Telegram Web Link
119 '

ስፔን 2 - 1 ጀርመን

ኦልሞ       ፍሎሪያን ቨርትዝ
ሜሪኖ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ስፔን ግማሽ ፍፃሜውን ተቀላቀሉ !

የስፔን ብሔራዊ ቡድን ከጀርመን ብሔራዊ ቡድን ጋር ያደረገውን የአውሮፓ ዋንጫ ሩብ ፍፃሜ ጨዋታ 2ለ1 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ግማሽ ፍፃሜውን ተቀላቅለዋል።

የስፔን ብሔራዊ ቡድን የማሸነፊያ ግቦችን ዳኒ ኦልሞ እና ሚኬል ሜሪኖ ከመረብ ማሳረፍ ሲችሉ ለጀርመን ፍሎሪያን ቨርትዝ አስቆጥሯል።

የአውሮፓ ዋንጫው አዘጋጅ ሀገር ጀርመን ከውድድሩ ውጪ ሆነዋል።

ጨዋታው ለጀርመን ብሔራዊ ቡድን አማካይ ቶኒ ክሩስ የእግርኳስ ህይወቱ የመጨረሻ ጨዋታው ሆኗል።

በጨዋታው እንግሊዛዊው የመሐል ዳኛ አንቶኒ ቴለር አስራ ስድስት የማስጠንቀቂያ ካርዶችን እና አንድ ቀይ ካርድ መዘዋል።

ስፔን በግማሽ ፍፃሜው የፖርቹጋል እና ፈረንሳይን አሸናፊ የሚገጥሙ ይሆናል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
እረፍት

ፈረንሳይ 0 - 0 ፖርቹጋል

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
#ተጠናቀቀ

ፈረንሳይ 0 - 0 ፖርቹጋል

- ሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች ጨዋታቸውን በአቻ ውጤት ማጠናቀቃቸውን ተከትሎ ወደ ተጨማሪ ሰዓት አምርተዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
#ተጠናቀቀ

ፈረንሳይ 0 - 0 ፖርቹጋል

- ጨዋታው በአቻ ውጤት መጠናቀቁን ተከትሎ ሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች ወደ መለያ ምት አምርተዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
የመለያ ምት ተጀምሯል !

🇵🇹 ፖርቹጋል

🇫🇷 ፈረንሳይ

ውጤት በዚሁ ፖስት ላይ " Update " ይደረጋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ፈረንሳይ ግማሽ ፍፃሜውን ተቀላቀሉ !

የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን ከፖርቹጋል አቻው ጋር ያደረገውን የአውሮፓ ዋንጫ ሩብ ፍፃሜ ጨዋታ በመለያ ምት 5ለ3 በማሸነፍ ግማሽ ፍፃሜ መድረሳቸውን አረጋግጠዋል።

በፖርቹጋል ብሔራዊ ቡድን በኩል ጇ ፊሊክስ የመለያ ምት ሳይጠቀም ቀርቷል።

ሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች መደበኛውን የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ጨዋታቸውን 0ለ0 በሆነ አቻ ውጤት አጠናቀዋል።

የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታውን ከስፔን ብሔራዊ ቡድን ጋር የሚያደርግ ይሆናል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
መልካም ዕድል!
ከፍ የተደረጉ ኦዶችን አይተዋል ? እንግዲያውስ ተወራረዱባቸው!
England - Switzerland
Netherlands - Turkey
ለተሻለ ውርርድ ቤቲካን ይጠቀሙ! አሁኑኑ Betika.et ላይ /በቴሌግራም ቦታችን - @BetikaETBot ይወራረዱ!
Forwarded from HEY Online Market
Play More and Spend less!

•PS4 Slim, 34,999 Birr
•PS4 PRO, 41,999 Birr
•Original Controller 6,499 Birr

Contact Us
0953964175 @heymobile

@heyonlinemarket
" ከውድድሩ መውጣታችን ያማል " ኔግልስማን

የጀርመን ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ጁሊያን ኔግልስማን ቡድኑ በስፔን ተሸንፎ ከአውሮፓ ዋንጫ ውድድር መውጣቱ " የሚያም ነበር " ሲሉ ገልጸዋል።

" በድጋሜ በምናዘጋጀው ውድድር የመሳተፍ እድል የምናገኝ አይመስለኝም " ያሉት አሰልጣኙ ከውድድሩ መውጣታችን ያማል አጨዋወታችን መጥፎ ቢሆን እንቀበለው ነበር ነገርግን ጥሩ ነው የተጫወትነው ሲሉ ተናግረዋል።

የቡድኑ የመጨረሻ ጨዋታውን ያደረገው ቶኒ ክሩስ በበኩሉ " ሁላችንም ያለምነው ህልም ቀርቷል ፣ ያለንን ሁሉ ሰጥተናል በዚህም ኩራት ይሰማናል።

ለጀርመን እግርኳስ በድጋሜ ተስፋ ሰጥተነዋል ነገርግን ከውድድሩ መውጣታችን ቅር አሰኝቶናል።"ሲል ተናግሯል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የኢትዮጵያን ፕርሚየር ሊግ ማን ያሳካል ?

የሊጉን አሸናፊ እስከ መጨረሻው ጨዋታ ያላሳወቀው የዘንድሮው የ2016 የኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ ውድድር በዛሬው ዕለት ከሚደረጉ ተጠባቂ ጨዋታዎች በኋላ አሸናፊውን ይለያል።

ፕርሚየር ሊጉን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በስልሳ አንድ ነጥቦች እና በሀያ ስምንት ንፁህ ግቦች በበላይነት እየመራው ይገኛል።

መቻል በበኩሉ ከሊጉ መሪ በአንድ ነጥብ ዝቅ ብሎ በስልሳ ነጥቦች እና በአስራ ዘጠኝ ንፁህ ግቦች ሁለተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል።

በሊጉ የመጨረሻ ሳምንት መርሐግብር ዛሬ ቀን 10:00 ሰዓት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከ ኢትዮጵያ መድን እንዲሁም መቻል ከ ድሬዳዋ ከተማ በተመሳሳይ ሰዓት የሚጫወቱ ይሆናል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጨዋታውን ማሸነፍ በቀጥታ የሊጉ ሻምፒዮን ሲያደርገው ነጥብ የሚጥል ወይም የሚሸነፍ ከሆነ እና መቻሎች የሚያሸንፉ ከሆነ ሊጉን ማሳካት ይችላሉ።

የኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ ውድድር አሸናፊውን በመጨረሻ ሳምንት ጨዋታ ሲለይ በውድድሩ ታሪክ ይህ ለስምንተኛ ጊዜ መሆኑ ተገልጿል።

Video Credit - Haileegziabher Adhanom

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
" የኢትዮጵያ ህዝብ እንዲፈርደኝ እፈልጋለሁ " ፍሬወይኒ ሀይሉ

ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ፍሬወይኒ ሀይሉ ያለአግባብ በፓሪስ ኦሎምፒክ ውድድር ተሳታፊ አትሌቶች ዝርዝር ውስጥ ሳልካተት ቀርቻለሁ ስትል ቅሬታዋን ህዝብ ይወቅልኝ በማለት ገልፃለች።

በ1500 እና 5000 ሜትር ተወዳዳሪ መሆኗን ያስታወሰችው አትሌት ፍሬወይኒ ሀይሉ በአመቱ ውስጥ በሁለቱም ርቀቶች ከሌሎች አትሌቶች የተሻለ ውጤት አስመዝግቤ ነበር ትላለች።

አትሌቷ በ2024 የቤት ውስጥ ሻምፒዮና በ1500ሜ ወርቅ እና የተሻለ ሰዓት እንዲሁም በ5000ሜ የ2024 የአለም ምርጥ 3ኛ ሰዓት ባስመዘግብም ከሁለቱም ርቀቶች ከኦሎምፒክ ውጪ ሆኛለሁ ብላለች።

አትሌት ፍሬወይኒ ሀይሉ ቀጥላም " እኔ በዚህ አመት የተሻለ ሰዓት ባስመዘግብም ከአመት በፊት ጥሩ ውጤት ያላቸው አትሌቶች ተመርጠው እኔ ቀርቻለሁ የኢትዮጵያ ህዝብ ይወቅልኝ።

በ2024 ምንም ውድድር ሳይወዳደሩ የ2023 አላቸው ተብሎ መምረጥ አግባብ አይደለም ለምን በሀቀኝነት አይመረጥም ምንም ሳይሮጡ እየተመረጡ ነው እኛ ግን ደክመንም እየቀረን ነው።

የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ እና አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለምንድን ነው የእኛን ማየት የማይችለው በዚህ ላይ ማብራሪያም እፈልጋለሁ።"ስትል ተናግራለች።

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በትላንትናው ዕለት ኢትዮጵያን በኦሎምፒክ የሚወክሉ አትሌቶችን ይፋ ሲያደርግ አትሌት ፍሬወይኒ ሀይሉ የ5000ሜ ተጠባባቂ ሆና ተመርጣለች።

ምንጭ - ሀገሬ ቴሌቪዥን

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ዌስትሀም ዩናይትድ ተጨዋች አስፈረሙ !

ዌስትሀም ዩናይትድ እንግሊዛዊውን የተከላካይ ስፍራ ተጨዋች ማክስ ኪልማን ከዎልቭስ ማስፈረማቸውን ይፋ አድርገዋል።

ዌስትሀም ለተጨዋቹ ዝውውር 40 ሚልዮን ፓውንድ ወጪ ማድረጋቸው ሲነገር ተጨዋቹ በክለቡ የሰባት አመት ኮንትራት መፈረሙ ተገልጿል።

" ዌስትሀም እንደሚፈልገኝ ሳውቅ ለመቀላቀል ፈልጊያለሁ ፣ ዌስትሀም ትልቅ ክለብ ነው የእግርኳስ ህይወቴ አንድ እርምጃ እንዳደገ ይሰማኛል።"ሲል ማክስ ኪልማን ተናግሯል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
አዲዳስ የጫማ ምርቱን ስያሜ በክሩስ ስም ሰየመ !

እውቁ የትጥቅ አምራች ተቋም አዲዳስ ቶኒ ክሩስ በብቸኝነት እስካሁን እየተጠቀመው የሚገኘውን " adidas 11pro " ጫም ስያሜ በክሩስ ስም መቀየሩን ይፋ አድርጓል።

በዚህም መሰረት የእግርኳስ መጫወቻ ጫማ ምርቱ ስያሜ ከዚህ በኋላ " Toni Kroos Pro boots " ተብሎ እንደሚጠራ ተገልጿል።

ጀርመናዊው ታሪካዊ ተጨዋች ቶኒ ክሩስ ባለፉት አስራ ሶስት አመታት ተመሳሳይ የአዲዳስ " adidas 11pro " ምርት የሆነ ጫማን ሲጠቀም እንደነበር ይታወቃል።

ቶኒ ክሩስ በቀድሞው የአዲዳስ " adidas 11pro " ምርት የሆነ ጫማ እየተጫወተ የሚያሻማቸው ኳሶች ትክክለኛነታቸው ከ90% በላይ እንደነበር ተገልጿል።

ስኬታማ የእግርኳስ ህይወት ማሳለፍ የቻለው ቶኒ ክሩስ ከእግርኳስ አለም ራሱን ማግለሉ አይዘነጋም።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
" አላማችን ሊጉን ማሸነፍ መሆን አለበት " አርኔ ስሎቶ

የመርሲሳይዱ ክለብ ሊቨርፑል ዋና አሰልጣኝ አርኔ ስሎት በሚቀጥለው የውድድር አመት አላማቸው የእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ ዋንጫን ማሳካት እንደሆነ ገልጸዋል።

" በቀጣይ አላማችን እና ሙሉ ትኩረታችን የፕርሚየር ሊጉን ዋንጫ ማሳካት ላይ መሆን አለበት " የሚሉት አሰልጣኝ አርኔ ስሎት ይህ ማድረግ የምንፈልገው ነገር ነው የሊጉ የበላይ መሆን እንፈልጋለን ብለዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ቶኒ ክሩስ ፔድሪን ይቅርታ ጠይቋል !

ጀርመናዊው የመሐል ሜዳ ተጨዋች ቶኒ ክሩስ ትላንት በስፔን በተሸነፉበት ጨዋታ ፔድሪ ላይ ለሰራው ጥፋት በማህበራዊ ትስስር ገፁ ተጫዋቹን ይቅርታ ጠይቋል።

" ፔድሪ ጉዳት እንዲያጋጥመው ሆንብዬ አስቤ አልነበረም ጥፋቱን የሰራሁት " ያለው ቶኒ ክሩስ ይቅርታ ማለት እና ቶሎ እንድትመለስ መመኘት እፈልጋለሁ አንተ ምርጥ ተጨዋች ነህ።"ሲል ተናግሯል።

በጨዋታው ፔድሪ ባጋጠመው ከባድ ጉዳት ምክንያት ተቀይሮ ለመውጣት መገደዱ የሚታወስ ሲሆን በቀጣይ በአውሮፓ ዋንጫ ጨዋታዎች ይሳተፋል ተብሎ አይጠበቅም።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
2024/09/30 12:35:22
Back to Top
HTML Embed Code: