Telegram Web Link
" ቀጣዩ የሲቲ አላማ ለአምስተኛ ጊዜ ማሸነፍ ነው "

የማንችስተር ሲቲው ሊቀመንበር ኸልዱን አል ሙባረክ በክለቡ የውድድር አመት ሁኔታ ዙሪያ በክለቡ ሚዲያ ቃለ ምልልስ አድርገው ነበር።

ሊቀመንበሩ በቃለ ምልልሳቸው የማንችስተር ሲቲን ያለፉት አመታት ስኬትን ጨምሮ የተለያዩ ጉዳዮችን አንስተዋል።

ከእነዚህም መካከል :-

- " የፕርሚየር ሊግ ዋንጫውን እንደምናሸንፍ ያወቅኩት ነሀሴ ወር ላይ ከአርሰናል ጋር ኤምሬትስ ስታዲየም በተሸነፍንበት ጨዋታ ነው።

- በቀጣይ የውድድር አመት የማንችስተር ሲቲ አላማ የሚሆነው የፕርሚየር ሊግ ዋንጫውን ለተከታታይ አምስተኛ ጊዜ ማሸነፍ ነው።

- በእንግሊዝ እግርኳስ ታሪክ ባለፉት መቶ አመታት ውስጥ ሊጉን ለተከታታይ አራት ጊዜ ማሸነፍ የቻለ ክለብ የለም ይህንን ስታውቅ ማንችስተር ሲቲን ማድነቅ ትጀምራለህ።

- ስለ ፔፕ ጋርዲዮላ ቆይታ በጋራ የምንወስነው ውሳኔ ነው የሚሆነው ለእኛም ለጋርዲዮላም የሚስማማ ውሳኔ እንወስናለን።

- የቀረቡብን 115 ክሶች የሚያበሳጩ ናቸው ነገርግን ሰዎች በክስ ሂደቱ ሳይሆን ከመጨረሻው ውሳኔ በኋላ በእኛ ላይ እንዲፈርዱ እንፈልጋለን የመጨረሻው ፍርድ እስከሚታወቅ ረጅም ጊዜ ይወስዳል።

- በፕርሚየር ሊጉ ባለፉት አመታት በእኛ ደረጃ የሚገኝ ቡድን ፈልገህ ማግኘት አትችልም።" ሲሉ ተደምጠዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
Forwarded from WANAW SPORT
🔊 #ሁለት ቀናት ብቻ ቀሩት

⚽️ ለእግር ኳስ ቡድንዎ ልዩ የሽያጭ ብስራት ⚽️

🔥 #እንዳያመልጥዎ፣ ዛሬውኑ ይዘዙን!

📌 ለበለጠ መረጃና ትዕዛዝ 📲 09011382830910851535 እና 0913586742 ላይ ይደውሉ።

👉🏾 እንዲሁም በቴሌግራም @Wanawsales ላይ የሽያጭ ሰራተኞቻችንን በቀጥታ በማናገር ወይም በቴሌግራም ቦት @WANAWSbot በኩል ይዘዙን።

Instagram | Facebook | TikTok

🏅 ዋናው ወደፊት...

@wanawsportwear
ሽመልስ በቀለ 1⃣8⃣ ገስት ሀውስ

በውቢቷ ሀዋሳ ቆይታዎ የት ለማረፍ አስበዋል ? ንፁህ እና በደንበኞቻችን ተወዳጅ በሆነው የእንግዳ ማረፊያችን መጥተው የእረፍት ጊዜውን ያሳልፉ።

እንግዶቻችንን ተቀበልን ለእይታ ሳቢ በሆነው የእንግዳ ማረፊያችን ማስተናገድ ከጀመርን አመታትን አስቆጥረናል።

አድራሻችን :- ሀዋሳ አርቴፍሻል ስታዲየም መንገድ ላይ ያገኙናል።

ለተጨማሪ መረጃ እና ለትዕዛዝዎ ይደውሉልን :- 0928684848

#ShemelesBekele18
TIKVAH-SPORT
ኦማሪ ፎርሰን ዩናይትድን ሊለቅ ነው ! የማንችስተር ዩናይትዱ ወጣት የፊት መስመር ተጨዋች ኦማሪ ፎርሰን በዚህ ክረምት ኮንትራቱ ሲጠናቀቅ ክለቡን ሊለቅ መሆኑ ተገልጿል። በቅርቡ ለዋናው ቡድን ተሰልፎ በመጫወት ጥሩ እንቅስቃሴ ማሳየት የቻለው ኦማሪ ፎርሰን በነፃ ዝውውር ማንችስተር ዩናይትድን እንደሚለቅ ተነግሯል። የ 19ዓመቱን የፊት መስመር አጥቂ ኦማሪ ፎርሰንን በነፃ ዝውውር ለማስፈረም በርካታ…
ጆኒ ኢቫንስ በዩናይትድ ሊቆይ ነው !

ማንችስተር ዩናይትድ የተከላካይ ስፍራ ተጨዋቹን ጆኒ ኢቫንስ ኮንትራት ለተጨማሪ አመት ለማራዘም ንግግር ላይ መሆናቸውን አስታውቀዋል።

እንግሊዛዊው ግብ ጠባቂ ቶም ሂተን በተመሳሳይ ውሉን ለማራዘም ከክለቡ ጋር በንግግር ላይ መሆናቸው ተዘግቧል።

የክለቡ አካዳሚ ውጤት የሆነው ብራንደን ዊሊያምስ በበኩሉ ከክለቡ ጋር ከአመታት በኋላ መለያየቱ ይፋ ተደርጓል።

ማንችስተር ዩናይትድን ሊለቅ እንደሚችል ሲነገር የቆየው የፊት መስመር ተጨዋቹ ኦማሪ ፎርሰን በበኩሉ አዲስ ኮንትራት እንደቀረበለት ተገልጿል።

ይሁን እንጂ የ 19ዓመቱን የፊት መስመር አጥቂ ኦማሪ ፎርሰን የቀረበለትን ኮንትራት ውድቅ በማድረግ ክለቡን ሊለቅ እንደሚችል ተነግሯል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ጁድ ቤሊንግሀም የአመቱ ምርጥ ተጨዋች ተባለ !

እንግሊዛዊው የመሐል ሜዳ ተጨዋች ጁድ ቤሊንግሀም የሪያል ማድሪድ የደጋፊዎች የአመቱ ምርጥ ተጨዋች በመሆን መመረጥ ችሏል።

ጁድ ቤሊንግሀም ሎስ ብላንኮዎቹ የላሊጋ ፣ ሻምፒየንስ ሊግ እና ስፔን ሱፐር ካፕ ዋንጫን ሲያሳኩ ሀያ ሶስት ግቦችን በማስቆጠር ለቡድኑ ጥሩ የሚባል ግልጋሎት መስጠት ችሏል።

" በመጀመሪያ አመቴ ይህንን ሽልማት በማሸነፌ ኩራት ተሰምቶኛል የመረጡኝን ደጋፊዎች ሁሉ አመሰግናለሁ።"ሲል ቤሊንግሀም ከሽልማቱ በኋላ ተናግሯል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
የሊቨርፑል የአመቱ ምርጥ ተጨዋች ታውቋል !

የመርሲሳይዱ ክለብ ሊቨርፑል የ2023/24 የውድድር አመት የደጋፊዎች የውድድር ዘመኑ ምርጥ ተጨዋች ይፋ አድርገዋል።

በዚህም መሰረት ግብፃዊው የፊት መስመር ተጨዋች መሐመድ ሳላህ የሊቨርፑል የውድድር ዘመኑ የደጋፊዎች ምርጥ ተጨዋች በመሆን በአብላጫ ድምፅ መመረጥ ችሏል።

መሐመድ ሳላህ በሊቨርፑል ቤት ባሳለፋቸው ሰባት አመታት የአመቱ ምርጥ ተጨዋች ተብሎ ሲመረጥ ለአራተኛ ጊዜ መሆኑ ተገልጿል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ዊሊያም ሳሊባ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ አጠናቋል !

ፈረንሳዊው የተከላካይ ስፍራ ተጨዋች ዊሊያም ሳሊባ የተጠናቀቀው የውድድር አመት የአርሰናል የአመቱ ምርጥ ተጨዋች ሽልማትን በሶስተኝነት ማጠናቀቅ ችሏል።

ዊሊያም ሳሊባ ከተሰጠው አጠቃላይ ድምፅ ሀያ በመቶውን በማግኘት ሶስተኛ ደረጃን ይዞ ማጠናቀቁ ተገልጿል።

በቀጣይ የዘንድሮው የውድድር አመት የአርሰናል የአምቱ ምርጥ ተጨዋች እና ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ ያጠናቀቀው ተጨዋች ይፋ ይደረጋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
የኤፌ ካፕ የአመቱ ምርጥ ተጨዋች ታውቋል !

በማንችስተር ዩናይትድ አሸናፊነት የተጠናቀቀው የዘንድሮው የ2023/24 የውድድር አመት የእንግሊዝ ኤፌ ካፕ ውድድር የውድድሩ ምርጥ ተጨዋች ይፋ ተደርጓል።

በዚህም መሰረት እንግሊዛዊው የማንችስተር ዩናይትድ የመሐል ሜዳ ተጨዋች ኮቢ ማይኖ የእንግሊዝ ኤፌ ካፕ ምርጥ ተጨዋች ተብሎ በአብላጫ ድምፅ መመረጥ ችሏል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
የሊጉ ክለቦች ቫር እንዲቀር ድምፅ ሊሰጡ ነው ! የእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ ክለቦች ከሚቀጥለው የውድድር አመት ጀምሮ ቫር ከሊጉ እንዲቀር ድምፅ ሊሰጡ መሆኑ ተገልጿል። ሀሳቡን ዎልቭስ ማምጣቱ እና ክለቦቹ በሚቀጥለው ወር በሚያደርጉት አመታዊ ስብሰባ ላይ በአጀንዳነት በመያዙ ድምፅ ለመስጠት መስማማታቸው ተነግሯል። በድምፅ አሰጣጥ ሂደቱ ውስጥ ከሀያው ክለቦች መካከል አስራ አራቱ ከተስማሙ ቫር በሚቀጥለው…
የሊጉ ክለቦች በቫር ዙሪያ ነገ ድምፅ ይሰጣሉ !

የእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ ክለቦች ከሚቀጥለው የውድድር አመት ጀምሮ #ቫር ከሊጉ እንዲቀር በዎልቭስ በቀረበው ሀሳብ ላይ ነገ በሚኖራቸው አመታዊ ስብሰባ ድምፅ ይሰጣሉ።

ይሁን እንጂ አብዛኞቹ የእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ ክለቦች ሀሳቡን አለመቀበላቸው እና ቫር እንዲቀጥል እንደሚፈልጉ የሀገሪቱ መገናኛ ብዙሀን ዘግበዋል።

ማንችስተር ሲቲ ፣ አርሰናል እና ቶተንሀም ቫር እንዲቀጥል ከሚፈልጉ ክለቦች ጎራ እንደሆኑ መታወቁ ተጠቁሟል።

በድምፅ አሰጣጥ ሂደቱ ውስጥ ከሀያው ክለቦች መካከል አስራ አራቱ ከተስማሙ ቫር በሚቀጥለው አመት ተግባራዊ እንደማይሆን ተዘግቧል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ሚሎስ ኬርኬዝ ወደ ማንችስተር ዩናይትድ ?

ማንችስተር ዩናይትድ በክረምቱ የተጨዋቾች የዝውውር መስኮት የግራ መስመር ተጨዋች ለማስፈረም ወደ ዝውውር ገባያው እንደሚገቡ ተነግሯል።

ቀያዮቹ ሴጣኖች በተጨማሪም በዚህ ክረምት የመሐል ተከላካይ እና የፊት መስመር አጥቂ ለማስፈረም ቅድሚያ ሰጥተው እንደሚሰሩ ይጠበቃል።

ማንችስተር ዩናይትድ ለማስፈረም ከተመለከቷቸው የግራ መስመር ተጨዋቾች አንዱ የበርንማውዙ ተጨዋች ሚሎስ ኬርኬዝ አንዱ መሆኑ ተገልጿል።

ይሁን እንጂ ማንችስተር ዩናይትድ እስካሁን ሀንጋራዊውን ተጫዋች ሚሎስ ኬርኬዝ ለማስፈረም ንግግር አለመጀመሩ ተዘግቧል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ሮናልዶ የወሩ ምርጥ ተጨዋች ተብሏል !

በአል ሂላል አሸናፊነት የተጠናቀቀው የሳውዲ ሮሽን ሊግ የ2023/24 የውድድር አመት የወርሀ ግንቦት የወሩ ምርጥ ተጨዋች ይፋ ተደርጓል።

በዚህም መሰረት ፖርቹጋላዊው የአል ናስር የፊት መስመር ተጨዋች ክርስቲያኖ ሮናልዶ የሳውዲ ሊግ የግንቦት ወር ምርጥ ተጨዋች በመሆን በአብላጫ ድምፅ መመረጥ ችሏል።

ክርስቲያኖ ሮናልዶ በዘንድሮው የውድድር ዘመን ለአምስተኛ ጊዜ የሳውዲ ሊግ የወሩ ምርጥ ተጫዋች በመባል መመረጥ ችሏል።

የአምስት ጊዜ ባሎን ዶር አሸናፊው ተጨዋች ክርስቲያኖ ሮናልዶ በተጠናቀቀው የውድድር አመት ባደረጋቸው ሰላሳ አንድ የሊጉ ጨዋታዎች ሰላሳ አምስት ግቦች ማስቆጠር ችሏል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
Stock Clearance Discount

📞 0925927457 @eBRO4
📞
0953964175 @heymobile

• iPhone X, White, 256 GB/ 100%    
   19,000 ETB
• iPhone Max, White, 64GB/ 89%     
   24,000 ETB
• iPhone Max, Black, 256 GB/ 89%
   28,000 ETB
• iPhone Max, Golden, 256 GB/ 92%
   29,000 ETB
• iPhone 11,  Red,  64 GB/ 75%  
   27,000 ETB
• iPhone 11, Black, 128 GB/ 91%  
   33,000 ETB
• iPhone 11 Pro, Black, 64 GB/ 63%
   35,000 ETB
• iPhone 11 Pro, Black, 256 GB/88%  
  39,000 ETB
•11 Pro Max, Black, 64 GB/ 77%  
  36,000 ETB
• iphone 12 mini, Red, 64 GB/ 98%  
  22,000 ETB
• iPhone 12 Pro, Blue, 128 GB/ 83%  
   47,000 ETB
• iPhone 12 Pro, Blue, 128 GB/ 89% 
  48,000 ETB
• iPhone 12 Pro, Black,256 GB/ 85%  
   51,000 ETB
• 12 Pro Max, Golden, 128 GB/ 85%
   59,000 ETB
• 12 Pro Max, Blue, 128 GB/ 86%
   43,000 ETB ⚠️

Exchange Available!
Free Delivery 🚚

@heyonlinemarket
❇️SMART ያልሆኑ TV SMART ለማድረግ ምን መግዛት እንዳለብዎ ካላወቁ  ይሄን እቃ ምርጫው ያድርጉ።

❇️የራሱ የሆነ BLUETOOTH ሪሞት ያለው ትክክለኛ 4K ምስል ጥራት ያለው

❇️የተለያዩ የፊልም እና የኳስ ቻናሎች የተጫኑበት በአጭር ጊዜ በሚቆ ይ ቅናሽ 3200 ብር ብቻ

Inbox Us 📩Admin @Sadikethio
Call 📱 +251 91 178 5693

የተለያዩ ነፃ የኳስ ቻናሎች የሚያገኙበት የዲሽ ቻናል 👇👇 https://www.tg-me.com/joinchat-AAAAAEnaa5LpZrcwQ-E0Tw
#MatchDay 🇪🇹

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዛሬ ምሽት የአለም ዋንጫ ማጣሪያ የምድብ ሶስተኛ ጨዋታውን ከጊኒ ቢሳው ብሔራዊ ቡድን ጋር የሚያደርግ ይሆናል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በጨዋታው ሙሉ ቢጫ ማልያ ለብሶ ወደ ሜዳ እንደሚገባ ተገልጿል።

የሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች ጨዋታ ዛሬ በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ምሽት 1:00 ሰዓት በስታዲዮ 24 ዴ ሴቴምብሮ የሚደረግ ይሆናል።

ጨዋታውን ማን ይመራዋል ?

ጨዋታውን ቤኒናውያን ዳኞች ጂንዶ ልዊስ በመሐል ዳኝነት አይማር ኤሪክ እና ጆ ኮርቴል በረዳት ዳኝነት እንዲሁም ሙሐመድ ኢሳ በአራተኛ ዳኝነት ይመሩታል።

ጨዋታውን በምን መመልከት ይቻላል ?

ጨዋታውን ከአንድ ሰዓት ጀምሮ በተከታዩ ሊንክ መከታተል ይችላሉ።

https://www.plus.fifa.com/en/content/guinea-bissau-v-ethiopia-caf-qualifiers-first-round-group-a-fifa-world-cup-26tm-live-stream-2024/acccd313-94dc-4a1d-ba44-2dbf97a5b894

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
እንግሊዝ ስብስቧን ይፋ አድርጋለች ! በአሰልጣኝ ጋሪዝ ሳውዝጌት የሚመራው የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን ለቀጣዩ የ2024 አውሮፓ ዋንጫ ውድድር የሚጠቀመውን ስብስብ ይፋ አድርጓል። ማርከስ ራሽፎርድ ከስብስቡ ውጪ የሆነው በእሱ ቦታ የተሻለ አመት ያሳለፉ ተጨዋቾች መኖራቸውን ተከትሎ መሆኑን አሰልጣኝ ጋሪዝ ሳውዝጌት ገልጸዋል። ብሔራዊ ቡድኑ በቀጣይ ከሚያደርጋቸው የወዳጅነት ጨዋታዎች በኋላ ሰባት ተጨዋቾችን…
ጄምስ ማዲሰን ከእንግሊዝ ስብስብ ተቀነሰ !

እንግሊዛዊው የቶተንሀም የመሐል ሜዳ ተጨዋች ጄምስ ማዲሰን ከቀጣዩ የ2024 አውሮፓ ዋንጫ ውድድር ውጪ መሆኑ ተገልጿል።

ከእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ጋሪዝ ሳውዝጌት ጥሪ ቀርቦለት የነበረው ጄምስ ማዲሰን አሁን ላይ ከስብስቡ መቀነሱ ተነግሯል።

ብሔራዊ ቡድኑ ለወዳጅነት ጨዋታዎች እና ዝግጅት ጥሪ ካደረገላቸው ተጨዋች ውስጥ ከጄምስ ማዲሰን በተጨማሪ ስድስት ተጨዋቾችን ቀንሶ ወደ አውሮፓ ዋንጫው ያመራል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
#MatchDay 🇪🇹 የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዛሬ ምሽት የአለም ዋንጫ ማጣሪያ የምድብ ሶስተኛ ጨዋታውን ከጊኒ ቢሳው ብሔራዊ ቡድን ጋር የሚያደርግ ይሆናል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በጨዋታው ሙሉ ቢጫ ማልያ ለብሶ ወደ ሜዳ እንደሚገባ ተገልጿል። የሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች ጨዋታ ዛሬ በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ምሽት 1:00 ሰዓት በስታዲዮ 24 ዴ ሴቴምብሮ የሚደረግ ይሆናል። ጨዋታውን ማን ይመራዋል…
" አስቸጋሪ ቡድን እንደምንገጥም እናውቃለን " ሉዊስ ቦ ሞርቴ

የዛሬ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ተጋጣሚ ጊኒ ቢሳው ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ሉዊስ ቦ ሞርቴ ኢትዮጵያ ጠንካራ ተጋጣሚ መሆኗን ከጨዋታው በፊት በሰጡት አስተያየት ተናግረዋል።

" የምንገጥመው ነጥብ ማግኘት የሚፈልግ ለማሸነፍ አስቸጋሪ የሆነ ቡድን መሆኑን እናውቃለን " ያሉት አሰልጣኝ ሉዊስ ቦ ሞርቴ " ነገርግን በሜዳችን እንደመጫወታችን አሸንፈን ሶስት ነጥቡን ማሳካት እንፈልጋለን።"ብለዋል።

ጊኒ ቢሳው በምድቡ አራት ነጥቦችን ሰብስባ ሶስተኛ ደረጃ ላይ ስትቀመጥ ኢትዮጵያ በአንድ ነጥብ አምስተኛ ደረጃን ይዛለች።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
" በሜዳችን መጫወታችን መነሳሳት ይጨምርልናል
" ማማ ባልዴ

የጊኒ ቢሳው ብሔራዊ ቡድን የፊት መስመር አጥቂ ማማ ባልዴ ቡድናቸው ዛሬ ከኢትዮጵያ ጋር በሚያደርገው ጨዋታ ደጋፊያቸው የአፍሪካ ዋንጫውን ክስተት ረስቶ ድጋፍ እንዲያደርግላቸው ጠይቋል።

ከምሽቱ ጨዋታ በፊት አስተያየቱን የሰጠው የሊዮን ተጨዋች ማማ ባልዴ " በሜዳችን እና ደጋፊያችን ፊት ነው የምንጫወተው ይህ ደግሞ መነሳሳት ይጨምርልናል።

በአፍሪካ ዋንጫው የተፈጠረውን ነገር መርሳት እና በቀጣይ የምናደርጋቸው ሁለት ጨዋታዎች ማተኮር አለብን ፣ ደጋፊው ከጎናችን እንደሚሆን ተስፋ እናደርጋለን።"ብሏል።

ጊኒ ቢሳው በቅርቡ በተደረገው የኮትዲቯር አፍሪካ ዋንጫ ውድድር ያደረገቻቸውን ሶስት የምድብ ጨዋታዎች ተሸንፋ ከምድቧ መሰናበቷ ይታወሳል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ሉካኩ ወደ ሳውዲ መሄድ እንደሚፈልግ ገለጸ !

ቤልጂየማዊው የፊት መስመር አጥቂ ሮሜሎ ሉካኩ የሳውዲ አረቢያ እግርኳስ በከፍተኛ ደረጃ እያደገ መሆኑን በሰጠው አሰሰተያየት ገልጿል።

" አንድ ቀን ሳውዲ አረቢያ መጫወት እፈልጋለሁ " የሚለው ሮሜሎ ሉካኩ እዛ እግርኳስ ከፍተኛ ደረጃ ላይ እንደሚደርስ አውቃለሁ ብዙ ተጨዋቾች ወደዛ መሄድ ይፈልጋሉ።"በማለት ተናግሯል።

" የሳውዲ አረቢያ እግርኳስ በፍጥነት እያደገ ነው የሚገኘው አሁን ካለበት ደረጃም ከፍ ይላል ፣ ሁሉም የአውሮፓ ክለቦች ሳውዲ ጠንካራ ሆና እንደምትመጣ ያውቃሉ።"ሉካኩ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ቼልሲ ተጨዋቾቹን ወደ ኦሎምፒክ አይልክም !

የምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ ተጨዋቾቹን ወደ ቀጣዩ የፈረንሳይ ፓሪስ የ2024 ኦሎምፒክ ውድድር ለብሔራዊ ቡድኖቻቸው እንደማይልክ ተገልጿል።

ሰማያዊዎቹ አርጀንቲናዊው ኢንዞ ፈርናንዴዝ እና ዩክሬናዊው ማይካሎ ሙድሪክ ወደ ኦሎምፒክ ውድድር እንዳይሄዱ ማድረጋቸው ተነግሯል።

ክለቡ ተጨዋቾቹ በኦሎምፒክ ውድድር እንዳይሳተፉ ያደረገው ከአውሮፓ እና ኮፓ አሜሪካ ውድድር ሲመለሱ ከአዲሱ አሰልጣኝ ጋር በቂ ጊዜ እንዲኖራቸው መሆኑ ተጠቁሟል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
Forwarded from WANAW SPORT
🔊 #አንድ ቀን ብቻ ቀረው

🔥 #እንዳያመልጥዎ፣ አሁኑኑ ይዘዙን!

📌 ለበለጠ መረጃና ትዕዛዝ 📲 0901138283፣ 0910851535 እና 0913586742 ላይ ይደውሉ።

👉🏾 እንዲሁም በቴሌግራም @Wanawsales ላይ የሽያጭ ሰራተኞቻችንን በቀጥታ በማናገር ወይም በቴሌግራም ቦት @WANAWSbot በኩል ይዘዙን።

Instagram | Facebook | TikTok

🏅 ዋናው ወደፊት...

@wanawsportwear
2024/10/03 19:23:51
Back to Top
HTML Embed Code: