Telegram Web Link
25 ' አታላንታ 2 - 0 ባየር ሊቨርኩሰን ( ዩሮፓ ሊግ ፍፃሜ )

ሉክማን

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
#እረፍት

አታላንታ ከባየር ሌቨርኩሰን ጋር እያደረጉ የሚገኙትን የዩሮፓ ሊግ ፍፃሜ ጨዋታ 2ለ0 በሆነ ውጤት እየመሩ ወደ መልበሻ ቤት አምርተዋል።

የአታላንታን የመሪነት ግቦች ሉክማን 2x ከመረብ ማሳረፍ ችሏል።

የጨዋታው የኳስ ቁጥጥር ምን ይመስላል ?

በመጀመሪያው አጋማሽ ባየር ሌቨርኩሰን 66% - 34% የኳስ ቁጥጥር ብልጫ ነበራቸው።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
አዴሞላ ሉክማን አዲስ ታሪክ ፅፏል !

ናይጄሪያዊው የአታላንታ የፊት መስመር ተጨዋች አዴሞላ ሉክማን በአውሮፓ መድረክ ውድድሮች ፍፃሜ ጨዋታ ላይ ሁለት ግቦችን ማስቆጠር የቻለ የመጀመሪያው አፍሪካዊ ተጨዋች መሆን ችሏል።

አታላንታ የመጀመሪያ የአውሮፓ መድረክ ፍፃሜ ጨዋታ ግቡን በሉክማን አማካኝነት ዛሬ ምሽት አስቆጥሯል።

ሉክማን በዘንድሮው የውድድር አመት ለአታላንታ በሁሉም ውድድሮች አስራ አራተኛ ግቡን ከመረብ ማሳረፍ ችሏል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
76 ' አታላንታ 3 - 0 ባየር ሊቨርኩሰን ( ዩሮፓ ሊግ ፍፃሜ )

         ሉክማን

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
አታላንታ የዩሮፓ ሊግ ሻምፒዮን ሆነ !

የጣልያኑ ክለብ አታላንታ ከጀርመኑ ክለብ ባየር ሊቨርኩሰን ጋር ያደረገውን የዩሮፓ ሊግ ፍፃሜ ጨዋታ 3ለ0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ሻምፒዮን መሆን ችለዋል።

የአታላንታን የማሸነፊያ ግቦች ናይጄሪያዊው ተጨዋች አዴሞላ ሉክማን 3x ከመረብ ማሳረፍ ችሏል።

የጣልያኑ ክለብ አታላንታ በታሪኩ የመጀመሪያ የዩሮፓ ሊግ ዋንጫውን በማሳካት አዲስ ታሪክ አስመዝግበዋል።

ናይጄሪያዊው የአታላንታ የፊት መስመር ተጨዋች አዴሞላ ሉክማን በዩሮፓ ሊግ ፍፃሜ ሀትሪክ መስራት የቻለ የመጀመሪያው ተጨዋች በመሆን አዲስ ታሪክ ፅፏል።

የጀርመኑ ክለብ ባየር ሊቨርኩሰን በዘንድሮው የውድድር አመት በሁሉም ውድድሮች የመጀመሪያ ሽንፈታቸውን አስተናግደዋል።

ባየር ሊቨርኩሰን ከሀምሳ አንድ ጨዋታዎች ያለመሸነፍ ጉዞ በኋላ የመጀመሪያ ሽንፈታቸውን አስተናግደዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
" ያሸነፍንበት መንገድ የማይታመን ነው " ጋስፔሪኒ

አትላንታን እየመሩ በአሰልጣኝነት ህይወታቸው የመጀመሪያ ዋንጫቸውን ያሳኩት አሰልጣኝ ጂያን ፔሮ ጋስፔሪኒ ድሉን " የማይታመን እና የማይረሳ " ሲሉ ገልፀውታል።

" የዩሮፓ ሊግ ዋንጫን ማሸነፍ ትልቅ ስኬት ነው " ያሉት አሰልጣኙ ባየር ሊቨርኩሰንን ያሸነፍንበት መንገድ የማይታመን እና የማይረስ ነው ፣ እኛ ብቻ ሳንሆን ደጋፊዎችም ታሪክ ሰርተዋል በማለት ተናግረዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
Forwarded from HEY Online Market
Affordable Gaming PC

•HP Pavilion
•HP Victus

•HP Omen 15
•HP Omen 16

Contact Us
0953964175 @heymobile

@heyonlinemarket
ሽመልስ በቀለ 1⃣8⃣ ገስት ሀውስ

በውቢቷ ሀዋሳ ቆይታዎ የት ለማረፍ አስበዋል ? ንፁህ እና በደንበኞቻችን ተወዳጅ በሆነው የእንግዳ ማረፊያችን መጥተው የእረፍት ጊዜውን ያሳልፉ።

እንግዶቻችንን ተቀበልን ለእይታ ሳቢ በሆነው የእንግዳ ማረፊያችን ማስተናገድ ከጀመርን አመታትን አስቆጥረናል።

አድራሻችን :- ሀዋሳ አርቴፍሻል ስታዲየም መንገድ ላይ ያገኙናል።

ለተጨማሪ መረጃ እና ለትዕዛዝዎ ይደውሉልን :- 0928684848

#ShemelesBekele18
" ይህንን ሽንፈት መቼም አልረሳውም " ዣቢ

ትላንት ምሽት በአታላንታ ተሸንፈው የዩሮፓ ሊግ ዋንጫን ያጡት ባየር ሌቨርኩሰን ዋና አሰልጣኝ ዣቢ አሎንሶ የምሽቱ ሽንፈት ሊረሱት የማይችሉት መሆኑን ገልጸዋል።

" ይህንን ሽንፈት መቼም አልረሳውም " ያሉት አሰልጣኝ ዣቢ አሎንሶ " ጥሩ ነበርን ነገርግን የአታላንታ ጥንካሬ ትልቅ ነበር ቡድኑ ያለውን ሁሉ ሰጥቶ ተጫውቷል ለተጨዋቾቹ ያለኝን ፍቅር አይለውጠውም " ብለዋል።

ባየር ሌቨርኩሰን ከሀምሳ አንድ ጨዋታዎች በኋላ የመጀመሪያ ሽንፈቱ ሲሆን በአመቱ ውስጥ የሶስትዮሽ ዋንጫ የማሳካት ህልሙንም ሳያሳካ ቀርቷል።

ያለፉትን አምስት የፍፃሜ ጨዋታዎች ማሸነፍ ያልቻለው የዣቢ አሎንሶው ቡድን ባየር ሌቨርኩሰን የአመቱ ሁለተኛ ዋንጫውን ለማሳካት የጀርመን ፖካል ፍፃሜ ጨዋታውን ከካይሴርስላውቴርን ጋር የፊታችን ቅዳሜ ያደርጋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
ቪንሴንት ኮምፓኒ ወዴት ሊያመራ ይችላል ? ቤልጂየማዊው የበርንሌይ ዋና አሰልጣኝ ቪንሴንት ኮምፓኒ በቀጣይ ታላላቅ ክለቦችን በሀላፊነት ለመረከብ ንግግር መጀመሩ በመዘገብ ላይ ይገኛል። የጀርመን ቡንደስሊጋው ክለብ ባየር ሙኒክ ቪንሴንት ኮምፓኒን በሀላፊነት ለመሾም እንደሚፈልጉ እና የክለቡ ሀላፊዎች ተደጋጋሚ የስልክ ልውውጥ ማድረጋቸው ተነግሯል። በትላንትናው ዕለት ከማውሪስዮ ፖቼቲኖ ጋር የተለያየው…
ኮምፓኒ ባየር ሙኒክን ለመረከብ ተቃረበ !

የጀርመኑ ክለብ ባየር ሙኒክ ቤልጂየማዊውን የበርንሌይ ዋና አሰልጣኝ ቪንሴንት ኮምፓኒ በአሰልጣኝ ቶማስ ቱሄል ምትክ በሀላፊነት ለመሾም መቃረባቸው ተገልጿል።

አሰልጣኝ ቪንሴንት ኮምፓኒ በሚቀጥሉት ቀናት ባየር ሙኒክን በሀላፊነት ለመረከብ ሙሉ ስምምነት ላይ ይደርሳሉ ተብሎ ይጠበቃል።

ባየር ሙኒክ አሁን ላይ በአሰልጣኙ የውል ካሳ ክፍያ ዙሪያ ከበርንሌይ ጋር በንግግር ላይ መሆናቸው የተገለጸ ሲሆን በሚቀጥሉት ቀናት ይጠናቀቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተዘግቧል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ኬቨን ዴብሮይን ወደ አሜሪካ ያመራ ይሆን ?

የአሜሪካ ሜጀር ሊግ ሶከሩ ክለብ ሳን ዲያጎ ቤልጂየማዊውን የማንችስተር ሲቲ የመሐል ሜዳ ተጨዋች ኬቨን ዴብሮይን የማስፈረም ሀሳብ እንዳላቸው ተገልጿል።

የኬቨን ዴብሮይን ተወካዮች ከአሜሪካው ክለብ ሳን ዲያጎ ጋር አንድ ጊዜ ተገናኝተው ለውይይት ተቀምጠው እንደነበር ተዘግቧል።

ይሁን እንጂ የማንችስተር ሲቲው የመሐል ሜዳ ተጨዋች ኬቨን ዴብሮይን ወደ አሜሪካ ለማምራት ዝግጁ መሆኑን የሚያመላክት ነገር አለመኖሩ ተነግሯል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
ኮምፓኒ ባየር ሙኒክን ለመረከብ ተቃረበ ! የጀርመኑ ክለብ ባየር ሙኒክ ቤልጂየማዊውን የበርንሌይ ዋና አሰልጣኝ ቪንሴንት ኮምፓኒ በአሰልጣኝ ቶማስ ቱሄል ምትክ በሀላፊነት ለመሾም መቃረባቸው ተገልጿል። አሰልጣኝ ቪንሴንት ኮምፓኒ በሚቀጥሉት ቀናት ባየር ሙኒክን በሀላፊነት ለመረከብ ሙሉ ስምምነት ላይ ይደርሳሉ ተብሎ ይጠበቃል። ባየር ሙኒክ አሁን ላይ በአሰልጣኙ የውል ካሳ ክፍያ ዙሪያ ከበርንሌይ ጋር…
ባየር ሙኒክ ለበርንሌይ ስንት አቀረበ ?

የቡንደስሊጋው ክለብ ባየር ሙኒክ ቤልጂየማዊውን የበርንሌይ አሰልጣኝ ቪንሴንት ኮምፓኒ ወደ ክለባቸው ለመውሰድ ለስምምነት እንደተቃረቡ መገለፁ ይታወቃል።

ከበርንሌይ ጋር በአሰልጣኙ ካሳ ክፍያ ዙሪያ ንግግር ላይ የሚገኙት ባየር ሙኒኮች #አስር ሚልዮን ዩሮ ማቅረባቸው ተገልጿል።

በርንሌይ በበኩላቸው የቀረበውን ሒሳብ ለመቀበል አለመፈለጋቸው እና #ሀያ ሚልዮን ዩሮ ክፍያ እንዲፈፀምላቸው እንደሚፈልጉ ተነግሯል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
#Tecno #Camon30Pro5G

ፍጥነት እና ቅልጥፍና መገለጫው የሆነውን MediaTek Dimensity 8200 ፕሮሰሰር አካቶ Tecno Camon 30 pro 5G ቀርቦሎታል

#Camon30Et #Camon30proEt #Camon30 #Camon30Pro #TecnoEt
📢 #ልዩ_የሽያጭ_ብስራቱ_ቀጥሏል!

⚽️#ዋናው ለእግር ኳስ ቡድንዎ  ማሊያ በቁምጣ እስከ #ግንቦት_30 ብቻ በሚቆየው ዋጋ በ #699 ብር ፦

👉🏾 ከ20 ብዛት ጀምሮ ሲገዙ ተጨማሪ 2 ባለኮሌታ ቲ-ሸርቶችን በነፃ ያገኛሉ።
👉🏾 ከ 50 ብዛት ጀምሮ ሲገዙ 5 ባለኮሌታ ቲ-ሸርቶችን እና 1 ባንዲራን በነፃ እንሰጥዎታለን።
👉🏾 ከ100 ብዛት ጀምሮ ሲገዙ ደግሞ 1 Molten 1ኛ ደረጃ ኳስ እና 1 ባንዲራን በነፃ የሚያገኙ ይሆናል።

🔥 #እንዳያመልጥዎ፣ አሁኑኑ ይዘዙን!

📍አድራሻችን:- ገርጂ መብራት ሃይል የካቲት ወረቀት ፊትለፊት፣ አለም ገብሬ ህንፃ፣ 2ተኛ ፎቅ።

📌 ለበለጠ መረጃና ትዕዛዝ 📲 0901138283፣ 0910851535 እና 0913586742 ላይ ይደውሉ።

👉🏾 እንዲሁም በቴሌግራም @Wanawsales ላይ የሽያጭ ሰራተኞቻችንን በቀጥታ በማናገር ወይም በቴሌግራም ቦት @WANAWSbot በኩል ይዘዙን።

Instagram | Facebook | TikTok

🏅 ዋናው ወደፊት...

@wanawsportwear
TIKVAH-SPORT
ዌስትሀም አሰልጣኝ ለመሾም ተስማማ ! በውድድር አመቱ መጨረሻ ከአሰልጣኝ ዴቪድ ሞይስ ጋር የሚለያዩት ዌስትሀም ዩናይትዶች በምትኩ አዲስ አሰልጣኝ ለመሾም ከስምምነት መድረሳቸው ተገልጿል። ዌስትሀም ዩናይትድ በሚቀጥለው የውድድር አመት አሰልጣኝ ጁሊያን ሎፕቲጌን በሀላፊነት ለመሾም ከስምምነት መድረሳቸው ተነግሯል። የቀድሞ የሪያል ማድሪድ ፣ ሲቪያ ፣ ዎልቭስ እና ስፔን ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ጁሊያን…
ዌስትሀም ዩናይትድ በይፋ አሰልጣኝ ሾመ !

በውድድር አመቱ መጨረሻ ከአሰልጣኝ ዴቪድ ሞይስ ጋር የተለያየው ዌስትሀም ዩናይትድ አዲስ አሰልጣኝ በሀላፊነት መሾሙን ይፋ አድርጓል።

ዌስትሀም ዩናይትድ የ 57ዓመቱን የቀድሞ የሪያል ማድሪድ ፣ ሲቪያ ፣ ዎልቭስ እና ስፔን ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ጁሊያን ሎፕቲጌን በሀላፊነት መሾሙን በይፋ አሳውቋል።

አሰልጣኝ ጁሊያን ሎፕቲጌ ከሀላፊነቱ በኋላ በሰጡት አስተያየት " እንደ አሰልጣኝ ሁልጊዜ ምኞቴ በየጊዜው መሻሻል ፣ ተጨዋቾችን ማሻሻል እና ትልቅ ነገሮችን ማሳካት ነው ለመጀመር ጓጉተናል " በማለት ተናግረዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
አሰልጣኝ ቲያጎ ሞታ ከቦሎኛ ጋር ተለያዩ !

አሰልጣኝ ቲያጎ ሞታ ከጣልያን ሴርያው ክለብ ቦሎኛ ጋር መለያየታቸውን ክለቡ ባወጣው ይፋዊ መግለጫ አረጋግጧል።

በሴርያው ስኬታማ የውድድር አመት ያሳለፉት አሰልጣኝ ቲያጎ ሞታ ቦሎኛን ከስልሳ አመታት በኋላ ለአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ በማሳለፍ አዲስ ታሪክ መፃፍም ችለዋል።

አሰልጣኝ ቲያጎ ሞታ በቀጣይ ጁቬንቱስን በሀላፊነት ለመረከብ ከስምምነት የደረሱ ሲሆን በቀጣይ ክለቡ ይፋ እንደሚያደርግ ይጠበቃል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ሪያል ማድሪድ ትልቅ ዋጋ ያለው ክለብ ሆኗል !

የስፔን ላሊጋው ክለብ ሪያል ማድሪድ ለሶስተኛ ተከታታይ አመታት የአለማችን ከፍተኛ ዋጋ ያለው ውድ ክለብ መሆን መቻሉ ተገልጿል።

የስፔን ላሊጋ ሻምፒዮኑ ሪያል ማድሪድ እንደ ፎርብስ መረጃ አሁን ላይ 6.6 ቢልዮን ዶላር የሚደርስ ዋጋ ይኖረዋል ተብሎ እንደሚገመት ተገልጿል።

የእንግሊዝ ፕርሚየር ሊጉ ክለብ ማንችስተር ዩናይትድ በ6.5 ቢልዮን ዶላር ዋጋ ሁለተኛ ደረጃን መያዙ ተነግሯል።

ትልቅ ዋጋ ያላቸው አስር ክለቦች የትኞቹ ናቸው ?

1️⃣ ሪያል ማድሪድ   :- 6.6 ቢልዮን ዶላር
2️⃣ ማንችስተር ዩናይትድ :- 6.5 ቢልዮን ዶላር
3️⃣ ባርሴሎና :- 5.6 ቢልዮን ዶላር
4️⃣ ሊቨርፑል :- 5.3 ቢልዮን ዶላር
5️⃣ ማንችስተር ሲቲ :- 5.1 ቢልዮን ዶላር

6️⃣ ባየር ሙኒክ :- 5 ቢልዮን ዶላር
7️⃣ ፒኤስጂ :- 4.4 ቢልዮን ዶላር
8️⃣ ቶተንሀም :- 3.2 ቢልዮን ዶላር
9️⃣ ቼልሲ :- 3.1 ቢልዮን ዶላር
1️⃣0️⃣ አርሰናል 2.6 ቢልዮን ዶላር

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ዩናይትድ ተጨዋቹ በቋሚነት ይቀጥላል !

ከማንችስተር ዩናይትድ በውሰት ለፖርቹጋሉ ክለብ ቤኔፊካ የሚጫወተው አልቫሮ ፈርናንዴዝ በክለቡ በቋሚነት ለመቀጠል የረጅም ጊዜ ውል መፈረሙ ተገልጿል።

ቤኔፊካ በተጨዋቹ ውል ውስጥ የተካተተውን የመግዛት አማራጭ መጠቀማቸውን ተከትሎ ማንችስተር ዩናይትድ #ስድስት ሚልዮን ዩሮ ክፍያ እንደሚያገኙ ተነግሯል።

ማንችስተር ዩናይትድ በተጨማሪም በውሉ ውስጥ የመልሶ የመግዛት አማራጭ እና ከተጨዋቹ ቀጣይ ሽያጭ ተጠቃሚ የሚያደርጋቸው ውል ማካተታቸው ተዘግቧል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ቼልሲ በቀጣይ ማንን ሊሾም ይችላል ?

ከአሰልጣኝ ማውሪስዮ ፖቼቲኖ ጋር የተለያየው የምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ በቀጣይ አዲስ አሰልጣኝ ለመሾም በማፈላለግ ላይ ይገኛሉ።

ሰማያዊዎቹ በቀጣይ ለመሾም በዝርዝራቸው ውስጥ ከያዟቸው አሰልጣኞች መካከል

- የሌስተር ሲቲው አሰልጣኝ ኢንዞ ማሬስካ

- የኢፕስዊች ታውኑ አሰልጣኝ ኬራን ማክኬና

- የብሬንትፎርዱ አሰልጣኝ ቶማስ ፍራንክ እንደሚገኙበት ተገልጿል።

ክለቡ ሲመለከታቸው የነበሩትን የጂሮና አሰልጣኝ ሚቼል እና የስቱትጋርቱን አሰልጣኝ ሴባስቲያን ሆኔስ ከዝርዝሩ ውስጥ ማስወጣቱ ተዘግቧል።

ቼልሲዎቹ በቀጣይ ተጨማሪ እጩ አሰልጣኞችን ለመመልከት ዝግጁ መሆናቸው የተገለፀ ሲሆን በውስጥ ንግግሮች መቀጠላቸው ተጠቁሟል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
2024/10/05 09:25:34
Back to Top
HTML Embed Code: