#ዋዜማ_የኪነ_ጥበብ_መርሐ_ግብር
ቅዳሜ ከቀኑ 8:00 ጀምሮ በወልድ ዋህድ ሰንበት ትምህርት ቤት አዳራሽ ይከናወናል ።
በመርሐ ግብሩ ላይ ከወልድ ዋህድ እና ከሌሎች እህት ሰንበት ትምህርት ቤቶች በተጋበዙ ወጣቶች
👉ቅኔ
👉ስነ ግጥም
👉ወጎች እንዲሁም
👉ጭውውት ይቀርባል ።
በመርሐ ግብሩ ላይ ትሳተፉ ዘንድ ጠርተነዎታል ።
መግቢያ ዋጋ :- #ሰዓት_ማክበር_ብቻ
ቅዳሜ ከቀኑ 8:00 ጀምሮ በወልድ ዋህድ ሰንበት ትምህርት ቤት አዳራሽ ይከናወናል ።
በመርሐ ግብሩ ላይ ከወልድ ዋህድ እና ከሌሎች እህት ሰንበት ትምህርት ቤቶች በተጋበዙ ወጣቶች
👉ቅኔ
👉ስነ ግጥም
👉ወጎች እንዲሁም
👉ጭውውት ይቀርባል ።
በመርሐ ግብሩ ላይ ትሳተፉ ዘንድ ጠርተነዎታል ።
መግቢያ ዋጋ :- #ሰዓት_ማክበር_ብቻ
ኪዳነምህረት በአባቶች ውዳሴ
[የእመቤታችን የየካቲት 16 ቃል ኪዳኗን አስመልክቶ በሊቃውንት የቀረበላት ውዳሴ (ቅዱስ ያሬድ፣ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ፣ አባ ዘመለኮት፣ አባ ጽጌ ድንግል)]
✍️ አዘጋጅ፡- መጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
💥 ቅዱሳን ሊቃውንት የአምላክን እናት አመስግነው በቃኝ አይሉም ነበር በተለይ ከኢትዮጵያ ሊቃውንት ቅዱስ ያሬድ፣ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ፣ አባ ጽጌ ድንግልና አባ ዘመለኮትን በዚህ ክፍል ላይ ስጠቅሳቸው በተለይ የክብር ባለቤት ልጇ በጎልጎታ የምሕረት ቃል ኪዳንን የገባላትን የየካቲት 16 ክብረ በዓሏን አስመልክቶ ከጻፉት ከብዙው በጣም ጥቂቱን የእመቤቴን በረከት ለመሳተፍ ስል አስፍሬዋለሁ፡፡
💥በቅዱስ ያሬድ💥
❤ ቅዱስ ያሬድ በድጓው በተለይ በዐጫብር ድጓ ዘኪዳነ ምሕረት ውስጥ ከተጻፈው፡-
✍️ “ለብእሲ ዕሩቅ እምልብሰ ምግባር
ታዕድዊዮ እምገሃነም ባሕር
ኦ ድንግል በኪዳንኪ ሐመር”
(ድንግል ሆይ በቃል ኪዳንሽ መርከብ ከምግባር ልብስ የተራቈተውን ሰው ከገሃነመ እሳት ባሕር ታሻግሪዋለሽ)
✍️ “ብእሲ ቅሩብ ለሙስና
ለድንግል በኪዳና
በመንግሥተ ሰማይ ዘኢይጸልም ብርሃና
ይረክብ ሕይወተ ዕረፍት ወጥዒና”
(ለጥፋት የቀረበ ሰው ለድንግል በተሰጣት ኪዳን፤ ብርሃኗ በማይጨልም በመንግሥተ ሰማይ ዕረፍትና ጤንነትን ያገኛል)
✍️ “ክነፈ ርግብ በብሩር ዘግቡር ወገበዋቲሃኒ በሐመልማለ ወርቅ
አንቲ ምሥራቅ ወወልድኪ ፀሐየ ጽድቅ
አማን ኪዳንኪ ኢየሐልቅ”
(በብር የተሠራች የርግብ ክንፍ ጐኖቿ በወርቅ ዐመልማሎ የተሸለመች አንቺ በምሥራቅ ስትመሰዪ ልጅሽ የእውነት ፀሐይ ነው፡፡ በእውነት ቃል ኪዳንሽ አያልቅም)፡፡
✍️ “አዕረግዋ መላእክት እምድር ውስተ ሰማያት በክብር ወበስብሐት
በእንቲኣነ ከመ ትስአል እምወልዳ ኪዳነ ምሕረት”
(ስለ እኛ ከልጇ የምሕረት ኪዳንን ትለምን ዘንድ በክብር በምስጋና መላእክት ከምድር ወደ ሰማያት አሳረጓት፡፡)
✍️ “ይቤላ ለእሙ ማርያም እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ተካየድኩ ምስሌኪ ኪዳነ ምሕረት ከመ አድኅን ዘተአመነኪ መሐልኩ ለኪ በርእስየ ዘመሐልኩ አነ ለኖኅ ገብርየ ወለአብርሃም ፍቁርየ፤ ዘመሐልኩ አነ ለዳዊት ኅሩይየ ብእሲ ምእመን ዘከመ ልብየ መሐልኩ ለኪ በርእስየ በቅዱስ ሥጋየ ወበክቡር ደምየ መሐልኩ ለኪ በርእስየ ከመ ኢይሔሱ ማእኰትየ”
(ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እናቱ ማርያምን እንዲኽ አላት በምልጃሽ ያመነብሽን አድን ዘንድ ካንቺ ጋራ የምሕረት ቃል ኪዳንን ተጋባኊ፤ ለአገልጋዬ ለኖኅና ለወዳጄ ለአብርሃም ቃል የገባኊ እኔ በራሴ ማልኹልሽ፤ እንደ ልቤ ለምለው ለታመነው ለዳዊት የማልኊ እኔ በራሴ ማልኹልሽ፤ በቅዱስ ሥጋዬና በክቡር ደሜ የማልኊ እኔ ምዬ እንደማልከዳ ማልኹልሽ)
💥💥💥
💥 አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ💥
✍️ድካመ ጌጋይየ ትማእ ማርያም ጽድቀ ዚኣኪ በጽንዓ
መዳልወ ጥበብ ሶበ መልኣ ሰማኒተ ነፍሳተ ወሰብዓ
ሕፍነ ማይ ኀየለ ወሞአ”
(ማርያም የአንቺ ጽድቅ የበደሌን ድካም ድል ትነሣ ዘንድ የጥበብ (የምስጢር) ሚዛኖች በመሉ ጊዜ እፍኝ ውሃ ሰባ ስምንት ነፍሳትን ፈጽሞ ድል ነሣ፡፡)
✍️ “በከመ ልማድኪ በሊ ኀበ ወልድኪ ከሃሊ
ኦ ርኅሩኅ ኢተበቃሊ
ያጠፍኦኑ ለሥዕሉ ሠዓሊ
ኪነተከ ዘትካት ኀሊ”
(እንደ ልማድሽ ኹሉን የሚችል ወደሚኾን ልጅሽ የማትበቀል ቸር ሆይ፤ ሠዓሊ ሥዕሉን ያጠፋዋልን? የቀድሞ ፍጥረትኽን ዐስብ በዪ)።
✍️ “ጊዜ ጸልዮትኪ በጽሐ ከመ ኢይሙት ገብርኪ
ቅድሜሁ ስግዲ ወአስተብርኪ
እንዘ ታዘክሪዮ እምጻማ ንግደትኪ
ርግብየ የዋሂት ለየዋህ ወልድኪ”
(ደገኛዪቱ ርግቤ ለደገኛው ልጅሽ የእንግድነትሽን ድካም እንደ እናት እያሳሰብሺው፤ በፊቱ ፍጹም ስገጂ፤ አገልጋዪሽ እንዳይሞት የጸሎትሽ ጊዜ ደረሰ)።
✍️ “እሙ በሊዮ በእንቲኣየ ለፍሬ ከርሥኪ እብኖዲ
ላዕሌሁ ምሕረተ ኢታጐንዲ
እመ አሕዘነከ ብእሲ አባዲ
ቤዛ ነፍሱ ንጽሕየ እፈዲ”
(የጌታዬ እናት የማሕፀንሽ ፍሬ እብኖዲን ስለ እኔ እንዲኽ በዪው በርሱ ላይ ይቅርታን አታዘግዪ፤ ሰነፍ ሰው ቢያሳዝንኽም የነፍሱን ምትክ ንጽሕናዬን ዋጋ አድርጌ እከፍልለታለኊ)።
✍️ “አንቲ ውእቱ ለእግዚአብሔር አትሮኑሱ
ለአዳም ክብረ ሞገሱ
በኪዳንኪ ኃጥኣን መንግሥተ ሰማያት ይወርሱ"
(የእግዚአብሔር አትሮንሱ (ዙፋኑ) የአዳም የግርማው ክብር አንቺ ነሽ፤ ኃጥኣንም በቃል ኪዳንሽ መንግሥተ ሰማያትን ይወርሳሉ)።
💥💥💥
💥 አባ ጽጌ ድንግል 💥
✍️ “ሚ ሠናይ ከመ ጼና ጽጌ ልሑይ
በኲሉ ጊዜ ምሒረ ነዳይ
በእንተ ኪዳንኪ ድንግል ለበላዔ ሰብእ ጊጉይ
ሶበ ዐብየ እምኀጢአቱ ክበደ መድሎቱ ለማይ
ለተአምርኪ በሰማይ ተገብረ ግናይ”
(ኹል ጊዜ ለደኻ መራራት መመጽወት እንደ ለመለመ አበባ ያማረ ነው (ምን ያምር?) ድንግል በቃል ኪዳንሽ ምክንያት ከበላዔ ሰብእ ኀጢአት የውሃ ሚዛን በልጦ በመታየቱ ለተአምርሽ በሰማይ ምስጋና ኾነ)።
✍️ “በከመ ይቤ መጽሐፍ ማእከለ ፈጣሪ ወፍጡራን
ለዕረፍት ዘኮንኪ ትእምርተ ኪዳን
ሰንበተ ሰንበታት ማርያም ዕለተ ብርሃን
ብኪ ይትፌሥሑ ዘገነተ ጽጌ ጻድቃን
ወብኪ ይወጽኡ ኃጥኣን እምደይን”
(መጽሐፍ እንደተናገረ በፈጣሪና በፍጡራን መካከል ለዕረፍት የኪዳን ምልክት የሆንሽ የብርሃን ዕለት የሰንበታት ሰንበት ማርያም በአንቺ የገነት አበባ ጻድቃን ይደሰታሉ፡፡ ኃጥአንም በአንቺ ምልጃ ከሲኦል ይወጣሉ)፡፡
💥💥💥
💥የመልክአ ኪዳነ ምሕረት ደራሲ አባ ዘመለኮት💥
✍️ “ሰላም ለዝክረ ስምኪ ዘአስተማሰልዎ በኮከብ
ሶበ ብርሃኖ ተከድኑ ጽልሙታነ ራእይ ሕዝብ
ኪዳነ አምላክ ማርያም ወተስፋ መድኀኒት ዘዐርብ
ተናዘዘ ብኪ አኮኑ ኅሊና ቀዳማይ አብ
አመ እምገነቱ ተሰደ በሐዘን ዕጹብ”
(ለጨለመባቸው ወገኖች ብርሃኑን ባሳየ ጊዜ በኮከብ የመሰሉት ለኾነ ለስም አጠራርሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ የዐርብ የመድኀኒት ተስፋ የአምላክ ኪዳን ማርያም ሆይ በሚያስጨንቅ ሐዘን ከገነቱ በተሰደደ ጊዜ የመዠመሪያው ሰው ኅሊና ባንቺ ተረጋጋብሽ እኮን)።
✍️ “ሰላም ለአእዛንኪ እለ ተበሥራ ኪዳነ
እምአፈ ፈጣሪ ወልድኪ ዘባሕርየኪ ተከድነ
አምሕለኪ ማርያም ከመ ኢታርእዪኒ ደይነ
እንበለ ምግባር ባሕቱ እመ ኢይጸድቅ አነ
ቦኑ ለከንቱ ኪዳንኪ ኮነ”
(ባሕርይሽን ከተዋሐደ ከፈጣሪ ልጅሽ አንደበት የኪዳን ምሥራችን ለተበሠሩ ጆሮዎችሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ ያለምግባር የማልጸድቅማ ከኾነ በውኑ ኪዳንሽ ለከንቱ ይኾናልና ማርያም ሆይ ፍርድን እንዳታሳዪኝ አምልሻለኊ)።
✍️ “ማርያም ኅሪት እምነ መላእክት ወሰብእ
ተዝካረኪ ለእመ ገብረ በተአምኖ ጽኑዕ
በመንግሥተ ሰማይ ምስሌኪ ይነግሥ ኃጥእ”
(ከመላእክትና ከሰዎች ይልቅ የተመረጠሸ ማርያም ሆይ መታሰቢያሽን በብርቱ መታመን ያደረገ በመንግሥተ ሰማይ ካንቺ ጋር ይነግሣል) በማለት አወድሰዋታል፡፡
💥 እኛም በረከቷ ይደርብን ጸሎቷ ይጠብቀን፡፡ በአስተያየት መስጫው ላይ የአምላክ እናት በተሰጣት ቃል ኪዳን ትጠብቃችሁ ዘንድ በምትወዱት መዝሙር ግጥም ወይም በምትወዱት የምስጋና ጸሎት አመስግኗት።
✍️ መጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ (በድጋሚ የተለጠፈ)
[የእመቤታችን የየካቲት 16 ቃል ኪዳኗን አስመልክቶ በሊቃውንት የቀረበላት ውዳሴ (ቅዱስ ያሬድ፣ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ፣ አባ ዘመለኮት፣ አባ ጽጌ ድንግል)]
✍️ አዘጋጅ፡- መጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
💥 ቅዱሳን ሊቃውንት የአምላክን እናት አመስግነው በቃኝ አይሉም ነበር በተለይ ከኢትዮጵያ ሊቃውንት ቅዱስ ያሬድ፣ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ፣ አባ ጽጌ ድንግልና አባ ዘመለኮትን በዚህ ክፍል ላይ ስጠቅሳቸው በተለይ የክብር ባለቤት ልጇ በጎልጎታ የምሕረት ቃል ኪዳንን የገባላትን የየካቲት 16 ክብረ በዓሏን አስመልክቶ ከጻፉት ከብዙው በጣም ጥቂቱን የእመቤቴን በረከት ለመሳተፍ ስል አስፍሬዋለሁ፡፡
💥በቅዱስ ያሬድ💥
❤ ቅዱስ ያሬድ በድጓው በተለይ በዐጫብር ድጓ ዘኪዳነ ምሕረት ውስጥ ከተጻፈው፡-
✍️ “ለብእሲ ዕሩቅ እምልብሰ ምግባር
ታዕድዊዮ እምገሃነም ባሕር
ኦ ድንግል በኪዳንኪ ሐመር”
(ድንግል ሆይ በቃል ኪዳንሽ መርከብ ከምግባር ልብስ የተራቈተውን ሰው ከገሃነመ እሳት ባሕር ታሻግሪዋለሽ)
✍️ “ብእሲ ቅሩብ ለሙስና
ለድንግል በኪዳና
በመንግሥተ ሰማይ ዘኢይጸልም ብርሃና
ይረክብ ሕይወተ ዕረፍት ወጥዒና”
(ለጥፋት የቀረበ ሰው ለድንግል በተሰጣት ኪዳን፤ ብርሃኗ በማይጨልም በመንግሥተ ሰማይ ዕረፍትና ጤንነትን ያገኛል)
✍️ “ክነፈ ርግብ በብሩር ዘግቡር ወገበዋቲሃኒ በሐመልማለ ወርቅ
አንቲ ምሥራቅ ወወልድኪ ፀሐየ ጽድቅ
አማን ኪዳንኪ ኢየሐልቅ”
(በብር የተሠራች የርግብ ክንፍ ጐኖቿ በወርቅ ዐመልማሎ የተሸለመች አንቺ በምሥራቅ ስትመሰዪ ልጅሽ የእውነት ፀሐይ ነው፡፡ በእውነት ቃል ኪዳንሽ አያልቅም)፡፡
✍️ “አዕረግዋ መላእክት እምድር ውስተ ሰማያት በክብር ወበስብሐት
በእንቲኣነ ከመ ትስአል እምወልዳ ኪዳነ ምሕረት”
(ስለ እኛ ከልጇ የምሕረት ኪዳንን ትለምን ዘንድ በክብር በምስጋና መላእክት ከምድር ወደ ሰማያት አሳረጓት፡፡)
✍️ “ይቤላ ለእሙ ማርያም እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ተካየድኩ ምስሌኪ ኪዳነ ምሕረት ከመ አድኅን ዘተአመነኪ መሐልኩ ለኪ በርእስየ ዘመሐልኩ አነ ለኖኅ ገብርየ ወለአብርሃም ፍቁርየ፤ ዘመሐልኩ አነ ለዳዊት ኅሩይየ ብእሲ ምእመን ዘከመ ልብየ መሐልኩ ለኪ በርእስየ በቅዱስ ሥጋየ ወበክቡር ደምየ መሐልኩ ለኪ በርእስየ ከመ ኢይሔሱ ማእኰትየ”
(ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እናቱ ማርያምን እንዲኽ አላት በምልጃሽ ያመነብሽን አድን ዘንድ ካንቺ ጋራ የምሕረት ቃል ኪዳንን ተጋባኊ፤ ለአገልጋዬ ለኖኅና ለወዳጄ ለአብርሃም ቃል የገባኊ እኔ በራሴ ማልኹልሽ፤ እንደ ልቤ ለምለው ለታመነው ለዳዊት የማልኊ እኔ በራሴ ማልኹልሽ፤ በቅዱስ ሥጋዬና በክቡር ደሜ የማልኊ እኔ ምዬ እንደማልከዳ ማልኹልሽ)
💥💥💥
💥 አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ💥
✍️ድካመ ጌጋይየ ትማእ ማርያም ጽድቀ ዚኣኪ በጽንዓ
መዳልወ ጥበብ ሶበ መልኣ ሰማኒተ ነፍሳተ ወሰብዓ
ሕፍነ ማይ ኀየለ ወሞአ”
(ማርያም የአንቺ ጽድቅ የበደሌን ድካም ድል ትነሣ ዘንድ የጥበብ (የምስጢር) ሚዛኖች በመሉ ጊዜ እፍኝ ውሃ ሰባ ስምንት ነፍሳትን ፈጽሞ ድል ነሣ፡፡)
✍️ “በከመ ልማድኪ በሊ ኀበ ወልድኪ ከሃሊ
ኦ ርኅሩኅ ኢተበቃሊ
ያጠፍኦኑ ለሥዕሉ ሠዓሊ
ኪነተከ ዘትካት ኀሊ”
(እንደ ልማድሽ ኹሉን የሚችል ወደሚኾን ልጅሽ የማትበቀል ቸር ሆይ፤ ሠዓሊ ሥዕሉን ያጠፋዋልን? የቀድሞ ፍጥረትኽን ዐስብ በዪ)።
✍️ “ጊዜ ጸልዮትኪ በጽሐ ከመ ኢይሙት ገብርኪ
ቅድሜሁ ስግዲ ወአስተብርኪ
እንዘ ታዘክሪዮ እምጻማ ንግደትኪ
ርግብየ የዋሂት ለየዋህ ወልድኪ”
(ደገኛዪቱ ርግቤ ለደገኛው ልጅሽ የእንግድነትሽን ድካም እንደ እናት እያሳሰብሺው፤ በፊቱ ፍጹም ስገጂ፤ አገልጋዪሽ እንዳይሞት የጸሎትሽ ጊዜ ደረሰ)።
✍️ “እሙ በሊዮ በእንቲኣየ ለፍሬ ከርሥኪ እብኖዲ
ላዕሌሁ ምሕረተ ኢታጐንዲ
እመ አሕዘነከ ብእሲ አባዲ
ቤዛ ነፍሱ ንጽሕየ እፈዲ”
(የጌታዬ እናት የማሕፀንሽ ፍሬ እብኖዲን ስለ እኔ እንዲኽ በዪው በርሱ ላይ ይቅርታን አታዘግዪ፤ ሰነፍ ሰው ቢያሳዝንኽም የነፍሱን ምትክ ንጽሕናዬን ዋጋ አድርጌ እከፍልለታለኊ)።
✍️ “አንቲ ውእቱ ለእግዚአብሔር አትሮኑሱ
ለአዳም ክብረ ሞገሱ
በኪዳንኪ ኃጥኣን መንግሥተ ሰማያት ይወርሱ"
(የእግዚአብሔር አትሮንሱ (ዙፋኑ) የአዳም የግርማው ክብር አንቺ ነሽ፤ ኃጥኣንም በቃል ኪዳንሽ መንግሥተ ሰማያትን ይወርሳሉ)።
💥💥💥
💥 አባ ጽጌ ድንግል 💥
✍️ “ሚ ሠናይ ከመ ጼና ጽጌ ልሑይ
በኲሉ ጊዜ ምሒረ ነዳይ
በእንተ ኪዳንኪ ድንግል ለበላዔ ሰብእ ጊጉይ
ሶበ ዐብየ እምኀጢአቱ ክበደ መድሎቱ ለማይ
ለተአምርኪ በሰማይ ተገብረ ግናይ”
(ኹል ጊዜ ለደኻ መራራት መመጽወት እንደ ለመለመ አበባ ያማረ ነው (ምን ያምር?) ድንግል በቃል ኪዳንሽ ምክንያት ከበላዔ ሰብእ ኀጢአት የውሃ ሚዛን በልጦ በመታየቱ ለተአምርሽ በሰማይ ምስጋና ኾነ)።
✍️ “በከመ ይቤ መጽሐፍ ማእከለ ፈጣሪ ወፍጡራን
ለዕረፍት ዘኮንኪ ትእምርተ ኪዳን
ሰንበተ ሰንበታት ማርያም ዕለተ ብርሃን
ብኪ ይትፌሥሑ ዘገነተ ጽጌ ጻድቃን
ወብኪ ይወጽኡ ኃጥኣን እምደይን”
(መጽሐፍ እንደተናገረ በፈጣሪና በፍጡራን መካከል ለዕረፍት የኪዳን ምልክት የሆንሽ የብርሃን ዕለት የሰንበታት ሰንበት ማርያም በአንቺ የገነት አበባ ጻድቃን ይደሰታሉ፡፡ ኃጥአንም በአንቺ ምልጃ ከሲኦል ይወጣሉ)፡፡
💥💥💥
💥የመልክአ ኪዳነ ምሕረት ደራሲ አባ ዘመለኮት💥
✍️ “ሰላም ለዝክረ ስምኪ ዘአስተማሰልዎ በኮከብ
ሶበ ብርሃኖ ተከድኑ ጽልሙታነ ራእይ ሕዝብ
ኪዳነ አምላክ ማርያም ወተስፋ መድኀኒት ዘዐርብ
ተናዘዘ ብኪ አኮኑ ኅሊና ቀዳማይ አብ
አመ እምገነቱ ተሰደ በሐዘን ዕጹብ”
(ለጨለመባቸው ወገኖች ብርሃኑን ባሳየ ጊዜ በኮከብ የመሰሉት ለኾነ ለስም አጠራርሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ የዐርብ የመድኀኒት ተስፋ የአምላክ ኪዳን ማርያም ሆይ በሚያስጨንቅ ሐዘን ከገነቱ በተሰደደ ጊዜ የመዠመሪያው ሰው ኅሊና ባንቺ ተረጋጋብሽ እኮን)።
✍️ “ሰላም ለአእዛንኪ እለ ተበሥራ ኪዳነ
እምአፈ ፈጣሪ ወልድኪ ዘባሕርየኪ ተከድነ
አምሕለኪ ማርያም ከመ ኢታርእዪኒ ደይነ
እንበለ ምግባር ባሕቱ እመ ኢይጸድቅ አነ
ቦኑ ለከንቱ ኪዳንኪ ኮነ”
(ባሕርይሽን ከተዋሐደ ከፈጣሪ ልጅሽ አንደበት የኪዳን ምሥራችን ለተበሠሩ ጆሮዎችሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ ያለምግባር የማልጸድቅማ ከኾነ በውኑ ኪዳንሽ ለከንቱ ይኾናልና ማርያም ሆይ ፍርድን እንዳታሳዪኝ አምልሻለኊ)።
✍️ “ማርያም ኅሪት እምነ መላእክት ወሰብእ
ተዝካረኪ ለእመ ገብረ በተአምኖ ጽኑዕ
በመንግሥተ ሰማይ ምስሌኪ ይነግሥ ኃጥእ”
(ከመላእክትና ከሰዎች ይልቅ የተመረጠሸ ማርያም ሆይ መታሰቢያሽን በብርቱ መታመን ያደረገ በመንግሥተ ሰማይ ካንቺ ጋር ይነግሣል) በማለት አወድሰዋታል፡፡
💥 እኛም በረከቷ ይደርብን ጸሎቷ ይጠብቀን፡፡ በአስተያየት መስጫው ላይ የአምላክ እናት በተሰጣት ቃል ኪዳን ትጠብቃችሁ ዘንድ በምትወዱት መዝሙር ግጥም ወይም በምትወዱት የምስጋና ጸሎት አመስግኗት።
✍️ መጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ (በድጋሚ የተለጠፈ)
+++ ጸልየህ ልታደርገው ትችላለህ? +++
ማልዶ ቤተ ክርስቲያን ተሳልሞ ወደ ሥራ የሚሄድ አንድ መንፈሳዊ ሰው በጉዞው ከሌላ መንገደኛ ሰው ጋር ይገናኛል። ጥቂት እንደ ተጨዋወቱ ይህ በመንገድ ያገኘው ሰው ከደረት ኪሱ የሲጋራ ፓኮ በማውጣት አንዱን መዝዞ እንዲወስድ ይጋብዘዋል። ያም መንፈሳዊ ሰው "አይ ይቅርብኝ" ሲል እምቢታውን ገለጸ። ባለ ሲጋራውም "ኃጢአት ነው ብለህ ስላሰብህ ነው እምቢ ያልከኝ? ማጨስ እኮ ከአስጨናቂዋ ሕይወት ፋታ ለመውሰድና ራስን ዘና ለማድረግ ይረዳል። ግድ የለህም አንዱን ሞክር" እያለ ሊያግባባው ጣረ። በመጨረሻም መንፈሳዊው ሰው "ግድ የለም ለእኔ ይቅርብኝ። ባይሆን አንተ ይጠቅመኛል ካልህ በቃ ሲጋራውን ከመለኮስህ በፊት አንድ "አባታችን ሆይ" ጸልይና ጀምር" አለው። በዚህ ጊዜ ያ መንገደኛ ደንግጦ እንዲህ ሲል መለሰ "ጸሎት ጸልዬማ እንዴት እንዲህ አደርጋለሁ?!"
በጸሎት ልትጀምር የማትችላቸው ማናቸውም ነገሮች ለአንተ መልካም አይደሉም። በልብህ ኃጢአት እንድታደርግ የሚገፉፉህ ክፉ ሐሳብ ሲመጣ "ይህን ጸልዬ ማድረግ እችላለሁ?" ብለህ ራስህን ጠይቅ። ከጸሎት ጋር የማይጣጣም ከመሰለህ እርሱ ኃጢአት ነውና ተወው። ጸልዮ የሚዘሙት፣ ጸልዮ የሚሰርቅ፣ ጸልዮ ባልንጀራውን የሚሳደብ፣ ጸልዮ በወንድሙ ላይ ክፉ የሚያደርግ ማን ነው?
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
አዲስ አበባ
ማልዶ ቤተ ክርስቲያን ተሳልሞ ወደ ሥራ የሚሄድ አንድ መንፈሳዊ ሰው በጉዞው ከሌላ መንገደኛ ሰው ጋር ይገናኛል። ጥቂት እንደ ተጨዋወቱ ይህ በመንገድ ያገኘው ሰው ከደረት ኪሱ የሲጋራ ፓኮ በማውጣት አንዱን መዝዞ እንዲወስድ ይጋብዘዋል። ያም መንፈሳዊ ሰው "አይ ይቅርብኝ" ሲል እምቢታውን ገለጸ። ባለ ሲጋራውም "ኃጢአት ነው ብለህ ስላሰብህ ነው እምቢ ያልከኝ? ማጨስ እኮ ከአስጨናቂዋ ሕይወት ፋታ ለመውሰድና ራስን ዘና ለማድረግ ይረዳል። ግድ የለህም አንዱን ሞክር" እያለ ሊያግባባው ጣረ። በመጨረሻም መንፈሳዊው ሰው "ግድ የለም ለእኔ ይቅርብኝ። ባይሆን አንተ ይጠቅመኛል ካልህ በቃ ሲጋራውን ከመለኮስህ በፊት አንድ "አባታችን ሆይ" ጸልይና ጀምር" አለው። በዚህ ጊዜ ያ መንገደኛ ደንግጦ እንዲህ ሲል መለሰ "ጸሎት ጸልዬማ እንዴት እንዲህ አደርጋለሁ?!"
በጸሎት ልትጀምር የማትችላቸው ማናቸውም ነገሮች ለአንተ መልካም አይደሉም። በልብህ ኃጢአት እንድታደርግ የሚገፉፉህ ክፉ ሐሳብ ሲመጣ "ይህን ጸልዬ ማድረግ እችላለሁ?" ብለህ ራስህን ጠይቅ። ከጸሎት ጋር የማይጣጣም ከመሰለህ እርሱ ኃጢአት ነውና ተወው። ጸልዮ የሚዘሙት፣ ጸልዮ የሚሰርቅ፣ ጸልዮ ባልንጀራውን የሚሳደብ፣ ጸልዮ በወንድሙ ላይ ክፉ የሚያደርግ ማን ነው?
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
አዲስ አበባ
በንጽሕና ለመኖር እየታገለ የሚወድቅን እግዚአብሔር አያዝንበትም። ድካሙን እና ያልተቋረጠ ጥረቱን አይቶ ድል የሚነሣበትን መንፈሳዊ ጸጋ ይሰጠዋል እንጂ። እንድትኖር በታዘዝከው ልክ ለመኖር ሞክረህ ስላልሆነልህ በራስህ ተስፋ አትቁረጥ። መሆንህን ብቻ ሳይሆን ፈልገህ መሞከርህን እግዚአብሔር ይቆጥርልሃል። ሰይጣን አቁስሎህ ስለሻረው ጠባሳህ አትቆጭ። ብዙ ጠባሳ እኮ ለሚዋደቅ ጀግና ወታደር የክብር ምልክቱ ነው። አፈ ወርቅ ዮሐንስ እንደሚለው የማይቆስለው የማይዋጋ ብቻ ነው።
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
ድኃ ሙስሊምች በተለይ ወንድች ይሄንን ዜና ከሰማችሁ በኋላ እንደምትከፍሩ ርግጠኛ ነኝ ።😳💪
በፎቶዉ ላይ የምታዩት የሳኡዲ ተወላጅ አባወራ በአንድ ጊዜ 3 ሴቶችን አግብቷል። እስከ 4 ሚስት ማግባት በሚፈቀድባት ሳኡዲ ‘ታዲያ ይህ ምን ይገርማል?’ ልትሉኝ ትችላላችሁ። አስገራሚዉ ነገር ሶስቱም ሚስቶቹ በአንድ የትምህርት ተቋም ዉስጥ ያሉ መሆናቸዉ ነዉ! ከሶስቱ ሴቶች አንዷ የተቋሙ ተማሪ፣ ሌላኛዋ መምህርት፣ ሶስተኛዋ ደግሞ የተቋሙ ኃላፊ ናቸዉ። ይበልጥ የሚገርመዉ ደግሞ ግለሠቡ ቀደም ሲል ያገባት የመጀመሪያ ሚስቱም በተመሳሳይ የትምህርት ተቋም ዉስጥ በሱፐርቫይዘርነት በማገልገል ላይ መሆኗ ነዉ።
እኔ የምለዉ ግን … ይሔ ሠዉዬ ከትምህርት ተቋሙ ጋር ያለዉ ግንኙነት መጣራት ያለበት አይመስላችሁም? 😀
በፎቶዉ ላይ የምታዩት የሳኡዲ ተወላጅ አባወራ በአንድ ጊዜ 3 ሴቶችን አግብቷል። እስከ 4 ሚስት ማግባት በሚፈቀድባት ሳኡዲ ‘ታዲያ ይህ ምን ይገርማል?’ ልትሉኝ ትችላላችሁ። አስገራሚዉ ነገር ሶስቱም ሚስቶቹ በአንድ የትምህርት ተቋም ዉስጥ ያሉ መሆናቸዉ ነዉ! ከሶስቱ ሴቶች አንዷ የተቋሙ ተማሪ፣ ሌላኛዋ መምህርት፣ ሶስተኛዋ ደግሞ የተቋሙ ኃላፊ ናቸዉ። ይበልጥ የሚገርመዉ ደግሞ ግለሠቡ ቀደም ሲል ያገባት የመጀመሪያ ሚስቱም በተመሳሳይ የትምህርት ተቋም ዉስጥ በሱፐርቫይዘርነት በማገልገል ላይ መሆኗ ነዉ።
እኔ የምለዉ ግን … ይሔ ሠዉዬ ከትምህርት ተቋሙ ጋር ያለዉ ግንኙነት መጣራት ያለበት አይመስላችሁም? 😀
Forwarded from J.CHRISTIAN
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
They might have horses and chariots but we will be great by the name of God YHWH
Forwarded from ልባም ሴት 😍
በእንግሊዝ ሆፕ ከተማ የሚገኝ የፕሮቴስታንት ቤተ ክርስቲያን መሪዎችን ጨምሮ ሙሉ ጉባኤያቸው ወደ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ተጨመሪ
ይህ መልካም ዜና የኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን እምነት ትክክለኛነትና ሐዋርያዊነትን በማሳየት ትልቅ ቦታ የሚሰጠው ነው።
ስለዚህ የምስራች የተነሱ ሀሳቦች :-
🎯የመቀየሪያው ምክንያት : የፕሮቴስታንት ቤተ ክርስቲያን መሪዎች እና ጉባኤያቸው የኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ትምህርቶችን፣ ታሪክን እና ሥርዓቶችን በጥልቀት ካጠኑ በኋላ እውነተኛውን የክርስትና እምነት እንዳገኙ በመግለጽ ወደ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ለመቀላቀል ወስነዋል።
🎯የመቀበያ ሥርዓት : ጉባኤው ወደ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የተጨመረው በጸሎት፣ በቅዱስ ቁርባን እና በሌሎችም የቤተ ክርስቲያን ሥርዓቶች አማካኝነት ነው።
🎯የቤተ ክርስቲያኒቱ ስያሜ: ወደ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የተጨመረው ቤተ ክርስቲያን "የቅዱስ ጆን ክሊማከስ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን" ተብሎ እንደተሰየመ ተገልጿል።
🎯የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምላሽ**: የኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የዚህን ጉባኤ ወደ እቅፏ መቀላቀል በደስታ ተቀብላለች።
ይህ መልካም ዜና በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እና በሌሎች የክርስትና እምነቶች መካከል ያለውን ግንኙነት በተመለከተ ብዙ ውይይቶችን አስነስቷል። እንዲሁም የኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን እምነትን እና ታሪክን ለማወቅ ለሚፈልጉ ሰዎች ትኩረት የሚስብ ሆኗል።
ይህ መልካም ዜና የኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን እምነት ትክክለኛነትና ሐዋርያዊነትን በማሳየት ትልቅ ቦታ የሚሰጠው ነው።
ስለዚህ የምስራች የተነሱ ሀሳቦች :-
🎯የመቀየሪያው ምክንያት : የፕሮቴስታንት ቤተ ክርስቲያን መሪዎች እና ጉባኤያቸው የኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ትምህርቶችን፣ ታሪክን እና ሥርዓቶችን በጥልቀት ካጠኑ በኋላ እውነተኛውን የክርስትና እምነት እንዳገኙ በመግለጽ ወደ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ለመቀላቀል ወስነዋል።
🎯የመቀበያ ሥርዓት : ጉባኤው ወደ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የተጨመረው በጸሎት፣ በቅዱስ ቁርባን እና በሌሎችም የቤተ ክርስቲያን ሥርዓቶች አማካኝነት ነው።
🎯የቤተ ክርስቲያኒቱ ስያሜ: ወደ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የተጨመረው ቤተ ክርስቲያን "የቅዱስ ጆን ክሊማከስ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን" ተብሎ እንደተሰየመ ተገልጿል።
🎯የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምላሽ**: የኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የዚህን ጉባኤ ወደ እቅፏ መቀላቀል በደስታ ተቀብላለች።
ይህ መልካም ዜና በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እና በሌሎች የክርስትና እምነቶች መካከል ያለውን ግንኙነት በተመለከተ ብዙ ውይይቶችን አስነስቷል። እንዲሁም የኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን እምነትን እና ታሪክን ለማወቅ ለሚፈልጉ ሰዎች ትኩረት የሚስብ ሆኗል።
"መምሬ ካሳሁን እንግዳ በአድዋ ጦርነት ጊዜ የቅዱስ ጊዮርጊስን ታቦት ይዘው በባዶ እግራቸው የዘመቱ አባታችን"
አድዋ የካቲት ፳፫ ቀን ፲፰፻፹፰ ዓ.ም በአድዋ ተራራ ላይ ጥቁር ሕዝቦች ለመጀመሪያ ጊዜ የማይቻል የሚመስለውን የቻሉበት፣ አይሆንም የተባለው የሆነበት፣ “ነጮች” “በጥቁሮች” የተሸነፉበት፣ ታላቅ ሁነት የተፈጸመበት፣ የድል በዓል መታሰቢያ ነው።
የአድዋን ድል ልዩ ያደረገው አንድ ሕዝብ በጦር ሜዳ ተዋግቶ ያሸነፈበት ታሪክ ስለ ሆነ ብቻ ሳይሆን በዘመኑ ዓለምን የተቆጣጠረውን “ጥቁር ሕዝብ ተፈጥሮውም፣ ኑሮውም ነጭን ለማሸነፍ አያስችለውም” የሚልና እንኳን ገዥዎችን ተገዥዎችንም ጭምር አሳምኖ የነበረ አስተሳሰብን የሻረ በመሆኑ ነው፡፡ ሁለት ለንጽጽር የማይገቡና ያልተመጣጠነ አሰላለፍ የነበራቸው ሕዝቦችና መንግሥታት ተዋግተው እንደ ጎልያድ በሰይፍ የመጣው ሳይሆን እንደ ዳዊት በእምነት ጠጠር የወነጨፈው ያሸነፈበት የማይታመን እውነታ በመሆኑም ነው፡፡
አድዋ የካቲት ፳፫ ቀን ፲፰፻፹፰ ዓ.ም በአድዋ ተራራ ላይ ጥቁር ሕዝቦች ለመጀመሪያ ጊዜ የማይቻል የሚመስለውን የቻሉበት፣ አይሆንም የተባለው የሆነበት፣ “ነጮች” “በጥቁሮች” የተሸነፉበት፣ ታላቅ ሁነት የተፈጸመበት፣ የድል በዓል መታሰቢያ ነው።
የአድዋን ድል ልዩ ያደረገው አንድ ሕዝብ በጦር ሜዳ ተዋግቶ ያሸነፈበት ታሪክ ስለ ሆነ ብቻ ሳይሆን በዘመኑ ዓለምን የተቆጣጠረውን “ጥቁር ሕዝብ ተፈጥሮውም፣ ኑሮውም ነጭን ለማሸነፍ አያስችለውም” የሚልና እንኳን ገዥዎችን ተገዥዎችንም ጭምር አሳምኖ የነበረ አስተሳሰብን የሻረ በመሆኑ ነው፡፡ ሁለት ለንጽጽር የማይገቡና ያልተመጣጠነ አሰላለፍ የነበራቸው ሕዝቦችና መንግሥታት ተዋግተው እንደ ጎልያድ በሰይፍ የመጣው ሳይሆን እንደ ዳዊት በእምነት ጠጠር የወነጨፈው ያሸነፈበት የማይታመን እውነታ በመሆኑም ነው፡፡