በካሜሩን ቴሌኮሙኒኬሽን (ካምቴል) ዋና ሥራ አስፈጻሚ ጁዲት ያህ ሰንደይ የተመራ የልዑካን ቡድን፣ በዲጂታል ፋይናንሻል አገልግሎት እና በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ረገድ ተሞክሮዎችን ለመቅሰም የሚያስችል ጉብኝት በኢትዮ ቴሌኮም አደረገ።
ዋና ሥራ አስፈፃሚያችን ፍሬሕይወት ታምሩ የኢትዮ ቴሌኮምን ፈጣን የለውጥ ጉዞ፣ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ስትራቴጂ እንዲሁም ከመደበኛ ኮኔክቲቪቲ አገልግሎት ባሻገር በዲጂታል ሶሉሽኖችን የዜጎች፣ ቢዝነስ እና ተቋማትን አቅም በመገንባት የሀገሪቱን ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን በማፋጠን ላይ ያለውን ቁልፍ ሚና ገልጸዋል፡፡
የልዑካን ቡድኑ አባላት በኤክስፒሪያንስ ማዕከላችንና ዳታ ሴንተር ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን፣ በጉብኝቱም ወቅት ከግብርና፣ ከትምህርት፣ ከጤና አጠባበቅ፣ ከማዕድን እና ከስማርት ቱሪዝም ጋር ስለተያያዙ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች ገለጻ ተደርጎላቸዋል፡፡
የልዑካን ቡድኑ አባላትም ሶሉሽኖቹ ጠንካራ የዲጂታል ኢኮኖሚን ለመገንባት እየተከናወነ ስለሚገኘው ቁርጠኛ ሥራ ማሳያ ስለመሆናቸው እንዲሁም በኩባንያችን ደንበኞች ቁጥር እድገት ያላቸውን አድናቆት ገልጸዋል፡፡
የካምቴል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኩባንያው ቴሌብርን እና ዲጂታል ሥነ-ምህዳርን ለማሳደግ እያደረገ የሚገኘው ጥረት በመላ አፍሪካ የዲጂታል ፈጠራ ፋናወጊ ለመሆን ያለውን አቅም ያሳያል ብለዋል፡፡
#DigitalAfrica #DigitalEthiopia #SmartAfrica #Camatel #GSMA #ITU #Ethiotelecom #telebirr
ዋና ሥራ አስፈፃሚያችን ፍሬሕይወት ታምሩ የኢትዮ ቴሌኮምን ፈጣን የለውጥ ጉዞ፣ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ስትራቴጂ እንዲሁም ከመደበኛ ኮኔክቲቪቲ አገልግሎት ባሻገር በዲጂታል ሶሉሽኖችን የዜጎች፣ ቢዝነስ እና ተቋማትን አቅም በመገንባት የሀገሪቱን ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን በማፋጠን ላይ ያለውን ቁልፍ ሚና ገልጸዋል፡፡
የልዑካን ቡድኑ አባላት በኤክስፒሪያንስ ማዕከላችንና ዳታ ሴንተር ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን፣ በጉብኝቱም ወቅት ከግብርና፣ ከትምህርት፣ ከጤና አጠባበቅ፣ ከማዕድን እና ከስማርት ቱሪዝም ጋር ስለተያያዙ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች ገለጻ ተደርጎላቸዋል፡፡
የልዑካን ቡድኑ አባላትም ሶሉሽኖቹ ጠንካራ የዲጂታል ኢኮኖሚን ለመገንባት እየተከናወነ ስለሚገኘው ቁርጠኛ ሥራ ማሳያ ስለመሆናቸው እንዲሁም በኩባንያችን ደንበኞች ቁጥር እድገት ያላቸውን አድናቆት ገልጸዋል፡፡
የካምቴል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኩባንያው ቴሌብርን እና ዲጂታል ሥነ-ምህዳርን ለማሳደግ እያደረገ የሚገኘው ጥረት በመላ አፍሪካ የዲጂታል ፈጠራ ፋናወጊ ለመሆን ያለውን አቅም ያሳያል ብለዋል፡፡
#DigitalAfrica #DigitalEthiopia #SmartAfrica #Camatel #GSMA #ITU #Ethiotelecom #telebirr
👍81❤9🙏7👏2😍1
ኢትዮ ቴሌኮም እና ሲንቄ ባንክ የዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎቶችን ለማስፋት ያለመ ስትራቴጂያዊ ምክክር አደረጉ!
የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ እና የሲንቄ ባንክ ፕሬዚዳንት ነዋይ መገርሳ የሁለቱ ተቋማት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት የሚያቀርቡትን አካታችነትን እና ተደራሽነትን የሚያረጋግጡ የዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎቶችን ለማስፋት ያለመ ስትራቴጂያዊ ውይይት አደረጉ፡፡
ዋና ሥራ አስፈጻሚያችን ኢትዮ ቴሌኮም ከፋይናንስ ተቋማት ጋር በአጋርነት ዜጎች የዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎቶች ተጠቃሚ በማድረግ አካታች የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ቀጣይነት ላለው ሀገራዊ እድገት የበኩሉን ሚና በመጫወት ላይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
አክለውም ከሲንቄ ባንክ ጋር በአጋርነት በማህበረሰባችን ህይወት ላይ ትርጉም ያለው ለውጥ የሚያመጡ አዳዲስ የፋይናንስ አገልግሎቶችን በማቅረብ ሁሉን አቀፍ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ የሚያፋጥኑ ዝግጅቶች መጠናቀቃቸውን ገልጸዋል፡፡
የሲንቄ ባንክ ፕሬዚደንት ነዋይ በበኩላቸው ባንካቸው በአጭር ጊዜ ሁሉን አቀፍ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን በማድረግ ፈጣን ለውጥ በማስመዝገብ ላይ መሆኑን በመግለጽ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር አጋርነት ማጠናከር የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት በፍጥነት ለማረጋገጥ አስቻይ መደላድል የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል፡፡
አክለውም ኢትዮ ቴሌኮም ከቅርብ አመታት ወዲህ በተለይም በዲጂታል ፋይናንስ ስነ-ምህዳሩ ላይ እያደረገ ያለው ፈጣን ለውጥ በማድነቅ ለዚህም አመራሩ ለባንካቸው መልካም አርአያና መበረታቻ እንደሆነ በአጽንኦት ገልጸዋል፡፡
#DigitalEthiopia #DigitalAfrica #SmartAfrica #GSMA #ITU #Ethiotelecom #Siinqee #telebirr
የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ እና የሲንቄ ባንክ ፕሬዚዳንት ነዋይ መገርሳ የሁለቱ ተቋማት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት የሚያቀርቡትን አካታችነትን እና ተደራሽነትን የሚያረጋግጡ የዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎቶችን ለማስፋት ያለመ ስትራቴጂያዊ ውይይት አደረጉ፡፡
ዋና ሥራ አስፈጻሚያችን ኢትዮ ቴሌኮም ከፋይናንስ ተቋማት ጋር በአጋርነት ዜጎች የዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎቶች ተጠቃሚ በማድረግ አካታች የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ቀጣይነት ላለው ሀገራዊ እድገት የበኩሉን ሚና በመጫወት ላይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
አክለውም ከሲንቄ ባንክ ጋር በአጋርነት በማህበረሰባችን ህይወት ላይ ትርጉም ያለው ለውጥ የሚያመጡ አዳዲስ የፋይናንስ አገልግሎቶችን በማቅረብ ሁሉን አቀፍ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ የሚያፋጥኑ ዝግጅቶች መጠናቀቃቸውን ገልጸዋል፡፡
የሲንቄ ባንክ ፕሬዚደንት ነዋይ በበኩላቸው ባንካቸው በአጭር ጊዜ ሁሉን አቀፍ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን በማድረግ ፈጣን ለውጥ በማስመዝገብ ላይ መሆኑን በመግለጽ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር አጋርነት ማጠናከር የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት በፍጥነት ለማረጋገጥ አስቻይ መደላድል የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል፡፡
አክለውም ኢትዮ ቴሌኮም ከቅርብ አመታት ወዲህ በተለይም በዲጂታል ፋይናንስ ስነ-ምህዳሩ ላይ እያደረገ ያለው ፈጣን ለውጥ በማድነቅ ለዚህም አመራሩ ለባንካቸው መልካም አርአያና መበረታቻ እንደሆነ በአጽንኦት ገልጸዋል፡፡
#DigitalEthiopia #DigitalAfrica #SmartAfrica #GSMA #ITU #Ethiotelecom #Siinqee #telebirr
👍57❤17😁4👏3
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ሚያዝያን ለኒያ ፋውንዴሽን ጆይ ኦቲዝም ማዕከል!!
በዚህ ወር በማኅበራዊ ትስስር ገፆቻችን በሚቀላቀሉ አዲስ ተከታዮች ብዛት ልክ 30 ብር እንዲሁም በሚጋሩ Share ልክ 10 ብር ለኒያ ፋውንዴሽን ጆይ ኦቲዝም ማዕከል እንለግሳለን!
🤝 እርስዎም ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገፆቻችንን ይከተሉ፤ ፖስቶቻችንን ያጋሩ፤ ለወገን ድጋፍ ይተባበሩ!
ቴሌግራም | ፌስቡክ | ኢንስታግራም | ሊንክዲን | ዩትዩብ | ቲክቶክ
በተጨማሪም በቴሌብር ሱፐርአፕ https://bit.ly/telebirr_SuperApp ለበጎ አድራጎት በሚለው አማራጭ የፈቀዱትን የገንዘብ መጠን በመለገስ ለወገንዎ ተስፋ ይሁኑ!
🙏 ዘላቂ የጋራ ማኅበራዊ ኃላፊነት ለወገን ብሩህ ተስፋ!
#MatchingFundForSustainableFuture
#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
በዚህ ወር በማኅበራዊ ትስስር ገፆቻችን በሚቀላቀሉ አዲስ ተከታዮች ብዛት ልክ 30 ብር እንዲሁም በሚጋሩ Share ልክ 10 ብር ለኒያ ፋውንዴሽን ጆይ ኦቲዝም ማዕከል እንለግሳለን!
🤝 እርስዎም ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገፆቻችንን ይከተሉ፤ ፖስቶቻችንን ያጋሩ፤ ለወገን ድጋፍ ይተባበሩ!
ቴሌግራም | ፌስቡክ | ኢንስታግራም | ሊንክዲን | ዩትዩብ | ቲክቶክ
በተጨማሪም በቴሌብር ሱፐርአፕ https://bit.ly/telebirr_SuperApp ለበጎ አድራጎት በሚለው አማራጭ የፈቀዱትን የገንዘብ መጠን በመለገስ ለወገንዎ ተስፋ ይሁኑ!
🙏 ዘላቂ የጋራ ማኅበራዊ ኃላፊነት ለወገን ብሩህ ተስፋ!
#MatchingFundForSustainableFuture
#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
👍53❤12🙏7
እንኳን ደስ አላችሁ፤ እንኳን ደስ አለን!
ኢትዮ ቴሌኮም ከ47 ሺህ በላይ የሚሆኑ ዜጎች የአክሲዮን ድርሻ ባለቤት ለማድረግ የሚያስችለውን ወሳኝ ታሪካዊ ምዕራፍ ላይ መድረሱን ሲገልጽ በታላቅ ደስታ ነው!!
መንግስት ያደረገውን የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ተከትሎ ኢትዮ ቴሌኮምን ወደ አክሲዮን ማኀበርነት ለመቀየር የተቋሙን 10 በመቶ የባለቤትነት ድርሻ ሽያጭ ከጥቅምት 6 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ እስከ የካቲት 7 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ለ121 ቀናት በዲጂታል መንገድ ሲከናወን መቆየቱ ይታወሳል፡፡
በዛሬው ዕለት በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ ዜጎችን በስፋት በመሳተፍ በተከናወነው የመደበኛ አክሲዮን ሽያጭ ከ47,377 ዜጎች ከ10.7 ሚሊዮን የአክሲዮን ድርሻ በዲጂታል መንገድ በማከናወን ብር 3.2 ቢሊየን የሚጠጋ ሀብት በማሰባሰብ ዜጎች በካፒታል ገበያ የሚሳተፉበትን መደላድል መፍጠር ተችሏል፡፡
የተሸጡ አክሲዮኖች ድልድል በካፒታል ገበያ ባለስልጣን የማጽደቅ ሂደት ከተከናወነ በኋላ ውጤቱን የምናሳውቅ ሲሆን፣ ቀሪ አክስዮኖችን በተመለከተ አክሲዮን የገዙ ባለድርሻዎችን መብት ባስጠበቀ መልኩ በቀጣይ በዝርዝር የሽያጭ ሂደቱን የምንገልጽ ይሆናል፡፡
ለበለጠ መረጃ፡ https://bit.ly/42u5SrT
ኢትዮ ቴሌኮም ከ47 ሺህ በላይ የሚሆኑ ዜጎች የአክሲዮን ድርሻ ባለቤት ለማድረግ የሚያስችለውን ወሳኝ ታሪካዊ ምዕራፍ ላይ መድረሱን ሲገልጽ በታላቅ ደስታ ነው!!
መንግስት ያደረገውን የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ተከትሎ ኢትዮ ቴሌኮምን ወደ አክሲዮን ማኀበርነት ለመቀየር የተቋሙን 10 በመቶ የባለቤትነት ድርሻ ሽያጭ ከጥቅምት 6 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ እስከ የካቲት 7 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ለ121 ቀናት በዲጂታል መንገድ ሲከናወን መቆየቱ ይታወሳል፡፡
በዛሬው ዕለት በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ ዜጎችን በስፋት በመሳተፍ በተከናወነው የመደበኛ አክሲዮን ሽያጭ ከ47,377 ዜጎች ከ10.7 ሚሊዮን የአክሲዮን ድርሻ በዲጂታል መንገድ በማከናወን ብር 3.2 ቢሊየን የሚጠጋ ሀብት በማሰባሰብ ዜጎች በካፒታል ገበያ የሚሳተፉበትን መደላድል መፍጠር ተችሏል፡፡
የተሸጡ አክሲዮኖች ድልድል በካፒታል ገበያ ባለስልጣን የማጽደቅ ሂደት ከተከናወነ በኋላ ውጤቱን የምናሳውቅ ሲሆን፣ ቀሪ አክስዮኖችን በተመለከተ አክሲዮን የገዙ ባለድርሻዎችን መብት ባስጠበቀ መልኩ በቀጣይ በዝርዝር የሽያጭ ሂደቱን የምንገልጽ ይሆናል፡፡
ለበለጠ መረጃ፡ https://bit.ly/42u5SrT
👍84❤29😁10🙏4🤩2😍2