Telegram Web Link
ሥርዓተ ማኅሌት ዘነሐሴ ፲፮

👉 @ortodoxtewahedo
#እመቤቴ ማርያም

እመቤቴ ማርያም እለምንሻለው
በለቅሶ በዋይታ ፊትሽ ወድቄአለው
እመቤቴ ስሚኝ ተማጽኜሻለው /2/
ሐዘኔን ጭንቀቴን ለማን እነግራለው
ችግሬን ጉዳቴን ለማን አዋያለው
እመቤቴ ስሚኝ ተማጽኜሻለው /2/
ሐዘኑ በዛብኝ ፈተናው ከበደኝ
እንደምን ልቻለው እኔስ ብቻዬን ነኝ
የዐማኑኤል እናት ፈጥነሽ ድረሽልኝ /2/
በጣም ተንገዳገድከ ልወድቅ ነው እኔ
እመ አምላክ ደግፊኝ ቁሚልኝ ከጎኔ
ምንም አጋር የለኝ ከአንቺ በቀር ለእኔ /2/

👉 @ortodoxtewahedo
Forwarded from ዘ-ተዋሕዶ ቦት
🙏 በማርያም ይሄን ቻናል ሳታዩ እንዳታልፉት JOIN የምትለውን ብቻ ይንኳት።🙏
‹‹የጥቁሩን አህያ ራስ ከነጩ የነጩን አህያ ራስ ከጥቁሩ››

አቡነ ቶማስ የመርዓስ ሀገር ኤጲስ ቆጶስ ሲሆኑ ታላቅ ሰማዕትነትን የተቀበሉ ሃይማኖት ምግባራቸው እጅግ የቀና ታላቅ አባት ናቸው፡፡ ከሃዲው ዲዮቅልጥያኖስ በነገሠ ጊዜ ክርስቲያኖቹን ሲያሠቃዩ በነበረበት ወቅት ከንጉሡ መኳንንት አንዱ ወደ መርዓስ ሄዶ አቡነ ቶማስን በጭፍሮቹ አሲያዛቸው፡፡ አባታችንን እንደያዟቸው ደብድበው በምድር ላይ እየጎተቱዋቸው ደማቸው እየፈሰሰ ወሰዷቸው፡፡ መኰንኑ ‹‹ለአማልክት ስገድ›› አላቸው፡፡ አቡነ ቶማስም ‹‹ከእግዚአብሔር በቀር የሚሰግዱለት አምላክ የለም›› አሉት፡፡ መኰንኑም እጅግ የበዙ ጽኑ ሥቃዮችን አሠቃያቸው፡፡ የነዳጅ ድፍድፍ አፍልተው በሰውነታቸው ላይ እንዲሁም በአፍና በአፍንጫቸው ጨመሩባቸው፡፡ ቶሎ ብለው እንዲሞቱ ሳይሆን በሥቃይ ሆነው እንዲቆዩ በማድረግ ለ22 ዓመታት በጨለማ ውስጥ እያሰሩ አሠቃዩአቸው፡፡ ከሃዲያኑም በየዓመቱ ወደ እስር ቤቱ እየገቡ አንድ አካላቸውን ይቆርጣሉ፡፡ እጆቻቸውንና እግሮቻቸውን በየተራ ቆራረጧቸው፡፡ አፍንጫቸውን፣ ከንፈሮቻቸውን፣ ጆሮዎቻቸውን ሁሉ በየተራ እየቆረጡ ለ22 ዓመትታት ጣዖታቸውን ሲያጥኑበት ኖረዋል፡፡
አንዲት ደግ ክርስቲያን ሴት ግን የተጣሉበትን ጉድጓድ አይታ ስለነበር በድብቅ ሌሊት እየሄደች ትመግባቸው ነበር፡፡ ደገኛውና ጻድቁ ንጉሥ ቆስጠንጢኖስ በነገሠ ጊዜ ይህች ሴት ሄዳ ስለ አቡነ ቶማስ ነግረችውና አባታችንን ከተጣሉበት ጉድጉድ አወጣቸው፡፡ ቆስጠንጢኖስ የከበሩ 318 ኤጲስ ቆጶሳትን በኒቅያ አገር እንዲሰበሰቡ ሲያደርግ አንዱ አቡነ ቶማስ ነበሩ፡፡ ወደ ጉባዔውም ሲሄዱ ደቀ መዛሙርቶቻቸው በቅርጫት አድርገው በአህያ ጭነው ወደ ጉባኤ ኒቂያ ይዘዋቸው ሄደዋል፡፡ በመንገድም ሳሉ ዐላዊያኑ አግኝተዋቸው አህዮቻቸውን ሌሊት ራስ ራሳቸውን ቆርጠው ጣሉባቸው፡፡ አቡነ ቶማስም ራሳቸው የተቆረጡትን አህዮች አምጡልኝ ብለው የጥቁሩን አህያ ራስ ከነጩ፣ የነጩን አህያ ራስ ከጥቁሩ ገጥመው ቢባርኳቸው ሁሉም አህዮች ከሞት ተነሥተዋል፡፡
ከጉባዔውም ሲደርሱ ንጉሥ ቆስጠንጢኖስ ጽድቃቸውን ዐውቆ ‹‹አባቴ በረከትዎ ትድረሰኝ›› በማለት በዐላዊያኑ የተቆራረጠ አካላቸውን ዳሶ ተባርኳል፡፡ አቡነ ቶማስ ዘመርዓስም ከሌሎቹ ኤጲስ ቆጶሳት ጋር ሆነው አርዮስን መክረውና አስተምረው እምቢ ቢላቸው አውግዘውት ወደ ሀገራቸው እንደተመለሱ ነሐሴ 24 በሰላም ዐርፈዋል፡፡

የአቡነ ቶማስ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን

✞ ✞ ✞

@ortodoxtewahedo
2024/09/30 21:33:40
Back to Top
HTML Embed Code: