድርጎ የመስራት እቅድ መያዙን እና ራሱ በሚያሳድጋቸው ተጨዋቾች ቡድን ሰርቶ ለሀገር የሚጠቅሙ ስፖርተኞች ማፍራት እንደሚፈልግ ፕሬዝዳንቱ ጨምረው ገልጸዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
እረፍት | እንግሊዝ 0 - 0 ስዊዘርላንድ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
75 ' እንግሊዝ 0 - 1 ስዊዘርላንድ

ኢምቦሎ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
80 ' እንግሊዝ 1 - 1 ስዊዘርላንድ

ሳካ                   ኢምቦሎ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ተጠናቀቀ | እንግሊዝ 1 - 1 ስዊዘርላንድ

ሳካ            ኢምቦሎ

- ሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች ጨዋታቸውን በአቻ ውጤት ማጠናቀቃቸውን ተከትሎ ወደ ተጨማሪ ሰዓት አምርተዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
የጨዋታ አሰላለፍ !

4:00 ቱርክ ከ ኔዘርላንድ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ተጠናቀቀ | እንግሊዝ 1 - 1 ስዊዘርላንድ

ሳካ             ኢምቦሎ

- ጨዋታው በአቻ ውጤት መጠናቀቁን ተከትሎ ሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች ወደ መለያ ምት አምርተዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
የመለያ ምት ተጀምሯል !

🏴󠁧󠁢󠁥󠁮󠁧󠁿 እንግሊዝ

🇨🇭 ስዊዘርላንድ

ውጤት በዚሁ ፖስት ላይ " Update " ይደረጋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
እንግሊዝ ግማሽ ፍፃሜውን ተቀላቀሉ !

በአውሮፓ ዋንጫ ሩብ ፍፃሜ የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን ከስዊዘርላንድ ብሔራዊ ቡድን ጋር ያደረጉትን ጨዋታ በመለያ ምት 5ለ3 በማሸነፍ ግማሽ ፍፃሜ መድረስ ችለዋል።

ሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች መደበኛውን የጨዋታ ክፍለጊዜ 1ለ1 በሆነ አቻ ውጤት ማጠናቀቅ ችለዋል።

በመደበኛው የጨዋታ ክፍለጊዜ ግቦችን ለእንግሊዝ ቡካዩ ሳካ እንዲሁም ለስዊዘርላንድ ብሪል ኢምቦሎ አስቆጥረዋል።

የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን በግማሽ ፍፃሜው የቱርክ እና ኔዘርላንድን አሸናፊ የሚገጥሙ ይሆናል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
35 ' ቱርክ 1 - 0 ኔዘርላንድ

አካይዲን

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
እረፍት | ቱርክ 1 - 0 ኔዘርላንድ

አካይዲን

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
2024/09/30 14:29:43
Back to Top
HTML Embed Code: