Telegram Web Link
"መምሬ ካሳሁን እንግዳ በአድዋ ጦርነት ጊዜ የቅዱስ ጊዮርጊስን ታቦት ይዘው በባዶ እግራቸው የዘመቱ አባታችን"

አድዋ የካቲት ፳፫ ቀን ፲፰፻፹፰ ዓ.ም በአድዋ ተራራ ላይ ጥቁር ሕዝቦች ለመጀመሪያ ጊዜ የማይቻል የሚመስለውን የቻሉበት፣ አይሆንም የተባለው የሆነበት፣ “ነጮች” “በጥቁሮች” የተሸነፉበት፣ ታላቅ ሁነት የተፈጸመበት፣ የድል በዓል መታሰቢያ ነው።

የአድዋን ድል ልዩ ያደረገው አንድ ሕዝብ በጦር ሜዳ ተዋግቶ ያሸነፈበት ታሪክ ስለ ሆነ ብቻ ሳይሆን በዘመኑ ዓለምን የተቆጣጠረውን “ጥቁር ሕዝብ ተፈጥሮውም፣ ኑሮውም ነጭን ለማሸነፍ አያስችለውም” የሚልና እንኳን ገዥዎችን ተገዥዎችንም ጭምር አሳምኖ የነበረ አስተሳሰብን የሻረ በመሆኑ ነው፡፡ ሁለት ለንጽጽር የማይገቡና ያልተመጣጠነ አሰላለፍ የነበራቸው ሕዝቦችና መንግሥታት ተዋግተው እንደ ጎልያድ በሰይፍ የመጣው ሳይሆን እንደ ዳዊት በእምነት ጠጠር የወነጨፈው ያሸነፈበት የማይታመን እውነታ በመሆኑም ነው፡፡

በአድዋ እንዴት ልናሸንፍ ቻልን?

የቤተ ክርስቲያናችን አስተዋጽኦ የሚገለጠው “እንዴት አሸነፍን?” የሚለውን ጥያቄ ለመመለስ ስንመረምር ነው፡፡ ይህ ዓለምን በብርቱ ጠፍንጎ የያዘና አንዱን ባሪያ ሌላውን ጌታ የሚያደርግ፣ ሰውን ያህል ፍጡር እንደ ከብት ነድቶ፣ እንደ ዕቃ ጎልቶ፣ ለገበያ አቅርቦ የሚሸጥ እኩይ አስተሳሰብ ከመሠረቱ የናደ፣ ነጻነት ማለት ምን ማለት እንደ ሆነ ለሌሎች ያሳየ፣ የአስተሳሰቡ ሰለባ የነበሩ ነጮችንም ያስደነገጠ ድል ኢትዮጵያውያን እንዴት ሊቀዳጁ ቻሉ? ዓቅሙና ብርታቱስ ከየት ተገኘ? ምዕራባውያን ያላቸው የሠለጠነ ወታደር፣ የጦር መሣሪያ ልዩነት እና ዓለምን የተቆጣጠረው “የነጮች” የበላይነት አስተሳሰብ እያለ የመግጠምስ ሞራሉና እምነቱ ከወዴት መጣ? ኢትዮጵያውያንን ከዚህ የአስተሳሰብና የሞራል ከፍታ ያደረሳቸው ገፊ ምክንያትስ ምንድን ነው? የሚሉ ጥያቄዎችን ስንጠይቅ መልሱ ቤተ ክርስቲያናችን ዘንድ ያደርሰናል፡፡

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቀደም ብላ ያስተማረችው ትምህርት፣ በነገሥታቱ እና በሕዝቡ ላይ ያሳደረችው በጎ ተፅዕኖ፣ “የእኔም ጦርነት ነው፤ በህልውናዬ ላይ የመጣ ነው” ብላ በማሰብ ደወል ደውላ፣ ዐዋጅ ነግራ ታቦት ይዛ ቀጥተኛ ተሳታፊ በመሆኗ ለኢትዮጵያውያን የአስተሳሰብ ከፍታ የነበራት አስተዋጽኦ ከፍተኛ ነው፡፡

ኢትዮጵያውያን በእግዚአብሔር የሚያምኑ፣ የካህናትን ትእዛዝ የሚቀበሉ፣ እግዚአብሔርን መፍራትንና ንጉሥ ማክበርን የሚያውቁ፣ መመካት ቢገባቸውም ምሕረትን፣ ፍርድንና ጽድቅንም በምድር ላይ በሚያደርገው በእግዚአብሔር እንጂ በጉልበት፣ በሠራዊት ብዛት፣ በመሣሪያ ጥራት እንዳልሆነ ሲሰበኩ የኖሩ፣ ይህን እውነትም በልባቸው የጻፉ ስለ ነበሩ ነው፡፡ (ኤር.፱፥፳፬)

የአድዋ አርበኞች “እኛኮ ዘመናዊ ትጥቅ የለንም፤ እኛኮ “ጥቁሮች” ነን፤ “ነጭን” ማሸነፍ አንችልም፤ እኛኮ እንበርበት አውሮፕላን፣ እንሽከረከርበት አውቶሞቢል የለንም፤ እንዴት እናሸንፋለን? እንዴትስ ይቻለናል?” የሚል ጥያቄ በፍጹም አልጠየቁም፡፡ ምክንያቱም ‹‹ኢይድኅን ንጉሥ በብዝኀ ሠራዊቱ ወያርብኅኒ በብዝኀ ኃይሉ….፤ንጉሥ በሠራዊቱ ብዛት አይድንም፤ ኀያልም በኃይሉ ብዛት አያመልጥም›› የሚል ትምህርትን ያስተማረችው፣ የእምነት ስንቅም ያስቋጠረችው ቤተ ክርስቲያን ናትና፡፡ (መዝ.፴፪፥፲፮) ብዙዎች የሚዘነጉት ጉዳይ ጦርነትን የሚያሸንፈው የሠራዊት ብዛት፣ የመሣሪያ ጥራት ብቻ ስለሚመስላቸው ነው፡፡

ይህ የአስተሳሰብ ችግር በሰው ልጅ ታሪክ ውስጥ ረጅም ዘመናትን የተሻገረ፣ አሁንም ድረስ ያልተቀረፈ አስተሳሰብ ነው፡፡ ብዙ ሰው መግደል ማለት ጦርነትን ማሸነፍ ማለት አይደለም፡፡ ብዙ ሠራዊት ያላቸው፣ ብዙ የጦር መሣሪያ የታጠቁ ሁሉ ብዙ ሰው ይገድሉ ይሆናል እንጂ ጦርነትን ያሸንፋሉ ማለት አይደለም፡፡ ምክንያቱም እውነተኛ አሸናፊነት፣ እውነተኛ ድል የሚገኘው እግዚአብሔርን ከሚያምን ንጉሥ፣ እግዚአብሔርን ከሚያምኑ ሠራዊት ወይም ከእውነተኛ ተዋጊዎች ነውና፡፡

ድል የሚነሡት ‹‹ድል መንሣት ዕውቀትም ካንተ ይገኛል፤ ጌትነትም ያንተ ገንዘብ ነው፤ እኔም ያንተ ባሪያ ነኝ›› የሚሉ ነገሥታትና ሠራዊት ናቸውና፡፡ (ዕዝ.ካልእ ፬፥፶፱)

ጣሊያን መካናይዝድ ጦር አሰልፎ፣ የሠለጠነ ሠራዊት አሰማርቶ፣ ዘመኑ ያፈራቸውን ትጥቆች ታጥቆ በባዶ እግራቸው በሚሄዱት፣ ሰይፍና ጎራዴ በታጠቁት ሊሸነፍ የቻለው ኢትዮጵያውያኑ ‹‹ድል መንሣት በእግዚአብሔር ኃይል ነው›› ብለው በመግጠማቸው ነው፡፡(፩ኛ መቃ.፳፩፥፫) ቁም ነገሩ ስለ ጣሊያን ሽንፈት ሳይሆን ስለ ኢትዮጵያውያኑ አሸናፊነትና የሥነ ልቡና የበላይነት ምክንያቱን ማንሣት ስለሆነ ቤተ ክርስቲያን በእምነት፣ በሥነ ልቡና፣ በአብሮነት፣ የገነባችው ሰብእና አድዋ ላይ አሸናፊ ሆኗል፡፡

ባለ ርእይ የነበሩ ሊቃውንቶቿ በጸሎት ተግተው፣ ራእይ አይተው፣ በቅኔያቸውና በስብከታቸው የጦርነቱን አይቀሬነት እየገለጹ፣ ዝግጅት እንዲደረግ እያሳሰቡና የሥነ ልቡና ግንባታ ሲያደርጉ ቆይተዋል፡፡ ኢትዮጵያውያን አድዋ ላይ ታሪክ መሥራታቸው ቤተ ክርስቲያን በአማኞቿ ላይ በሠራችው ሥራ በገነባቸው የሥነ ልቡና የበላይነትና የአሸናፊነት መንፈስ ነው፡፡

የሮም ካቶሊክ መሣሪያ ባርካ ለወረራ ልካለች፤ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ደግሞ ሠራዊቱን በጸሎት ባርካ ራስን፣ ሀገርን፣ ሃይማኖትን ለመከላከል ልካለች፤ ካቶሊክ በመሣሪያ ተማምናለች፤ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ደግሞ በጸሎት ተማምናለች፤ እነርሱ በታንክ ሊያሸንፉ መጡ፤ እኛ በታቦት ልናሸንፍ ታቦት ተሸክመን ወጣን፤ እኛም አሸነፍን፤ እነርሱም ተሸነፉ፡፡ ቤተ ክርስቲያን በእግዚአብሔር መታመንን አስተማረች፤ ካቶሊክ በሠራዊትና በመሣሪያ ታምኖ ለወረራ የሚሄድን ባርካ ሸኘች፡፡ እናም ምዕራባውያኑ እስከ ክፉ መሻታቸው ተሸነፉ፡፡ አሸናፊነት ከእግዚአብሔር ነውና፡፡ መጽሐፍ እንደ ተናገረ ‹‹አንተ ከሠራዊታቸው ጋር በከሃሊነትህ አጠፋሃቸው፤ ቤተ መቅደስህን ያጎሳቁሉ ዘንድ የስምህ ጌትነት ማደሪያ የሆነች ደብተራ ኦሪትንም ያሳድፉ ዘንድ መክረዋልና በብረትም የመሠዊያህን ቀንዶች አፍርሰዋልና›› ይላል፡፡ (ዮዲት ፱፥፰)

ሌላኛው የአድዋ ድል ምክንያት ደግሞ ካህናቱ ዘምተዋል፤ ሊቃውንቱ ዘምተዋል፤ ታቦቱ ዘምቷል፤ በየድንኳኑ ሰዓታት እየቆሙ ቅዳሴ እየቀደሱ፣ የሚያቆርቡ ነበሩ፤ የሞቱ እየተፈቱ በጸሎትና በምሕላ፣ በሞራልና በስንቅ ንጉሡንና ሠራዊቱን እየተራዱ ብዙ ሥራ የሠሩ የቤተ ክርስቲያን አባቶች ናቸው፡፡ የጦርነቱን ፍትሐዊነት፣ ለሃይማኖት፣ ለርስት፣ ለሚስት፣ ለልጅ ተብሎ የሚከፈል መሥዋዕትነት መሆኑን እና አሸነፊነት ደግሞ ከእግዚአብሔር መሆኑን፣ ቤተ ክርስቲያን አስተምራለች፤ አበረታታለች፤ ብዙዎቹም ሊቃውንትና ካህናት ከአርበኞች ጋር በግንባር ተሠውተዋል፤ አጥንታቸውን ከስክሰዋል፤ ደማቸውን አፍስሰዋል፤ ይህም ለተዋጊዎች ኃይልና ብርታት ሰጥቷቸዋል፡፡

በመጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ የሚል፤ ታሪክ አለ፡፡ ‹‹ሳሙኤልም የሚቃጠለውን መሥዋዕት ሲያሳርግ ፍልስጥኤማውያን ከእስራኤል ጋር ሊዋጉ ቀረቡ፤ እግዚአብሔርም በዚያች ቀን በፍልስጥኤማውያን ላይ ታላቅ ነጎድጓድ አንጎደጎደ፤ አስደነገጣቸውም፤ በእስራኤል ፊት ድል ተመቱ›› ይላል የሚገርም ነው፡፡ (፩ኛ ሳሙ.
፯፥፲) አድዋ ላይ የሆነውም ይህ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ካህናትም በጦር ግምባር በድንኳን በቅዱስ ጊዮርጊስ ታቦት ላይ የሚቃጠለውን መሥዋዕት ሲያሳርጉ፣ ንጉሡም ቅዳሴውን ሲያስቀድሱ፣ የልዳው ኮከብ የፋርሱ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ በጣሊያኖቹ ላይ አንጎደጎደባቸው፤ አስደነገጣቸውም፡፡ በእነዚያ ልበ ሙሉዎች ጎራዴ ይዘው በመድፍ ፊት በሚቆሙ ደፋሮች ኢትዮጵያውያን ድል ተመቱ፡፡

የአድዋ ድል ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በገነባችው የመንፈሳዊ ሥነ ልቡና ብርታትና ለሀገርና ለሃይማኖት እስከ ሞት የመጋደል ወኔ የተገኘ መሆኑ ከድሉ እኩል መነገር ያለበት ነው። ኢትዮጵያውያን የኢጣሊያን ወረራ በሀገረ እግዚአብሔር ላይ እንደ ተደረገ ሰይጣናዊ ጥቃት ነበር የቈጠሩት።

እነሆ ዛሬ እኛ የድል አድራጊዎች ልጆች ተባልን፤ “ነጭም” “በጥቁር” ተሸነፈ፤ የነጻነትን ጣዕም ጥቁሮች ቀመሱ፤ የነጭ ፍልስፍና ተሻረ፤ ሰውን ያህል ፍጡር ባሪያ የሚያደርገው፣ አንዱን ገዥ ሌላውን ተገዥ የሚያስብለው የቅኝ ገዥዎች አስተሳሰብም ታሪኩ በጥቁር መዝገብ ተጻፈ፤ ይህም ከሆነ እነሆ ፻፳፰ ዓመታት ተቆጠሩ፡፡ አባቶቻችን ድል አድርገው ታሪክ ሠሩ፤ እኛ ደግሞ ድል ማድረግ፣ ታሪክ መሥራት ቀርቶ ታሪክን መሸከም ከብዶን ለመውደቅ እንፍገመገማለን፡፡

አድዋ አንድነት ነው፤ አድዋ እኩልነት ነው፤ አድዋ ነጻነት ነው፡፡ አድዋ የድሉ ባለቤቶችን መዘከር ነው፡፡ እነዚህን ዘንግቶ፣ የድሉ ፊታውራራዎችን በማንኳሰስ፣ የቤተ ክርስቲያንንም ሚና በመዘንጋት የሚከበር የአድዋ በዓል ትርጉም አልባና ታሪክን የማጥፋት ሴራ ነው፡፡

ለሀገርና ለሃይማኖት የተሠዉትን ሁሉ ነፍሳቸውን ይማርልን።

ጽሑፉን ለማሰናዳት የማኅበረ ቅዱሳንን ድረገጽ እንዲሁም ሐመር መጽሔትን ተጠቅመናል።
ገራሚ ጥያቄ ነው ለሸኪ የቀረበው ሙስሊም ክርስቲያኑም ቢሰማ ይጠቀምበታል 🙏
ሾይጧን ታስሯል ተብሎ የለ እንዴ 😂😳
የመግሪብ አዛን ውስጥ ነው 😂😍🫠😋
ማሜይዝም ይለምልም 💪😂😂
የጎሠቆለ ባሕርይ (Fallen Nature)

ይህን ጉዳይ ትንሽ ዘርዘር አድርጎ ለመረዳት አዲሱን "ዐይነ ልቡና" የሚለውን መጽሐፌን ይመልከቱ። አምስት ኪሎ "ሰርዲኖስ የመጻሕፍት መደብር" ዋና አከፋፋይ ኾኖ በሌሎችም የመጻሕፍት መደብር ታገኙታላችሁና። ዛሬ በአጭሪ ላቀርብ ወዳሰብኹት ጉዳይ ልግባ።

የጎሠቆለ ባሕርይ የሚባለው በዋነኛነት አዳም ከበደለ በኋላ የኾነው ነው። አዳም ከውድቀቱ በኋላ የሰውነት ባሕርዩ አልተለወጠም። ከውድቀት በፊት ኾነ ከውድቀት በኋላ በሰውነት ለውጥ የለምና። ነገር ግን ከውድቀት በፊት በንጹሕ ባሕርይ መልክአ እግዚአብሔሩ ሳይደክም፤ የጸጋ ልብስን ለብሶ በፍጥረት ላይ የገዥነትን ሥልጣን ተጎናጽፎ በክብር ይኖር ነበረ። ሕገ እግዚአብሔርን ተላልፎ በወደቀ ጊዜ ግን የባሕርይ ውድቀት (ሕማም) ወይም ንዴተ ህላዌ (የባሕርይ ድህነት) ገጠመው።

- Fallen Nature በዋነኛነት የመልክአ እግዚአብሔር መድከምን፦ አዳም የተፈጠረው በእግዚአብሔር መልክ ነው። ያን በተፈጥሮ የተሰጠውን መልክአ እግዚአብሔር ሙሉ በሙሉ ባያጣውም በሕግ መተላለፉ ምክንያት አደከመው። አንዱና ዋነኛው የጎሠቆለ ባሕርይ ምልክት ይህ ነው። ኹለተኛው የጎሠቆለ ባሕርይ የሚባለው ከጸጋ እግዚአብሔር የተራቆተ፦ ማለትም እግዚአብሔር አልብሶት የነበረውን የብርሃን ልብስ ያወለቀ፥ የእግዚአብሔር ልጅነትን ያጣ ባሕርይ ነው። ሦስተኛ ከባሕርዩ መጎሥቆል የተነሣ ለኃጢአት የሚያዘነብል መኾን ነው። አራተኛ ጉሥቁል ባሕርይ ያለው ሰውነት ርግማንን ተሸክሟል። ይኸውም መርገመ ሥጋ መርገመ ነፍስ ነው። በሥጋው ወደ መቃብር ገብቶ መበስበስ (ሞተ ሥጋ)፤ በነፍሱ ወደ ሲኦል መግባት ነው (ሞተ ነፍስ) ዋናው ሞተ ነፍስ ከእግዚአብሔር መለየት ገጥሟቸዋል። ስለ ርግማን ሞት ስናነሣ በዋነኛነት የነፍስ ከሥጋ መለየትን ብቻ ሳይኾን የሥጋን ወደ መቃብር ገብቶ መበስበስ፣ የነፍስን ከእግዚአብሔር መለየት (ሞታ ለነፍስ ርሒቅ እም እግዚአብሔር እንዲል ሊቁ ቅዱስ ያሬድ) ይህን ይመለከታል። የሐዲስ ኪዳንን ሞት ለመረዳት "ዐይነ ልቡና" የምትለውን መጽሐፌን ይመልከቱ። እነዚህ በመሠረታዊነት ሰውነትን የጎዱና ያደከሙ ናቸው።

-በባሕርዩ መጎሥቆል ምክንያት የመጡ ጎጂ ያልኾኑ ኹኔታዎች ወይም ሕማማት ዘአልቦቱ ኃጢአት (blemeless Passions) ኃጢአት አልባ ሕማማትን መቀበል ግን በአምላካችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስለኛ ተብሎ በፈቃዱ ለቤዛነት ብሎ የተቀበላቸው ናቸው፤ እመቤታችን ደግሞ ሰው እንደ መኾኗ ያን እንድትቀበል ልጇ ወዳጇ ኢየሱስ ክርስቶስ ፈቅዷል። ስለዚህም ተርባለች፣ አዝናለች፣ ተሠቃይታለች፣ ሞታለች። እነዚህ ኹኔታዎች በራሳቸው ኃጢአቶች አይደሉም። እንደ ነውርና ርኲሰትም አይቆጠሩም። ጌታችንም እነዚህን ስለኛ ብሎ የተቀበለው በዚህ ምክንያትና ስለኛ ቤዛ ሊኾነን ነው። ይሄን የተቀበለው ደግሞ ሥግው ቃል እንደ መኾኑ ነው። ስለኛ መራቡን፣ መጠማቱን፣ መገረፉን፣ የእሾህ አክሊል መቀዳጀቱን፣ መራራ ሆምጣጤ መጠጣቱን፣ በመስቀል ላይ ዕርቃኑን መሰቀሉን፣ መሞቱን በእውነት የተቀበላቸው ቤዛ ሊኾነን እንጂ ያን በመቀበሉ ምክንያት የጎሠቆለ ባሕርይን ለብሷል ለመሰኘት አይደለም። ቃል ከሥጋ ከተዋሐደ በኋላ ሥግው እንደ መኾኑ ለቤዛነት የተቀበላቸውን ነገሮች የማዳን ሥራ (Economy of Salvation) እንላለን እንጂ በሌላ መንፈስ እንዲታይ ፈጽሞ አናደርግም።

እነዚህን ነገሮች ሥግው ቃል በፈቃዱ ያደረጋቸው ናቸው። ብዙ ቅዱሳን ሊቃውንትም ቅዱስ ቄርሎስ፣ ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ፣ ቅዱስ ያሬድ፣ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ... "ኅሥሩ" -"ጉሥቁል" ሥጋን ነሣ ሲሉ በአንድ በኩል ከደካማው አዳም ሰውነት የተከፈለውን ሰውነት መንሣቱን ለማሳየት ሲኾን በሌላ በኩል በፈቃዱ ሕማም፣ መከራና ሞት የሚስማማውን ሰውነት ገንዘብ ማድረጉን ለማመልከት ነው። ከዚህ ውጭ ከላይ በዋነኛነት የወደቀ ባሕርይን የሚገልጡ ነገሮች ያሉበትን ሰውነት ለበሰ ለማለት አይደለም። ለዝርዝሩ "ዐይነ ልቡናን" ይመልከቱ። በነገራችን ላይ አኹን እንኳን እኛ ኦርቶዶክሳውያን አምነን፣ ተጠምቀን በቅብዐ ሜሮን ከብረን ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ተቀብለን የክርስቶስ አካል ከኾን በኋላ blemeless passions የሚባሉት ያልቀሩልን በራሳቸው ክፉዎች ስላልኾኑ ነው። እነዚህ ነገሮች አዲስ ሰውነትን ገንዘብ አለማድረግን የሚያመለክቱ አይደሉም። ይኸውም ማለት በጥምቀት ከአሮጌ ማንነት ወጥተን ክርስቶስን ለብሰን አዲስ የምንኾን መኾናችንን የሚያስቀሩ አይደሉምና። ከአሮጌ ማንነት በጥምቀት ከተላቀቅን በኋላ መልሰን ባረጀ ሰውነት ውስጥ እንዳለን አድርገን አንናገርም። በትንሣኤ አኹን ከለበስነው የበለጠ የከበረ ኢመዋቲ ኢድኩም ወኢሕሙም የኾነ ሰውነትን መልሳችንን ፍጽሙ ድኅነት ከትንሣኤ በኋላ መኾኑን የሚያረጋግጥ እንጂ አኹን ብትጠመቁም አሮጌ ማንነት ውስጥ ነው ያላችሁ የሚያስብል አይደለም። ሌላው ቀርቶ ያን አዳም በገነት እያለ ያወለቀውን የብርሃን ልብስ ስንጠመቅ እንለብሰዋለን (በተለይ ቅዱስ ኤፍሬምና ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ በትኩረት ይህን ያስተምራሉና) ነገር ግን ለኛ ለዐይነ መጭማጮች ከተጠመቅንም በኋላ ያን የብርሃን ልብስ መልበሳችን አለመታየቱ ያለመልበሳችን ማረጋገጫ ሊኾን አይችልም። ነገር ግን በግልጽ አኹን ያን ልብስ መልበሳችንን ማየት ባንችልም ከትንሣኤ በኋላ ተገልጦ እናየዋለን። ያኔ የሚገለጠው ግን ላልተጠመቁ ሳይኾን በጥምቀት ለከበሩት ክርስቶስን ለለበሱ ነው። ይህን ልብ ማለት ይገባል።

- አካላዊ ቃል የተዋሐደው ሥጋ ንጹሕ ሥጋ ነው። ምንም ዓይነት ነውርና ነቀፋ የለበትም። መንሣትና መዋሐድ ያለመቀዳደም የኾነ ስለ ኾነ ከእመቤታችን የነሣው ሰውነት ንጹሕና ነውር ነቀፋ የሌለበት ነው። የኃጢአት ጠባሳም አላገኘውም። ጸጋን የተመላ፣ መልክአ እግዚአብሔሩ ያልደከመ፣ ኃጢአት ያልገዛው፣ መርገም ያላረፈበት ንጹሕ ሰውነት ነው። ቅድስት ድንግል ማርያም የተጠበቀችው የጉሥቁልና ውጤት ከኾነው ከጸጋ መራቆት፣ ከመልክአ እግዚአብሔር መድከም፣ ለኃጢአት ከማዘንበል፣ ከመርገመ ሥጋ ወነፍስ፣ ከልማደ አንስት በወሊድ ጊዜ ከሚመጣ ምጥ ኹሉ ነው። ይህ ከእርሷ በቀር ከሰው ወገን ለማንም ቀድሞ የተደረገ አይደለም። ስለዚህም ምክንያት በዋነኛው የውድቀት ምልክት አንጻር አድርገን ስናይ እርሷ የወደቀ ሰውነትን ገንዘብ እንዳታደርግ ልጇ ጠብቋታል እንላለን። የእርሷን ሕይወት በልዩ ኹኔታዎች እንዲመላ ያደረገው እርሱ አምላኳ ነውና። የጎሠቆለ ሰውነትን አልለበሰችም ስንል ሕማም፣ ኀዘን፣ መከራ፣ ሞት የማይስማማውን ሰውነት ገንዘብ አድርጋለች ማለታችን አይደለም። ይህን የሚልም አይኖርም ይልቅስ ከላይ እንዳልኹት ከዋነኛው የጒሥቁልና ውጤት መጠበቋን ማዕከል በማድረግ የወደቀ ሰውነትን አልለበሰችም እንላለን። አበውም ያስተማሩት በዚህ አግባብ ነው። በዝርዝር የእርሷን ጉዳይ ለመረዳት "ዐይነ ልቡና" ይነበብ። ልጇ በፈቃዱ ስለኛ የሞተው በማስመሰል ሳይኾን በአማን ነው። ሞትንም በፈቃዱ የተቀበለው ያ ሥጋ የዕሩቅ ብእሲ ሥጋ ሳይኾን የሥግው ቃል ሥጋ ነውና። ሞትን ስለኛ የተቀበለው ሥጋ ራሱ ለኛ ሕይወትን የሚያድል ነው። የሞተውም ሊበሰብስ ሳይኾን ሞትን በሞቱ ገድሎ ሞት የወረሰውን ሰውነት ሕይወት ሊያለብሰው ነው። ይህ የቅዱስ አትናቴዎስና የቅዱስ ቄርሎስ የትምህርት ማዕከል ነው።

እመቤታችን ለምን ሞተች? መልሱ በአጭሩ፦
1) የሞተችው ለመበስበስ ሳይኾን የትንሣኤን አካል ገንዘብ ለማድረግ ነው። ይኸውም ኢመዋቲ አካልን ገንዘብ ለማድረግ እንጂ ለመበስበስ አይደለም። ይህ ዮሐንስ ዘደማስቆ በመደነቅ የገለጸው ነው። ሰውነቷ እንዲበሰብስ ልጇ አለመፍቀዱን ሞታ መበስበስ ሳያገኛት ከልጇ ትንሣኤ በኋላ በልጇ ሥልጣን በሦስተኛው ቀን መነሣቷን ብዙዎቹ ቅዱሳን ሊቃውንት የገለጹት እና እኛም የምናምነው ነው።

2) የሞተችው ሰው ስለ ኾነች ነው። አምላክ በመውለዷ ምክንያት በሕሊናቸው ሰው አይደለችም የሚሉ ሰዎች እንዳይኖሩና በእርሷ ሰው የመኾን ጉዳይ ጥርጣሬ እንዳይፈጠር ሞትን ትቀምስ ዘንድ ልጇ ፈቅዷል። ይህ እነ አብሮኮሮስ በአጽንዖት ያስረዱት ነው። ይህ ምክንያት ቃል ሰው አልኾነም የሚለውን ክሕደትናና እርሷም ሰው አይደለችም የሚለው ስሕተት የሚያርም ነው።

3) ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ እንዳለው ያረፈችው የልጇን የሞት ጽዋ ለመቅመስ ነው። ይህም እንዲኾን የእርሱ ፈቃድ ነው።

4) ሞቷ የመሸነፍ ሳይኾን የክብር እና የድል እንደ ኾነ እንድናውቅ ነው። ይህን ለመረዳት የሞቷን ዜና ከልጇ ዘንድ የተላከው ቅዱስ ገብርኤል ሊያበሥራት ሲመጣ የድል ምልክት የኾነውን የዘንባባ ዝንጣፊ ይዞ መምጣቱን እነ ማክሲሞስ ተናዛዚው የቀደሙ ትውፊቶችን ማዕከል አድርገው "The Life of The Virgin" በሚለው መጽሐፍ ዘግበዋልና።

5) ሞቷ ተራ ሞት ሳይኾን በመደነቅና በመገረም የሚናገሩት ሞት ነው። ቅዱስ ያሬድ "ማትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ ለማርያም የአጽብ ለኲሉ" - ሞትማ ለሚሞት ይገባል የማርያም ሞት ግን ለኹሉ ያስደንቃል" የሚለው ለዚህ ነው። እንደ በሥጋና በደም ኾነን በድፍረት ከመናገር ልንቆጠብና ልናደንቅ ይገባል።
ማሜይዝም ይለምልም 💪😜
40 ገርፈን ቀይደር ካልተጠመቁ እና ቀኖና ካልተሰጣችሁ .....
ቅዳሜ እና እሁድ መስቀል አደባባይ ሰለዋት ካልሰገዳችሁ የሚል ወሂ ወርዶልኛል 😎


እኔ እምለው ክርስቲኖች ላይ የሚያቅራሩት #አብዱሎች እኛ በሶ የጨበጥን መስሏቸው ነው 😳
ወደ ሀገራችን ኢትዮጵያ የመጡት Franklin Graham ትውልድ ቀዬያቸው መለኮታዊ ጥሪ ርቆታል።
Franklin አሜሪካዊ ናቸው። በሀገራቸው አሜሪካን ሀገር 65 በመቶ ከቁጥጥራቸው ውጪ ነው (ፕሮቴስታንት የሚለውን እንደው ብንቀበለው)። የሚገርመው ደግሞ እግዚአብሔር የለም የሚል Etheist 95 ሚሊዮን ፤ በአምላክ ስጦታ አናምንም በማለት ጾታቸውን የቀየሩ፤ ግብረ ሰዶም ጋብቻ የፈጸሙና ጠቅላላ LGBTQ ደግሞ 23 ሚሊዮን ሕዝብ በጉያቸው ታቅፈዋል። ከዚያው ስንወጣ እሳቸው በተወለዱባት አሜሪካ ግዛት Asheville, North Carolina ከጠቅላላ 94,589 ሰዎች 50% ብቻ ነው ፕሮቴስታንት፤ 35% አምላክ የለምና ወደ ላይ የሚሸኑ ሲሆን የቀረችው 15% ሌላ ሃይማኖት የሚከተሉ ነው።
እንደው ይታያችሁ! ከ2019 ጀምሮ ብቻ ወደ 4,500 የፕሮቴስታንት ቤተ እምነቶች ከተዘጉበት ከተማ ነው የመጡት። በSouthern Baptist Convention (SBC) ደግሞ (ጥናቶች እንደሚያሳዩት) በ2022 ብቻ 50,423 ፕሮቴስታንት ቸርቾች ተዘግተዋል።
ተመልከቱ! ብያንስ የትውልድ ቦታቸውን፤ ከፍ ብለው የሚኖሩባትን ሀገር ወንጌል ሳያሳምኑ ወደ ኢትዮጵያ መጥተው መለኮታዊ ጥሪ ልያቀብሉን። እጅግ በጣም የሚያሳዝነውና ጉዳዩ ትንኮሳ እንደሆነ የሚያረጋግጥልን ደግሞ ትክክለኛ ሥርዓተ አምልኮ ለመፈጸም ሳይሆን መቆሚያ፤ ከበሮና ጸናጽል በመያዝ ወደ መስቀል አደባባይ ወጥተው ጊዜ የሰጣቸው ቅሎች ድንጋይ ለመስበር መሞከራቸው ነው። ጸናጽልና መቆሚያ ለመያዝ ብያንስ ቅዱስ ያሬድን ማወቅና መቀበል ያስፈልጋል።
ይህ መሳለቅና መንግስታዊ ድጋፍን በመተማመን የተደረገ ድፍረት እንጂ ንጹህ አምልኮ አይደለም፤ በዚህ ደግሞ እግዚአብሔር አይከብርም። ነገ ሌላ ቀን ነው!
አንጋፋው የግጥም ደራሲ ይልማ ገ/አብ እንዲህ ብሎ ነበር👇
አበባም አብቦ ሲበቃው ይደርቃል፣
ልብስም አጊጦበት እያጠቡት ያልቃል፤
ሰውም ይክረም እንጂ ቦታውን ይለቃል።
©ደግነህ ዘርፉ
በቤተ መንግስቱ አዳራሽ 1200 ፓስተሮች ሲሰለጥኑበት ዋሉ

በብልፅግና መንግስት ድጋፍ እና ትብብር ዛሬ በቤተ መንግስቱ አዳራሽ 1200 ፓስተሮች " ስልጠና ተሰጥቷቸዋል ።

የስልጠናው ዋና ጭብጥ እግዚአብሔርን ከተከተልክ በቁሳዊ ሀብት መበልፀግ የመባረክህ ምልክት ነው የሚል ነው።
DEWOL ደወል ሚዲያ
አይ ኢቲቪ ስብከት ማስተላለፉ ሳያንስ ጭራሽ ለአፅዕኖተ ነገር እንዲሆን ቆርጦ በድጋሚ “የፍራንክሊን ግራሃም ስብከት” ብሎ ጫነ።

በነገራችን ላይ እንዲህ ያለ መድረክ ቀርቶ በዓመት በሚታወቁና በካሌንደር በሚዘጉ ሃይማኖታዊ በዓላት አከባበር በሚኖር የቀጥታ ሥርጭት የetv ኤድቶሪያል ፖሊሲ ጥቅል ሃሳብ ይህ ነው።

ማንኛውም የሃይማኖት በዓል የቀጥታ ሥርጭት ላይ ስብከት ወይንም ሃይማኖታዊ ትምህርቶች አይተላለፉም። ይህ ግን መልእክቶችንና ክዋኔዎችን አይመለከትም።

ለዚህም ነው ካያችሁ መስቀል ወይ ጥምቀት አከባበር በቀጥታ ሲሰራጭ ስብከት መርሐ ግብር ላይ ጋዜጠኞቹ ተሳታፊ እንግዳ በማስገባት ተሯሩጠው ሚያቋርጡት።

ዛሬ እንደመንፈሳዊ ጣቢያ የእገሌ ስብከት ቢል የቀድሞ ቤቴ ምን አገኘው ብዬ ነው እንጂ ለማን አማው ነበር?

ደግሞም አምቼውም አላውቅ!
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን የጥቃት ዓላማ ያደረጉ የጥላቻ ንግግሮች እንዲቆሙ ምእመናን ጠየቁ !

መጋቢት 1 ቀን 2017 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ)

በተለያዩ የማኅበራዊ ሚዲያ አማራጮች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ዒላማ ያደረጉ የጥላቻ ንግግሮች እና መልእክቶች በአፋጣኝ እንዲቆሙ እና መንግስትም ሕጋዊ እርምጃ እንዲወስድ ቲኤምሲ ያነጋገራቸው ምእመናን ገልጸዋል።

ማናቸውም ቤተ እምነቶች መብቶቻቸው እንዲከበር እንደሚፈልጉትና የሃይማኖታቸውን አስተምህሮ በነጻነት ማስተላለፍ ሕገ መንግስታዊ መብታቸው እንደሆነ የጠቆሙት አስተያየት ሰጪ ምእመናኑ በተመሳሳይም ሁሉም ቤተ እምነቶች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን እምነት እና አስተምህሮ ባከበረ መልኩ ሊንቀሳቀሱ እንደሚገባ ገልጸዋል።

ሁሉም ኢትዮጵያውያን የሃይማኖት ነጻነታቸውን ተጠቅመው በማናቸውም መልኩ ሃይማኖታቸውን ማራመድ ሕገ መኖግስታዊ መብታቸው ቢሆንም የሌላውን እምነት ማንቋሸሽ፣ ማኮሰስ እና ማጥላላት ፈጽሞ ተቀባይነት የሌለው እና ግጭት ቀስቃሽና ጸረ ሰላም እንቅስቃሴ መሆኑ ነው የተገለጸው።

ባለፉት ጊዜያት ከአንዳንድ ቤተ እምነት ተከታዮች ስለ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ፣ ስለ ቅዱሳን፣ ስለ ንዋያተ ቅድሳት ብሎም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት በምታስተምቸው ትምህርቶች ላይ ትኩረት ያደረጉ የጥላቻ ንግግሮች ሲተላለፉ መቆየታቸው የሚታወስ ነው።

በተለይም መዋቅራዊ ድጋፍ እየተሰጠው በሚመስል መልኩ የጥላቻ ንግግሮች ተባብሰው መቀጠላቸው እና ይኸው ጥላቻም በኤሌክትሮኒክስ ሚዲያ ብቻ ሳይሆን በሜንስትሪም እና በመጽሐፍትም ጭምር ሲካሄድ መቆየቱ እና እየተካሄደ መሆኑ በርካታ ምእመናንን ያሳዘነና ያስቆጣ መሆኑ ተመላክቶአል።
2025/07/06 14:00:53
Back to Top
HTML Embed Code: