Telegram Web Link
መልካም ዕድል!
ከፍ የተደረጉ ኦዶችን አይተዋል ? እንግዲያውስ ተወራረዱባቸው!
England - Switzerland
Netherlands - Turkey
ለተሻለ ውርርድ ቤቲካን ይጠቀሙ! አሁኑኑ Betika.et ላይ /በቴሌግራም ቦታችን - @BetikaETBot ይወራረዱ!
Forwarded from HEY Online Market
Play More and Spend less!

•PS4 Slim, 34,999 Birr
•PS4 PRO, 41,999 Birr
•Original Controller 6,499 Birr

Contact Us
0953964175 @heymobile

@heyonlinemarket
" ከውድድሩ መውጣታችን ያማል " ኔግልስማን

የጀርመን ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ጁሊያን ኔግልስማን ቡድኑ በስፔን ተሸንፎ ከአውሮፓ ዋንጫ ውድድር መውጣቱ " የሚያም ነበር " ሲሉ ገልጸዋል።

" በድጋሜ በምናዘጋጀው ውድድር የመሳተፍ እድል የምናገኝ አይመስለኝም " ያሉት አሰልጣኙ ከውድድሩ መውጣታችን ያማል አጨዋወታችን መጥፎ ቢሆን እንቀበለው ነበር ነገርግን ጥሩ ነው የተጫወትነው ሲሉ ተናግረዋል።

የቡድኑ የመጨረሻ ጨዋታውን ያደረገው ቶኒ ክሩስ በበኩሉ " ሁላችንም ያለምነው ህልም ቀርቷል ፣ ያለንን ሁሉ ሰጥተናል በዚህም ኩራት ይሰማናል።

ለጀርመን እግርኳስ በድጋሜ ተስፋ ሰጥተነዋል ነገርግን ከውድድሩ መውጣታችን ቅር አሰኝቶናል።"ሲል ተናግሯል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የኢትዮጵያን ፕርሚየር ሊግ ማን ያሳካል ?

የሊጉን አሸናፊ እስከ መጨረሻው ጨዋታ ያላሳወቀው የዘንድሮው የ2016 የኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ ውድድር በዛሬው ዕለት ከሚደረጉ ተጠባቂ ጨዋታዎች በኋላ አሸናፊውን ይለያል።

ፕርሚየር ሊጉን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በስልሳ አንድ ነጥቦች እና በሀያ ስምንት ንፁህ ግቦች በበላይነት እየመራው ይገኛል።

መቻል በበኩሉ ከሊጉ መሪ በአንድ ነጥብ ዝቅ ብሎ በስልሳ ነጥቦች እና በአስራ ዘጠኝ ንፁህ ግቦች ሁለተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል።

በሊጉ የመጨረሻ ሳምንት መርሐግብር ዛሬ ቀን 10:00 ሰዓት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከ ኢትዮጵያ መድን እንዲሁም መቻል ከ ድሬዳዋ ከተማ በተመሳሳይ ሰዓት የሚጫወቱ ይሆናል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጨዋታውን ማሸነፍ በቀጥታ የሊጉ ሻምፒዮን ሲያደርገው ነጥብ የሚጥል ወይም የሚሸነፍ ከሆነ እና መቻሎች የሚያሸንፉ ከሆነ ሊጉን ማሳካት ይችላሉ።

የኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ ውድድር አሸናፊውን በመጨረሻ ሳምንት ጨዋታ ሲለይ በውድድሩ ታሪክ ይህ ለስምንተኛ ጊዜ መሆኑ ተገልጿል።

Video Credit - Haileegziabher Adhanom

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
" የኢትዮጵያ ህዝብ እንዲፈርደኝ እፈልጋለሁ " ፍሬወይኒ ሀይሉ

ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ፍሬወይኒ ሀይሉ ያለአግባብ በፓሪስ ኦሎምፒክ ውድድር ተሳታፊ አትሌቶች ዝርዝር ውስጥ ሳልካተት ቀርቻለሁ ስትል ቅሬታዋን ህዝብ ይወቅልኝ በማለት ገልፃለች።

በ1500 እና 5000 ሜትር ተወዳዳሪ መሆኗን ያስታወሰችው አትሌት ፍሬወይኒ ሀይሉ በአመቱ ውስጥ በሁለቱም ርቀቶች ከሌሎች አትሌቶች የተሻለ ውጤት አስመዝግቤ ነበር ትላለች።

አትሌቷ በ2024 የቤት ውስጥ ሻምፒዮና በ1500ሜ ወርቅ እና የተሻለ ሰዓት እንዲሁም በ5000ሜ የ2024 የአለም ምርጥ 3ኛ ሰዓት ባስመዘግብም ከሁለቱም ርቀቶች ከኦሎምፒክ ውጪ ሆኛለሁ ብላለች።

አትሌት ፍሬወይኒ ሀይሉ ቀጥላም " እኔ በዚህ አመት የተሻለ ሰዓት ባስመዘግብም ከአመት በፊት ጥሩ ውጤት ያላቸው አትሌቶች ተመርጠው እኔ ቀርቻለሁ የኢትዮጵያ ህዝብ ይወቅልኝ።

በ2024 ምንም ውድድር ሳይወዳደሩ የ2023 አላቸው ተብሎ መምረጥ አግባብ አይደለም ለምን በሀቀኝነት አይመረጥም ምንም ሳይሮጡ እየተመረጡ ነው እኛ ግን ደክመንም እየቀረን ነው።

የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ እና አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለምንድን ነው የእኛን ማየት የማይችለው በዚህ ላይ ማብራሪያም እፈልጋለሁ።"ስትል ተናግራለች።

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በትላንትናው ዕለት ኢትዮጵያን በኦሎምፒክ የሚወክሉ አትሌቶችን ይፋ ሲያደርግ አትሌት ፍሬወይኒ ሀይሉ የ5000ሜ ተጠባባቂ ሆና ተመርጣለች።

ምንጭ - ሀገሬ ቴሌቪዥን

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ዌስትሀም ዩናይትድ ተጨዋች አስፈረሙ !

ዌስትሀም ዩናይትድ እንግሊዛዊውን የተከላካይ ስፍራ ተጨዋች ማክስ ኪልማን ከዎልቭስ ማስፈረማቸውን ይፋ አድርገዋል።

ዌስትሀም ለተጨዋቹ ዝውውር 40 ሚልዮን ፓውንድ ወጪ ማድረጋቸው ሲነገር ተጨዋቹ በክለቡ የሰባት አመት ኮንትራት መፈረሙ ተገልጿል።

" ዌስትሀም እንደሚፈልገኝ ሳውቅ ለመቀላቀል ፈልጊያለሁ ፣ ዌስትሀም ትልቅ ክለብ ነው የእግርኳስ ህይወቴ አንድ እርምጃ እንዳደገ ይሰማኛል።"ሲል ማክስ ኪልማን ተናግሯል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
አዲዳስ የጫማ ምርቱን ስያሜ በክሩስ ስም ሰየመ !

እውቁ የትጥቅ አምራች ተቋም አዲዳስ ቶኒ ክሩስ በብቸኝነት እስካሁን እየተጠቀመው የሚገኘውን " adidas 11pro " ጫም ስያሜ በክሩስ ስም መቀየሩን ይፋ አድርጓል።

በዚህም መሰረት የእግርኳስ መጫወቻ ጫማ ምርቱ ስያሜ ከዚህ በኋላ " Toni Kroos Pro boots " ተብሎ እንደሚጠራ ተገልጿል።

ጀርመናዊው ታሪካዊ ተጨዋች ቶኒ ክሩስ ባለፉት አስራ ሶስት አመታት ተመሳሳይ የአዲዳስ " adidas 11pro " ምርት የሆነ ጫማን ሲጠቀም እንደነበር ይታወቃል።

ቶኒ ክሩስ በቀድሞው የአዲዳስ " adidas 11pro " ምርት የሆነ ጫማ እየተጫወተ የሚያሻማቸው ኳሶች ትክክለኛነታቸው ከ90% በላይ እንደነበር ተገልጿል።

ስኬታማ የእግርኳስ ህይወት ማሳለፍ የቻለው ቶኒ ክሩስ ከእግርኳስ አለም ራሱን ማግለሉ አይዘነጋም።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
" አላማችን ሊጉን ማሸነፍ መሆን አለበት " አርኔ ስሎቶ

የመርሲሳይዱ ክለብ ሊቨርፑል ዋና አሰልጣኝ አርኔ ስሎት በሚቀጥለው የውድድር አመት አላማቸው የእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ ዋንጫን ማሳካት እንደሆነ ገልጸዋል።

" በቀጣይ አላማችን እና ሙሉ ትኩረታችን የፕርሚየር ሊጉን ዋንጫ ማሳካት ላይ መሆን አለበት " የሚሉት አሰልጣኝ አርኔ ስሎት ይህ ማድረግ የምንፈልገው ነገር ነው የሊጉ የበላይ መሆን እንፈልጋለን ብለዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ቶኒ ክሩስ ፔድሪን ይቅርታ ጠይቋል !

ጀርመናዊው የመሐል ሜዳ ተጨዋች ቶኒ ክሩስ ትላንት በስፔን በተሸነፉበት ጨዋታ ፔድሪ ላይ ለሰራው ጥፋት በማህበራዊ ትስስር ገፁ ተጫዋቹን ይቅርታ ጠይቋል።

" ፔድሪ ጉዳት እንዲያጋጥመው ሆንብዬ አስቤ አልነበረም ጥፋቱን የሰራሁት " ያለው ቶኒ ክሩስ ይቅርታ ማለት እና ቶሎ እንድትመለስ መመኘት እፈልጋለሁ አንተ ምርጥ ተጨዋች ነህ።"ሲል ተናግሯል።

በጨዋታው ፔድሪ ባጋጠመው ከባድ ጉዳት ምክንያት ተቀይሮ ለመውጣት መገደዱ የሚታወስ ሲሆን በቀጣይ በአውሮፓ ዋንጫ ጨዋታዎች ይሳተፋል ተብሎ አይጠበቅም።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
የቱርክ ደጋፊዎች የኔዘርላንድን ተጨዋቾች ለመረበሽ ሞክረዋል !

የአውሮፓ ዋንጫ ሩብ ፍፃሜ ጨዋታቸውን ከኔዘርላንድ ጋር የሚያደርጉት ቱርክ ብሔራዊ ቡድን ደጋፊዎች የተጋጣሚያቸውን ደጋፊዎች ለመረበሽ መሞከራቸው ተገልጿል።

የቱርክ ብሔራዊ ቡድን ደጋፊዎች ትላንት ሌሊት የኔዘርላንድ ተጨዋቾች ባረፉበት ሆቴል በማምራት ርችት እና ተቀጣጣይ ነገሮችን በማጮህ ለመረበሽ መሞከራቸው ተነግሯል።

የሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች ጨዋታ ዛሬ ምሽት 4:00 ሰዓት በርሊን በሚገኘው ግዙፉ ኦሎምፒያስታድዮን ስታዲየም ይደረጋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
Forwarded from WANAW SPORT
📢 #ዋናው የቴሌግራም ቦት እንዴት የስፖርት አልባሳትን ያዛሉ?

🤖 @WanawSportBot 🤖

🏅 ዋናው ወደፊት...

@wanawsportwear
TIKVAH-SPORT
ቶኒ ክሩስ ፔድሪን ይቅርታ ጠይቋል ! ጀርመናዊው የመሐል ሜዳ ተጨዋች ቶኒ ክሩስ ትላንት በስፔን በተሸነፉበት ጨዋታ ፔድሪ ላይ ለሰራው ጥፋት በማህበራዊ ትስስር ገፁ ተጫዋቹን ይቅርታ ጠይቋል። " ፔድሪ ጉዳት እንዲያጋጥመው ሆንብዬ አስቤ አልነበረም ጥፋቱን የሰራሁት " ያለው ቶኒ ክሩስ ይቅርታ ማለት እና ቶሎ እንድትመለስ መመኘት እፈልጋለሁ አንተ ምርጥ ተጨዋች ነህ።"ሲል ተናግሯል። በጨዋታው ፔድሪ…
ፔድሪ በብሔራዊ ቡድኑ ስብስብ ይቆያል !

የስፔን ብሔራዊ ቡድን የመሐል ሜዳ ተጨዋች ፔድሪ ባጋጠመው ጉዳት ምክንያት በቀጣይ በአውሮፓ ዋንጫው በሚኖሩ ጨዋታዎች መሳተፍ እንደማይችል ይፋ ሆኗል።

ይሁን እንጂ የባርሴሎናው የመሐል ሜዳ ተጨዋች ፔድሪ እስከ ውድድሩ መጨረሻ በስፔን ብሔራዊ ቡድን ስብስብ እንደሚቆይ ተገልጿል።

ፔድሪ ያጋጠመው የጉልበት ጉዳት እስከ አንድ ወር ከሜዳ ሊያርቀው እንደሚችል ተነግሯል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
የጨዋታ አሰላለፍ !

1:00 እንግሊዝ ከ ስዊዘርላንድ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሻምፒዮን ሆነ !

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከኢትዮጵያ መድን ጋር ያደረገውን የኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ የመጨረሻ ሳምንት መርሐ ግብር 2ለ0 በማሸነፍ ሻምፒዮን መሆናቸውን አረጋግጠዋል።

ንግድ ባንክ በውድድር ዘመኑ የሰበሰባቸውን ነጥቦች ስልሳ አራት በማድረስ ከመቻል በአንድ ነጥብ በልጠው የሊጉ አሸናፊ ሆነዋል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ወደ ኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ በመጣበት አመት በታሪኩ የመጀመሪያው የሆነውን የኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ ዋንጫ ማሳካት ችሏል።

ኤርትራዊው የሀዋሳ ከተማ የፊት መስመር ተጨዋች ዓሊ ሱሌይማን በውድድር ዘመኑ ሀያ የሊግ ግቦችን በማስቆጠር ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ በመሆን አጠናቋል።

ሀምበሪቾ ዱራሜ እና ሻሸመኔ ከተማ ከኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ ወደ ከፍተኛ ሊግ የወረዱ ክለቦች ናቸው።

ኢትዮ ኤሌክትሪክ እና አርባምንጭ ከተማ በበኩላቸው በሚቀጥለው አመት ወደ ኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ አድገዋል።

በተጨማሪም ከውድድር ውጪ የነበሩት የትግራይ ክልል ክለቦች መቐለ ሰባ እንደርታ ፣ ስሑል ሽረ እና ወልዋሎ አዲግራት ዩንቨርስቲ ቀጣይ አመት ወደ ሊጉ ይመለሳሉ።

በሚቀጥለው የ2017 የውድድር አመት የኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ በአስራ ዘጠኝ ክለቦች መካከል የሚደረግ ሲሆን አምስት ክለቦች ወደ ከፍተኛ ሊግ ይወርዳሉ።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
2024/10/02 16:29:15
Back to Top
HTML Embed Code: