Telegram Web Link
" በስፔን ጨዋታ የታክቲክ ለውጥ እናደርጋለን " ሉቺያኖ ስፓሌቲ

የጣልያን ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ሉቺያኖ ስፓሌቲ ቡድናቸው ትላንት ምሽት ባስመዘገበው ድል ቢደሰቱም ያደረገው እንቅስቃሴ የሚደነቅ አለመሆኑን ከጨዋታው በኋላ ገልጸዋል።

አሰልጣኙ ከጨዋታው በኋላ በሰጡት አስተያየትም " ጨዋታውን በትክክል ተጫውተናል እውነት ነው ነገርግን ውጤቱ የሁለቱን ቡድኖች ልዩነት አያሳይም ፣ በመጨረሻ ሰዓት የአቻነት ግብ ለማስተናገድ ተቃርበን ነበር።"ብለዋል።

በቀጣይ ከስፔን ጋር ለሚያደርጉት ጨዋታ የታክቲክ ለውጥ ሊያደርጉ እንደሚችሉ የጠቆሙት አሰልጣኝ ሉቺያኖ ስፓሌቲ " ስፔን ከአልባንያ በተለየ መልኩ ታዘጋጀናለች።

ከአልባንያ ጋር ካደረግነው በተሻለ ኳሱን ማፍጠን አለብን ከስፔን ጋር በብዛት ኳስ ወደፊት በመውሰድ እና ከተከላካይ ጀርባ መጫወት እንፈልጋለን።"ብለዋል።

ጣልያን በድጋሜ የአውሮፓ ዋንጫውን ታሳካ እንደሆነ የተጠየቁት ሉቺያኖ ስፓሌቲ " ወሳኙ የምናሳየው ብቃት ነው ፣ የእግርኳሳችን ብራንድ እና ቡድናችን ይጠቅመናል።"ሲሉ መልሰዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ባየር ሙኒክ የተጫዋቹን ውል አራዝሟል !

የጀርመን ቡንደስሊጋው ክለብ ባየር ሙኒክ የመሐል ሜዳ ተጨዋቻቸው አሌክሳንደር ፓቭሎቪችን ኮንትራት ለተጨማሪ አመታት ማራዘማቸውን ይፋ አድርገዋል።

ጀርመናዊው የመሐል ሜዳ ተጨዋች አሌክሳንደር ፓቭሎቪች በባየር ሙኒክ ቤት እስከ 2029 የሚያቆየውን የአምስት አመት ውል መፈረሙ ይፋ ሆኗል።

አሌክሳንደር ፓቭሎቪች ውሉን ካራዘመ በኋላ በሰጠው አስተያየት " ባየር ሙኒክ ልቤ ውስጥ ያለ ክለብ ነው እዚህ በመሆኔ ኩራት እና ደስታ ይሰማኛል ፣ ከቡድኑ ጋር ዋንጫዎችን ማሸነፍ እፈልጋለሁ።"ብሏል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ጋሪዝ ሳውዝጌት የቡድን መሪዎችን አቋቁመዋል !

የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ጋሪዝ ሳውዝጌት በብሔራዊ ቡድኑ ስብስብ ውስጥ " የቡድን መሪዎች " ማቋቋማቸው ተገልጿል።

አሰልጣኙ በስብስቡ ውስጥ ባቋቋሙት የቡድን መሪዎች ውስጥ ሀሪ ኬን ፣ ካይል ዎከር ፣ ጁድ ቤሊንግሀም እና ዴክላን ራይስ መካተታቸው ተነግሯል።

አሰልጣኝ ጋሪዝ ሳውዝጌት የቡድን መሪዎችን ያቋቋሙት በቡድኑ ውስጥ ያለውን ሁኔታ በደንብ ለመረዳት እና ከወጣት ተጨዋቾች ጋር በደንብ ለመግባባት መሆኑ ተገልጿል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
" የአውሮፓ ዋንጫውን እንደምናሸንፍ እናምናለን " ፓልመር

የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን የፊት መስመር ተጨዋች ኮል ፓልመር እንግሊዝ የዘንድሮውን የአውሮፓ ዋንጫ ውድድር ማሸነፍ እንደምትችል ተናግሯል።

" የቡድን ስብስባችን ድንቅ ነው " ሲል የገለጸው ኮል ፓልመር " እኛ የአለም ምርጥ ተጨዋቾች አሉን የአውሮፓ ዋንጫውን እንደምናሸንፍ አምናለሁ እኛ የተሻለ የማሸነፍ እድል ያለን ይመስለኛል።"ብሏል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ቫን ዳይክ የሜዳው ጥራት እንዳሰጋው ገለጸ !

የኔዘርላንድ ብሔራዊ ቡድን አምበል ቨርጅል ቫን ዳይክ ቡድናቸው ዛሬ ከፖላንድ ጋር ጨዋታውን የሚያደርግበት ስታዲየም ጥራት እንዳሰጋው አስተያየቱን ሰጥቷል።

" ጨዋታችንን የምናደርግበት ስታዲየም ጥሩ አይመስለኝም ፣ ነገርግን በፍጥነት ልንላመደው ይገባል ተጋጣሚያችንንም እንደዛው።" ሲል ቫን ዳይክ ተናግሯል።

ስለ ዋንጫው አሸናፊነት ያነሳው ቨርጅል ቫን ዳይክ " እንግሊዝ በጣም ጥሩ ቡድን ናቸው ፣ ፈረንሳይ እና ጀርመንም እንደዛው እኛ ከዋንጫ ተፎካካሪዎች ውስጥ እንደምንሆን ተስፋ አደርጋለሁ።"ብሏል።

ኔዘርላንድ ዛሬ ቀን 10:00 ከፖላንድ ጋር ሃምቡርግ ከተማ በሚገኘው የጀርመን ሁለተኛ ሊጉ ክለብ ሀምቡርገር ስታዲየም ቮልክስፓርክስታዲዮን የሚጫወቱ ይሆናል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
#EURO2024

ኔዘርላንድ ከፖላንድ ጋር ዛሬ ቀን 10:00 ለሁለቱም ሀገራት በቅርብ ርቀት ላይ በሚገኘው የጀርመኑ ሃምቡርግ ከተማ የአውሮፓ ዋንጫ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።

ጨዋታው የሚደረግበት ከተማ ለሁለቱም ሀገራት አማካይ ቦታ ላይ መሆኑ በርካታ ደጋፊዎች በከተማዋ እንዲገኙ እና የምድብ ጨዋታውን ከሌሎች በተለየ መልኩ ደማቅ እንዲሆን አድርጎታል።

የምድብ ጨዋታው የሚደረግበት የጀርመኑ ሃምቡርግ ከተማ ከኔዘርላንድ ድንበር 200 ኪ.ሜ እንዲሁም ከፖላንድ ድንበር 300 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ይገኛል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
Forwarded from WANAW SPORT
#ዋናው ስፖርት ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለዒድ አል አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ ይላል፡፡

ዒድ ሙባረክ!


Instagram | Facebook | TikTok

🏅 ዋናው ወደፊት...

@wanawsportwear
መልካም ዕድል!
ከፍ የተደረጉ ኦዶችን አይተዋል ? እንግዲያውስ ተወራረዱባቸው!
Poland - Netherlands
Serbia - England
ለተሻለ ውርርድ ቤቲካን ይጠቀሙ! አሁኑኑ Betika.et ላይ /በቴሌግራም ቦታችን - @BetikaETBot ይወራረዱ!
የቡናማዎቹ ታዳጊዎች ሻምፒዮን ሆነዋል !

የኢትዮጵያ ቡና ከ 20ዓመት በታች ቡድን ከመቻል አቻው ጋር ያደረገውን U-20 የኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ ፍፃሜ ጨዋታ በማሸነፍ ሻምፒዮን ሆነዋል።

የኢትዮጵያ ቡና ታዳጊዎች ከመቻል ታዳጊዎች ጋር ያደረጉት የፍፃሜ ጨዋታ መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ 0ለ0 መጠናቀቁን ተከትሎ በተሰጠ መለያ ምት ቡናማዎቹ ባለድል ሆነዋል።

የዘንድሮውን የኢትዮጵያ ከ 20ዓመት በታች ፕርሚየር ሊግ ውድድር መቻል ሁለተኛ እንዲሁም ኢትዮ ኤሌክትሪክ ሶስተኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
የጨዋታ አሰላለፍ !

10:00 ፖላንድ ከ ኔዘርላንድ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
#EURO2024

ኔዘርላንድ ከፖላንድ ጋር ከሚያደርጉት ጨዋታ በፊት በስታዲየሙ አካባቢ በተፈጠረ ክስተት አንድ ግለሰብ ስለታማ እና ተቀጣጣይ ነገሮችን ይዞ ፖሊሶችን ሲያስፈራራ እንደነበር ተገልጿል።

ግለሰቡ በአካባቢው በነበረ የፖሊስ የፀጥታ አካል በጥይት የመመታት የሀይል እርምጃ እንደተወሰደበት የአካባቢው ፖሊስ አስታውቋል።

ግለሰቡ አሁን ላይ በተወሰደበት የሀይል እርምጃ መቁሰሉ እና የህክምና እርዳታ እየተደረገለት መሆኑን የአካባቢው ፖሊስ ጨምሮ ገልጿል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
#EURO2024

አሰልጣኝ ሮናልድ ኮማን ከደቂቃዎች በኋላ በሚጀመረው ጨዋታ በቀኝ መስመር ላይ የማጥቃት ባህሪ ካለው የባየር ሌቨርኩሰኑ ፍሪምፖንግ ይልቅ የመከላከል ባህሪ ያለውን ዴንዜል ዱምፍሪሴን ምርጫቸው አድርገዋል።

ኔዘርላንድ በጨዋታው በፊት መስመሩ ዌግሆርስት ፣ ማለን እና ጆሽዋ ዝርኪዜ እንዲሁም በአማካይ ስፍራ ዊናልደም እና ግራቨንበርች የመሳሰሉ ተጨዋቾችን በተጠባባቂነት አሳልፋለች።

በጉዳት ምክንያት ከጨዋታው ውጪ በሆነው ሮበርት ሌዋንዶውስኪ ምትክ አዳም ቡክሳ የፖላንድን የፊት መስመር ይመራል።

የ 27ዓመቱ ተጨዋች አዳም ቡክሳ በቱርኩ ክለብ አንታላይስፑር ያሳለፈው ጥሩ የውድድር እንዲሁም በብሔራዊ ቡድኑ ያለው ጥሩ ሪከርድ የሌዋንዶውስኪ ትክክለኛ ምትክ ሆኖ አቅርቦታል።

ሮበርት ሌዋንዶውስኪ ከጨዋታው ውጪ መሆኑን ተከትሎ ፒዮትር ዜሊንስክ ፖላንድን በአምበልነት እየመራ ወደ ሜዳ ይገባል።

" ሌዋንዶውስኪ ሊያግዘን ባለመግባቱ በጣም ያሳዝናል እሱ ታላቅ ተጨዋች ቢሆንም እኔም ሆንኩ ጓደኞቼ ጨዋታውን ለማሸነፍ ያለንን እንሰጣለን።"ሲል የናፖሊው ተጨዋች ፒዮትር ዜሊንስክ ተናግሯል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
" ሁሉም እንድንሸነፍ ፈርዶብናል "

የፖላንድ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ሚቻል ፕሮቤርዝ አሁን ላይ ሁሉም ሰው ፖላንድ በኔዘርላንድ ትሸነፋለች ብሎ እያወራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

" ሁሉም ሰው እንድንሸነፍ ፈርዶብናል " ያሉት አሰልጣኙ ሰዎች እንደሚያስቡት ከሆነ እኛ ምንም የማሸነፍ እድል የለንም ነገርግን እኔ ዋና ነገር ቡድን መገንባት ነው ብዬ አስባለሁ እርስበርስ የሚሰራ ቡድን።"ሲሉ ተደምጠዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
15 ' ፖላንድ 1 - 0 ኔዘርላንድ

ቡክሳ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
29 ' ፖላንድ 1 - 1 ኔዘርላንድ

ቡክሳ ጋክፖ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
እረፍት | ፖላንድ 1 - 1 ኔዘርላንድ

    ቡክሳ      ጋክፖ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ወላይታ ድቻ ድል አድርጓል !

በኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ የሀያ ሰባተኛ ሳምንት መርሐ ግብር ወላይታ ድቻ ከሀድያ ሆሳዕና ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 2ለ1 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችለዋል።

የወላይታ ድቻን የማሸነፊያ ግቦች አብነት ደምሴ እና ብሩክ ማርቆስ በራሱ ግብ ላይ ከመረብ ሲያሳርፉ ለሀድያ ሆሳዕና ተመስገን ብርሀኑ አስቆጥሯል።

ወላይታ ድቻ ካለፉት አስራ አራት የሊግ ጨዋታዎች ሁለተኛ ድላቸውን አሳክተዋል።

የሊጉ ደረጃ ሰንጠረዥ ምን ይመስላል ? 

1️⃣0️⃣ ሀድያ ሆሳዕና :- 35 ነጥብ

1️⃣3️⃣ ወላይታ ድቻ  :- 32 ነጥብ

ቀጣይ ጨዋታ ምን ይመስላል ?

- ድሬዳዋ ከተማ ከ ሀድያ ሆሳዕና

- ሀምበሪቾ ዱራሜ ከ ወላይታ ድቻ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
83 " ፖላንድ 1 - 2 ኔዘርላንድ

    ቡክሳ      ጋክፖ
ዌግሆርስት

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ኔዘርላንድ ውድድሯን በድል ጀምራለች !

በአውሮፓ ዋንጫ የምድብ የመጀመሪያ ጨዋታ የኔዘርላንድ ብሔራዊ ቡድን ከፖላንድ ብሔራዊ ቡድን ጋር ያደረገውን ጨዋታ 2ለ1 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችሏል።

ለኔዘርላንድ ብሔራዊ ቡድን የማሸነፊያ ግቦችን ኮዲ ጋክፖ እና ዎት ዌግሆርስት ከመረብ ማሳረፍ ችሏል።

ለፖላንድ ብሔራዊ ቡድን የመሪነት ግብ አዳም ቡክሳ ከመረብ አሳርፏል።

የሊቨርፑሉ የፊት መስመር ተጨዋች ኮዲ ጋክፖ ለኔዘርላንድ ብሔራዊ ቡድን አስረኛ ግቡን ከመረብ ማሳረፍ ችሏል።

ዎት ዌግሆርስት ለኔዘርላንድ ብሔራዊ ቡድን ተቀይሮ በገባባቸው አስራ አንድ ጨዋታዎች ሰባት ግቦች አስቆጥሯል።

በምድቡ ሁለተኛ ጨዋታ ቀጣይ ሳምንት አርብ ኔዘርላንድ ከፈረንሳይ እንዲሁም ፖላንድ ከኦስትሪያ ጋር ይገናኛሉ።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
2024/06/30 19:21:23
Back to Top
HTML Embed Code: