Telegram Web Link
┈ድንቅ ታሪክ ናት┈┉┅━

{በሙሳ ዐ.ሰ} በዘመን ነው ....
አንድ በጣም ድህነት ያጎሳቆላቸው ለዘመናት በችግር እና በረሀብ የኖሩ ባልና ሚስት ነበሩ።
ይሁን እንጂ ይህን ሁሉ ዘመናት በሰብር አሳልፈዋል.።

እናም አንድ ቀን እቤታቸው ጋደም ብለው ሳለ
#ሚስት #ለባለቤትዋ፦"ሙሳ አላህን ማናገር የሚችል ነቢይ ነው አይደል?" ብላ ትጠይቀዋለች።

#እሱም፦"አዎን" ይላታል።
"ታዲያ ለምን እሱጋ ሄደን ስለ ሁኔታችን አንነግረውም አላህንም ስለኛ ያናግረው ሀብታም እንዲያረገን ቀሪ ህይወታችንን በድሎት እንድንኖርም ይጠይቅልን።" አለችው።

🍃🍃ባልም በሚስቱ ሀሳብ ይስማማና ሌሊቱ እንደነጋ ጉዞ ወደ {ሙሳ ዐ.ሰ} ቤት ጀመሩ።
{ሙሳንም ዐ.ሰ} አገኟቸው። ስለድህነታቸው ነግረዋቸውም በዚህ ጉዳይ እሳቸው አላህን እንዲለምኑላቸው ጠየቋቸው።
{ሙሳም ዐ.ሰ} አላህን ለመኑላቸው።


#አላህም፦"ሙሳ ሆይ! እኔ እነዚህን ሰዎች በችሮታዬ ለአንድ አመት ያህል ሀብታም አደርጋቸዋለሁ ! አንድ አመት ካለፈም ወደነበሩበት ድህነት እመልሳቸዋለሁ። #ብሎ_መለሰላቸው

እሳቸውም ጥንዶቹ ጋ በመሄድ  #አላህ ዱዓቸውን #ሙስተጃብ እንዳደረገላቸው። ሀብታምም እንደሚሆኑ ነግረዋቸው እናም ግን ለ አንድ አመት ቢቻ እንደሚቆይ አክለው ነገሯቸው። እነዚህ ምስኪኖችም የሰሙትን ማመን ተሳናቸው።

በአጭር ግዜ ውስጥ ካለሰቡበት መንገድ ሀብታም መሆን ጀመሩ ማንም ከሚኖረው የተሻለ ኖሮ መኖርም ጀመሩ። እናም አንድ ቀን ይህች ብልህ #ሚስት #ለባሏ እንዲህ አለችው፦

"ይህ ፀጋ ይህ ድሎት ለአንድ አመት ብቻ እንደሚዘገይ ታውቃለህ አይደል? ስለዚህ በዚህ ንብረታችን #አንድ_መልካም_ስራ_እንስራ
#ባልይውም በሀሳቧ ይስማማል።

ከዚያም በከተማዋ ግንባር ቦታ ላይ አደባባይ መልክ አንድ ትልቅ ቤት ይገነቡና 7 በር አበጁለት። ለሰውም መተላለፊያ ሰሩ። ቤቱ ተገንብቶ ካለቀ በኋላ እዛ ቤት ውስጥ ምግብ እያዘጋጁ ለአላፊ አግዳሚ #ጠዋት #ማታ ምግብ ይቀልቡ ጀመር...በዚህ ሁኔታ ሳሉ ወራት አስቆጠሩ።

#ሙሳም በትኩረት ይከታተሏቸው ነበር። ማይደርስ ቀን የለምና ያ የተወሰነላቸው ቀን ቀጠሮውን ጠብቆ ከች አለ። እነሱ ግን የቀጠሮ ቀኑ ሁላ ትዝ አላላቸውም በስራቸው ተጠምደዋል። ያ ቀጠሮ ቀናቸው አለፈ እነሱ ግን ያው ናቸው ምንም አልቀነሱም ብቻ በስራቸው ተጠምደዋል....

{ሙሳንም ዐ.ሰ} ባዩት ሁኔታ ተገርመው፦
#ያ_ረብ_ቃል_የገበኽላቸው_ለአንድ_አመት_ሆኖ_ሳለ_እንዴት_እስካሁን_እልደኸዩም?"ብለው አላህን ጠየቁ። እዚጋ እሳቸው ሰዎቹን ተመቃኝተው ሳይሆን #የአላህን_ሂክማ_ለማወቅ_ነው


የጠየቁት/ ቸር የሆነው #አላህም፦ ሙሳ ሆይ ለነዚህ ጥንዶች ከፀጋ በሮቼ አንዲትን በር ስከፍትላቸው... እነሱ ደሞ 7 በር ከፍተው ባሪያዎቼን መቀለብ ጀመሩ።  ሙሳ ሆይ እነሱ ይሄን ሲያረጉ አይቼ የከፈትኩላቸውን በር መዝጋት ከበደኝ"አለው።

━┅┉┈ሱብሀን አላህ┈┉┅━

SHARE 🔗SHARE
http://www.tg-me.com//@arebgendamesjid
አረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ ዘርፍ
42ኛ  ሓዲስ

መሃርታን መጠየቅ እና ተውሒድ

🚩:አነስ ኢብን ማሊክ የአላህ መልእክተኛ صلى الله عليه وسلم እንዲህ ሲሉ ሰምቻቸዋለሁ አለ፦ አላህ እንዲህ አለ “አንተ የአደም ልጅ ሆይ!አንተኮ በጠራሃኝ እና መሃርታን በጠየቅከኝ ግዜ ካንተ ምንም ቢኖርም እምርሃለሁ ወንጀልህ ቢበዛም ምንም አይመስለኚም። አንተ የአደም ልጅ ሆይ!ወንጀልህ ሰማይ ቢደርስኳ መሃርታን ከጠየቅከኝ እምርሃለሁ። አንተ የአደም ልጅ ሆይ!አንተኮ ምድርን የሞላ ወንጀል ይዘህ በእኔ ግን ሳታጋራ ወደኔ ብትመጣ ከዚያም ብትገናኘኝ እኔም እሷን በሞላ መሃርታ ወዳንተ እመጣ ነበር።”

📚ሓዲሱን ቲርሚዚይ ዘግቦታል📚

📍ከአርባ ሁለተኛው ሓዲስ የምንወስዳቸው ትምህርቶች📍

1⃣.የሰው ልጅ ኣላህን በለመነ እና ከኣላህ በከጀለ ቁጥር ኣላህ እንደሚምረው።
2⃣.የኣላህ እዝነትን እንረዳለን። 
3⃣.የሰው ልጅ ወንጀል ቢበዛም፣ ከኣላህ መሃርታን ከጠየቀ ኣላህ እንደሚምረው።  
4⃣ተውሒድ (ኣምልኮን ለኣላህ ብቻ ማድረግ እና ኣምልኮን ለኣላህ ብቻ ብሎ መስራት)በጣም ትልቅ ደረጃ እንዳለውና ወንጀላችንን እንድንማር እንደሚያደርግ።
 
📘:አርበዑነ ነወውያ(42 ሀዲሶች))
       ከ27ኛው -42 ኛው ሀዲስ ተጠናቀቁ

👉 http://www.tg-me.com//@arebgendamesjid
📮📮#የኢብሊስ_አሟሟት📮📮

ዱንያ ልትጠናቀቅ ጥቂት ሲቀራት እና ጡሩንባው
ከመነፋቱ በፊት የሰው ልጆች በየመገበያያዎቻቸው ላይ
በመገበያየት ላይ ሳሉ ድንገት ከፍተኛ ድምፅ ይፈጠርና
ከምድር ሰዎች ግማሹ በድንህጋጤ ሲሞት የተቀሩት
ደግሞ ልክ አውሬ እንዳየ እንስሳት ይደናበራሉ።
በዚህ ሁኔታ ላይ ሳሉም ብዙ ሳይቆዩ ከወደ ሰማይ በኩል
ከፍተኛ የሆነ እና የመብረቅ ነጎድጓድ መሳይ ድምፅ
መጥቶ የተቀረውን ፍጥረት ከሙታን ተርታ ያሰልፋል።
ያን ግዜ ምድር ከህያዋን ፍጥረታት ባዶ ትሆናለች።
ጂኖች፣ ሰዎች እና ሰይጣናት በሙሉ ሙተው ምድር ላይ
ኢብሊስ ብቻውን ይቀራል።ይህች ቅፅበት በአላህ እና
ለኢብሊስ መካከል የነበረችዋ ቃል ኪዳን ምትፈፀምባት
ናት።
አላህም ለመለከል መውት እንዲህ ይለዋል፦"እኔ
በመጀመሪያዎቹም በመጨረሻዎቹም ፍጥረታቴ ቁጥር
ያህል ረዳቶችን መድቤልሃለሁ። የሰማይን እና የምድር
ነዋሪያንን ጉልበት ሁሉ ሚያክል ላንተ ሰጥቼሀለሁ።
ዛሬ የቁጣን እና የበቀልን ልብስ አልብሼሀለሁ። በበቀል
እና በቁጣ ተሞልተህ ወደ ረገምኩት ኢብሊስ ውረድ።
ሞትንም አቅምሰው። ከሞት ምሬትም ፍጥረታት፣ ጂኖች
እና ሰዎች ሁሉ የቀመሱትን እጥፍ ድርብ አድርገህ
አቅምሰው።
ዘባኒያዎችም የጀሀነምን ሰንሰለት ይዘው ይጠብቁሀል።
ከጀሀነም በሆኑ 70,000 አውሬዎችም ተጠቅመህ ግም
የሆነች ነፍሱን ገሽልጣት።ከዝያም ማሊክ/የጅሀነም
ጠባቂን በሯን እንዲከፍት ጥራው" ይላል።
ከዝያም መለከል መውት ለአላህ ትዕዛዝ በመተናነስ ወደ
ምድር ፍፁም አስፈሪ በሆነ ገፅታው ይወርዳል። በዚያ
ገፅታው ሰው፣ጂን እና መላዕክት ቢመለከቱት ትዕይንቱን
መቋቋም አቅቷቸው ይቀልጡ ነበር።
መለከል መውት ምድር ወርዶ ልክ ኢብሊስን
እንደተመለከተው በከፍተኛ ድምፅ ይጮህበት'ና ኢብሊስ
ራሱን ሲስት አንድ ግዜ ይጠልዘዋል።
ይህን ግዜ መለከል መውትም እየተከተለው፦"ቁም አንተ
እርጉም ዛሬ ባጠፋኸው ነፍስ ቁጥር ሁሉ አንተንም ሞትን
አቀምስሃለሁ። ስንት እድሜ ጨርሰሃል!!! ምን ያህል ክፍለ
ዘመናትንስ ነው ፍጥረትን በማጥመም የከረምከው!!!!?
በጀሀነም ሚቆራኙህ ስንት ቁራኛዎች እንዳሉህ ብታይ!
ዛሬማ ባንተ እና በአላህ መካከል የነበረችው ቃል ኪዳን
ምትፈፀምበት ቀን ናት። ዛሬ ወዴት ትሸሻለህ!!!?"
ይለዋል።
ከዝያም ኢብሊስ ወደ ምስራቅ ጫፍ ይሸሻል። ይሁን
እንጂ ፊቱ ላይ መለከል መውትን ያገኘዋል። ባህር ውስጥ
ይሰምጣል። አሁንም ከፊቱ መለከል መውትን ያገኛል፤
ባህርም ይተፋዋል።
ምንም ሳይታክት በተቻለው መጠን ለመሸሽ ምድርን
ይዞራል። ይሁን እንጂ ምንም ማምለጫም ሆነ መሸሸግያ
አይኖርም።ከዝያም ምድር ወገብ ላይ የአደም ቀብር
በሚገኝበት ስፍራ ይቆም'ና፦"አንተ አደም!!! ባንተ ሰበብ
ነው እርጉም ሆኜ የቀራሁት። ምን ነበር ባልተፈጠርክ!'
ይላል።
ከዝያም ኢብሊስ ለመለከል መውት፦"በምን አይነት ፅዋ
ነው ሞትን ምታቀምሰኝ?! ይለዋል።
መለከል መውትም፦"በ ለዟ፣ በሰቀር እና በእሳት ሰዎች
ፅዋ ነው አባዝቼ እማቀምስህ" ይለዋል።
ይህን የተመለከተው ኢብሊስም ጥቂት መሬት ላይ በፀፀት
ይንከባለልና ወደ ምስራቅ እና ወደ ምዕራብ ሲመላለስ
ዘባኒያ የተባሉት የጀሀነም ወታደሮች ድሮ ኢብሊ ከሰማይ
የወረደባት ቦታ ላይ ከጀሀነም አውሬዎች ጋር ሁነው
ይይዙታል።
በአውሬዎቹ እየተዘረገፈ እና እየተሰቃየ ላልተወሰነ ግዜ
በጣዕረ ሞት ላይ ይቆያል። ከዝያም ሀዋ እና አደም
ትዕይንቱን እንዲያዩ ይደረጉ'ና፦"ጠላታችሁን ተመልከቱ።
የሞትን ፅዋም እንዴት እንደሚቀምስ እዩ" ይባላሉ።
ሀዋ እና አደምም፦"ጌታችን ሆይ!!! ፀጋህን እኛ ላይ
ሞልተህልናል" ይላሉ።

📚📚📚🎀🎀🎀🌹🌹🌿🌿🥀🥀
ቻናላችን ⤵️
#join
ያድርጉና ይቀላቀሉ👇👇👇
http://www.tg-me.com//@arebgendamesjid
✹••••━━✿✿━━••••

የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ ዘርፍ
♻️🔺አሏህ ሱብሀናሁተአላ ሱረቱል ቀሶስ ላይ ለወንድም ለሴትም  አንድ ከባድ የሆነ  መልካም የሆነ  የስው ልጆች ሊላበሱት የሚገባ መልካም ስነምግባረ  ይጠቅሳል  ‼️
🔺ይህም ስነምግባረ ሀያእ  አይናፋረነትን መላበስ አስመልክቶ ተናግሯል።


وَلَمَّا وَرَدَ مَآءَ مَدْيَنَ وَجَدَ عَلَيْهِ أُمَّةًۭ مِّنَ ٱلنَّاسِ يَسْقُونَ وَوَجَدَ مِن دُونِهِمُ ٱمْرَأَتَيْنِ تَذُودَانِ ۖ قَالَ مَا خَطْبُكُمَا ۖ قَالَتَا لَا نَسْقِى حَتَّىٰ يُصْدِرَ ٱلرِّعَآءُ ۖ وَأَبُونَا شَيْخٌۭ كَبِيرٌۭ
ወደ መድየንም ውሃ በመጣ ጊዜ በእርሱ ላይ ከሰዎች ጭፍሮችን (መንጋዎቻቸውን) የሚያጠጡ ሆነው አገኘ፡፡ ከእነርሱ በታችም (ከውሃው መንጎቻቸውን) የሚከለክሉን ሁለት ሴቶች አገኘ፡፡ «ነገራችሁ ምንድን ነው» አላቸው፡፡ «እረኞቹ ሁሉ (መንጋዎቻቸውን) እስከሚመልሱ አናጠጣም፡፡ አባታችንም ትልቅ ሽማግሌ ነው» አሉት፡፡

فَسَقَىٰ لَهُمَا ثُمَّ تَوَلَّىٰٓ إِلَى ٱلظِّلِّ فَقَالَ رَبِّ إِنِّى لِمَآ أَنزَلْتَ إِلَىَّ مِنْ خَيْرٍۢ فَقِيرٌۭ
ለሁለቱም አጠጣላቸው፡፡ ከዚያም ወደ ጥላው ዘወር አለ፡፡ «ጌታዬ ሆይ! እኔ ከመልካም ነገር ወደኔ ለምታወርደው ፈላጊ ነኝ» አለ፡፡


فَجَآءَتْهُ إِحْدَىٰهُمَا تَمْشِى عَلَى ٱسْتِحْيَآءٍۢ قَالَتْ إِنَّ أَبِى يَدْعُوكَ لِيَجْزِيَكَ أَجْرَ مَا سَقَيْتَ لَنَا ۚ فَلَمَّا جَآءَهُۥ وَقَصَّ عَلَيْهِ ٱلْقَصَصَ قَالَ لَا تَخَفْ ۖ نَجَوْتَ مِنَ ٱلْقَوْمِ ٱلظَّٰلِمِينَ
ከሁለቱ አንደኛይቱም ከሐፍረት ጋር የምትኼድ ሆና መጣችው፡፡ «አባቴ ለእኛ ያጠጣህልንን ዋጋ ሊመልስልህ  ይጠራሃል» አለችው፡፡ ወደእርሱ በመጣና ወሬውን በእርሱ ላይ በተረከለትም ጊዜ «አትፍራ ከበደለኞቹ ሕዝቦች ድነሃል» አለው፡፡

በንግግሯም በተግባሯም ይች ሴት ሀያእ እንደተላበስች አሏህ ሱብሀናሁተአላ  ይናገራል ።

ስትመጣም በሀያእ ነው የመጣችው ስትናገረም ሀያእ በተሞላበትነው የተናገረችው ።ከቁረአኑ ባጭሩ ይሄንን እንረዳለን።

አሏሁሱብሀናሁተአላ ለኛ ይች ሴት ሞደል እንድትሆንና የሷን ተግባረ የሷን መልካምነት እንስንከተል ይህ ቁረአን ላይ አስፈረው።በንግግሯም በተግባሯም ሀያእን መላበስ እንዳለበት አንድት ሴት ልጅ. ከዚህ ከቁረአን አያ እንረዳለን ።

ስለዚህ አንድት ሴትልጅ ሀያእ አላት  ‼️  ሀያእዋ ሙሉነው ሊባል የሚችለው  እነዚህን ሁለት ነገሮች አንድ ላይ ስታራግ ነው ‼️👉በንግግሯም
👉 በተግባሯም ሀያእ ሲሞላነው።‼️ ሀያእ አላት እሚባለው ሀያእ ሲኖራት ነው።

👉ከሁለቱ  አንዱ ከጎደለ ሀያእዋ ሀያእ አይባልም።

አንዳንድ ጊዜ ንግግሯ ሀያእ ሊያስወግድ ይችላል አንድን ሴት ልጅ በንግግራ ማወቅ ይቻላል ሀያእ የሌላት መሆኑን ‼️
አንዳንድ  ጊዜ. በንግግሯ ሀያእ  ሊኖራት ይችላል ። በተግባሯ ሀያእ ላይኖራት ይችላል።
ስለዚህ  ተግባሯ ሀያእን ሊያስወግድባት ይችላል ‼️
አንዳንደዜ በተግባሯ ሀያእ አላት በንግግሯ ግን ምንም ሀያእ  የላትም ስለዚህ ንግግሯ ሀያእን ሊያስወግድባት ይችላል።

ስለዚህ አንድ ሴት ልጅ ሀያእዋ ሙሉነው እሚባለው እነዚህን ሁለት ነገሮች ስታቆራኝ ነው።
👉በንግግሯም
👉በተግባሯም ልክ ከላይ እንደተጠቀስችው አይነት ሴትማለት ነው።

👌🏻ሀያእ የሚባለው ነገረ  የሴት ልጅ ጌጧ ውበቷ ነው። ሴትልጅ ምንም አታጌጥም ከሀያእ በላይ‼️
👌🏻ከትልቅ ነገረ አላት አይባልም ከሀያእ  በላይ ውበት የላትም ።
ሴትልጅ ሀያእዋ ከውስጧ ከተወገደ ውበቷ ይጠፋል።

የሴት ልጅ ትክክለኛ ቁንጅናዋ ውበቷ ሀያእዋ አይናፋረነቷ ነው።

ትክክለኛ ውበትን የፈለገ ስው ሀያእ ያላትን ሴት ሊመረጥ ይገባዋል   ሊያይ ይገባዋል።
ምክንያቱም የፈለገ ውበቷ ቢያምረ ሀያእ ከሌላት ውበቷ ይወገዳል።

ከወንድማችን አቡ አብዲላህ ኢብኑ ኽይሩ "ሀያእ  የውበት መገለጫ ነው ከሚለው ድምጽ ፋይል  የተወሰደ።
🔺ሴት_ልጅ ማንኛውም ሰው ሊያነሳት
የሚመኝ ቆንጆ አበባ ነች።
ውዷ እህቴ ይህን ስልሽ የሴት ልጅ ውበቷ 
👉በገፅታዋ ፣ 
👉በቆዳዋ ቀለም
👉ወይምባላት ማቴርያሎች ሳይሆን 
......ትክክለኛ እና እውነተኛ ውበቷ .......
👉በልቧ 
👉በሀያዕዋ 
👉በኢማኗ 
👉በተቅዋዋ እና ለዲነል ኢስላም
ባልት ፍቅር መሆኑን እወቂ
http://www.tg-me.com//@arebgendamesjid
𝑱𝑶𝑰𝑵 𝑨𝑵𝑫 𝑺𝑯𝑨𝑹𝑬⤴️⤴️⬆️⬆️

📌የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ ዘርፍ📌
🔰ኢማንን የሚጨምሩ ነገሮች🔰

ኢማንን የሚጨምሩ ነገሮች በርካታ ሲሆኑ ከነዚህ መካከል የሚከተሉት ይገኛሉ፡-
ጠቃሚ የሆነ እውቀት መማር፤ የተከበረውን ቁርኣን በማስተንተን መቅራት፤ የአላህን መልካም ስሞችና ከፍተኛ የሆነውን መገለጫ ማወቅ፤ የኢስላምን ሓይማኖት ውበትና መልካምነት መገንዘብ፤ የነብያችን ﷺ እና የተከበሩትን ሶሃቦች ታሪክ
መማር፤ በዚህ ሰፊ የሆነ አለም ውስጥ ያለውን የአላህ ተዓምር ማስተንተን ናቸው፡፡
አላህ በተከበረው ቁርኣን የሚከተለውን ተናግሯል፡-

رَبَّنَا مَا خَلَقْتَ هَٰذَا بَاطِلًا سُبْحَانَكَ فَقِنَا عَذَابَ النَّارِ
«ጌታችን ሆይ! ይኸን በከንቱ አልፈጠርከውም፤ ጥራት ይገባህ፤ ከእሳትም ቅጣት ጠብቀን» የሚሉ ናቸው፡፡አል ኢምራን፡ 191

የአላህን ትእዛዝ አጥብቆ መያዝ፤ ወደአላህ መቃረብን አላማ በማድረግ ዒባዳዎችን በጥንክርና ተፈጻሚ ማድረግ ኢማንን ይጨምራል፡፡ አላህ በተከበረው ቁርኣን የሚከተለውን ተናግሯል፡-

‟وَالَّذِينَ جَاهَدُوا فِينَا لَنَهْدِيَنَّهُمْ سُبُلَنَا ۚ وَإِنَّ اللَّهَ لَمَعَ الْمُحْسِنِينَ

‟እነዚያም በእኛ መንገድ የታገሉ መንገዳችንን በእርግጥ እንመራቸዋለን፡፡ አላህም በእርግጥ ከበጎ ሠሪዎች ጋር ነው፡፡
አንከቡት፡ 69

ኢማንን የሚያጓድሉና የሚቀንሱ ነገሮች፡-
በአላህ ዲን ላይ ማህይም (ጃሂል) መሆን፤ አኼራን መርሳት ወይም መዘንጋት፤ ከአላህ ህግ ማፈንገጥ፤ ወንጀል መስራት፤ በመጥፎ ለምትጎተጉት ነፍስ ታዛዥ መሆን፤ ከአመጸኞች ጋር መቀላቀል፤ ስሜትን እና ሰይጣንን መከተል፤ በዱንያ መሸንገል፤ ዱንያን የመጨረሻ ትልቁ ዓላማና ግብ ማድረግ ናቸው፡፡

⬅️ ‟روى الحاكم في"المستدرك"من حديث عبد الله بن عمرو بن العاص رضي الله عنه أن النبي صلى الله عليه وسلم قال":إن الإيمان ليخلق في جوف أحدكم كما يخلق الثوب الخلق ، فاسألوا الله أن يجدد اإليمان في قلوبكم"
➡️‟ የአላህ መልክተኛ ﷺ የሚከተለውን ተናግረዋል፡-
“ልክ ልብስ እንደሚያልቀው ኢማን በአንዳችሁ ውስጥ ያልቃል ፤ በልቦቻችሁ ውስጥ ኢማንን እንዲያድስላችሁ አላህን ለምኑት፡፡”
ሃኪም ፊልሙስተድረክ፡ 5
ሐዲሱን አልባኒ ሶሂህ ብለውታል ሶሂሁ አልጃሚዕ፡ 1590

ኢማንን ለማደስ ነብዩ ﷺ የሚከተለውን አቅጣጫ ሰጠዋል፡-
"فاسألوا الله أن يجدد اإليمان في قلوبكم"
“ኢማንን በልቦቻችሁ ውስጥ እንዲያድስ አላህን ጠይቁ፡፡

ኢማናችንን እንዲያድስልን፣ እንዲያጠነክርልንና እንዲያመቻችልን አላህን ችክ ብሎ መለመን ያስፈልጋል፡፡ አላህ በተከበረው ቁርኣን የሚከተለውን ተናግሯል፡-

يُثَبِّتُ اللَّهُ الَّذِينَ آمَنُوا بِالْقَوْلِ الثَّابِتِ فِي الْحَيَاةِ الدُّنْيَا وَفِي الْآخِرَةِ

‟አላህ እነዚያን ያመኑትን በቅርቢቱም ሕይወት በመጨረሻይቱም (በመቃብር) በተረጋገጠው ቃል ላይ ያረጋቸዋል፡፡
ኢብራሒም፡ 27

ኢማንን በልቦና ውስጥ ለማረጋገጥ ወይም ለማሟላት እያንዳንዱ ሰው የራሱን ጥረት ማድረግና መታገል አለበት፡፡ የዚህ ማህበረሰብ ቀደምቶች ለዚህ ትልቅ አብነት ናቸው፡፡ ኢማንን ወደራሳቸው ለማምጣት ከፍተኛ ትግል አደረጉ፤ ኢማን ከምግብ፣ ከመጠጥ እና ከአየር ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባ መሆኑን ተገነዘቡ፡፡ እምነታቸውን በየጊዜው አደሱ፤ ኢማን የሚጨምሩ ነገሮችን ሰሩ፤ በዚህም ትክክለኛ የሆነውን ኢማን አረጋገጡ፡፡

◾️ዑመር  ለጓደኞቹ “ኑ ወደዚህ እምነታችንን እንጨምር” ይላቸው ነበር፡፡

◾️ዓብደላህ ብን መስዑድ ደግሞ  “ኑ ከእኛ ጋር ተቀመጡ ኢማናችንን እናድስ” ይል ነበር፡፡ የሚከተለውን ዱዓም ያደርግ ነበር ፡- “አላህ ሆይ! ኢማንን ጨምርልን፤ እርግጠኝነትን ስጠን”
ዓብደላህ ብን አህመድ ፊ አስሱንና፡ 797

◾️ዓብደላህ ብን ረዋሃ 4 የጓደኞቹን እጅ ይዞ “እርሱን በመታዘዝ በምህረቱ እንዲያስታውሰን ኑ! የተወሰነ ሰዓት እንመን፤ አላህን እናስታውስ፤ ኢማናችንን እንጨምር” ይል ነበር፡፡
ኢብኑ አቢ ሸይባህ፡ 30426

◾️አቡደርዳእ ደግሞ “እምነታቸው ከሚጨምርላቸው ሰዎች ነኝ? ወይስ ከሚጎድልባቸው? የሚል ጥያቄ ለነፍሱ የሚጠይቅ ከሆነ ይህ ሰው የእውቀት ባለቤት ለመሆኑ አመላካች ነው” ይል ነበር፡፡ ይህ ማለት አንድ ሰው ሰይጣን በየት በኩል መጦ እንደሚጎተጉተው ካወቀ ይህ ሰው የእውቀት ባለቤት ለመሆኑ አመላካች ነው ማለት ነው፡፡ አልኸላል ፊ አስሱናህ፡ 1585
ኢብኑ በጣህ ፊ አልኢባነቲ አልኩብራ፡ 1140

◾️ዑመይር ብን ሀቢብ  የሚከለተለውን ይናገር ነበር “ኢማን ይጨምራል ይቀንሳል”፤ “ምንድን ነው መጨመር መቀነስ” የሚል ጥያቄ ቀረበለት፤ “አላህን ስናስታውስ፤ ስናመሰግነው፤ ስናጠራው ይህ ነው የኢማን መጨመሩ፤ ስንዘነጋ፤ (ፈርዶችን) ስንተው ስንረሳ ደግሞ ይህ ነው የኢማን መጉደል” የሚል ምላሽ ሰጠ፡፡
ኢብኑ አቢ ሸይባህ
ዓብደላህ ብን አህመድ ፊ አስሱንናህ ፡ 624

"የኢማን ትሩፋት ኢማን ይጨምራል ይቀንሳል" ከሚለው ሪሳላህ የተወሰዴ!!

┄┄┉┉✽‌»‌🌹🌹»‌✽‌┉┉┄┄
   ሼር 👇JoiN👇 & Share
http://www.tg-me.com//@arebgendamesjid
    ።።።።።።።።።።።።🍡🍡።።።።።።።።።

شباب عرب غندي مسجد
የሽርክ  አይነቶች ሁለት ናቸው ፡-

ሽርኩል አክበር
ሽርኩል አሰስገር ይባላሉ


ሽርኩል አክበር (ትልቁ ሽርክ) ፡

ይህ ትልቁ ሽርክ የተባለው ከእስልምና የሚያስወጣ ነው ፡ተውበት ሳያደርግ የሞተም ከሆነ
እሳት ዘውታሪ የሚያደርገው የሆነ ትልቅ ወንጀል ነው፡
ይህ ሽርከል አክበር የተባለው ከአምልኮ ዘርፎችን ከአሏህ ሌላ ለሆነ ፍጡር መስጠት ነው ከነዚህም መካከል

ከአሏህ ሌላን መለመን , ቀብሮች ላይ ማረድ , የሞቱ ሰዎችንም እንዲሁም ጂኖችን መፍራት ይጎዳሉ , ይገላሉ ,ያሳምማሉ በማለት ማመን, እንዲሁም ከአሏህ ሌላ በሆነ አካል እርዳታን መፈለግ  አቅም (ችሎታ) በሌለው ነገር እና የመሳሰሉት የሽርክ አክበር ሁኔታዎች አሉት

ሽርኩል አስገር (ትንሹ ሽርክ):-
ይህ ትንሹ ሽርክ የተባለው ከእስልምና የማያስወጣ ሲሆን ነገር ግን ተውሂድን ያጎድላል ወደ ትልቁ ሽርክም አዳራሽ ነው ፡፡
  
ይህም ሁለት ሁኔታዎች ሲኖሩት

አንደኛው፡- በአካል ወይም በግልፅ የሚደርግ ሽርክ

ከነሱም ውስጥ በንግግር ከሚደረጉት የሺርክ አይነቶች

ከ አሏህ ሌላ በሆነ አካል መማል የአሏህ መልእክተኛ صلى الله عليه وسلم እንዲህ አሉ

  《من حلف بغير الله فقد كفر او أشرك 》.

[ ከአሏህ ሌላ የማለ በእርግጥም ከፍሯል(ከሀይማኖቱ ወጥቷል) ወይም አጋርቷል].

እንዲሁም (አሏህ እና አንተ ከፈለጋችሁ) የሚለው ንግግር መጠቀም
የአሏህ መልእክተኛ صلى الله عليه وسلم አንድን ሰው አሏህ እና አንተ ከፈለጋችሁ ባለ ሰአት እንዲህ አሉት


《 اجعلتني لله ندا !؟!  قل: ماشاء الله وحده》.
[የአሏህ አጋዥ(ረዳት)አደረከኝን፡  አሏህ ብቻውን ከፈለገ በል].

ከተግባር ከሚፈፀሙ የሽርክ አይነቶች  ደግሞ ፡

ልክ እርዝን ማንጠልጠል የሚመጡ አደጋዎችን ይከላከላሉ በማለት ይህ ሰብብ ናቸው ብሎ ካመነ ነው ነገር ግን እነዚህን ነገሮች ራሳቸው ጉዳት ያመጣሉ ብሎ ካመነ ግን ይህ ሽርከል አክበር ይሆናል ፡፡

ሁለተኛው አይነት ከትንሹ ሽርክ

ቀላሉ ሽርክ የሚባለው ነው እሱም ምንድነው ይዩልኝ ይስሙልኝ ወይም በኒያ(በሀሳብ) የሚገኝ የሽርክ አይነት ነው ፡

ይዩልኝ ይስሙልኝ ማለት ምን ማለት ነው ፡ አንድን ስራ ይሰራል ወደ አሏህ የሚያቃርበውን በዚህ ስራው ይፈልጋል የሰዎችን ውዳሴ እና ሙገሳ ፡ ልክ ሶላቱን እንደ ማሳመር ወይም ሶዶቃን(ምፀዋት) ያደርጋል የሰዎችን ውዳሴ ፈልጓ ወይም ድምፁን ያሳምራል ቁርአንን በሚቀራበት ሰአት ሰዎች እንዲያሞግሱት

ይዪልኝ ይስሙልኝ ማለት ከስራ ጋር ከመጣ ሰራውን ውድቅ ያደርገዋል
አሏህ سبحنه وتعالى እንዲህ ይላል

《فمن كان يرجوا لقاء ربه فليعمل عمﻻ صالحا ولا يشرك بعبادة ربه احدا》[الكهف :١١٠ ]

[ ከጌታው ጋር መገናኘትን የሚመኝ ጥሩ ስራን ይስራ በጌታው አምልኮም ላይ አንድንም እንዳያጋራ] {ከሕፍ :110}

እንዲሁም የአሏህ መልእክተኛ صلى الله عليه وسلم እንዲህ አሉ

☆ أخوف ما أخاف عليكم الشرك اﻷصغر ، قالوا يارسول الله ، وما الشرك اﻷصغر؟ فقال : (الرياء ).

ለእናንተ ከምፈራላችሁ ፍራቻ ትንሹን ሽርክ ነው አሉ ,ሶሀቦች ምንድነው ትንሹ ሽርክ ብለው ጠየቁ ? የአሏህ መልእክተኛ صلى الله عليه وسلم
(እዪልኝ ስሙልኝ) ማለት ነው አሏቸው ፡፡

ይህንንም ስራ የሚሰራው የዱንያ ኑሮውን ሊያመቻች ብሎ ሊሠራም ይችላል ልክ ሰዎችን በማሰገድ ላይ ያለ ወይም አዛን የሚልም ሊሆን ይችላል ገንዘብን ለመሰብሰብ  ብሎ እውቀትን መውሰድ  ይገኙበታል  ፡፡

📚 ኢብኑል ቀዮም እንዲህ ይላል ፡-

" ይህ የሽርክ አይነት በጣም ሰፊ እንደ ባህር ነው ማቆሚያ የለውም ፡ ከዚህ ነገር የሚድኑት ጥቂቶቹ ናቸው ፡ በስራው ከአሏህ ፊት ውጪ የፈለገበት ከሆነ ይህ በእርግጥም ሽርክን አሰገኝቷል::

   ሼር 👇JoiN👇 & Share

ሌሎችም የተለያዩ ትምህርቶች ለማግኘት ከታች ያለውን ሊንክ ይጫኑ
http://www.tg-me.com//@arebgendamesjid
┈┅𝑱𝑶𝑰𝑵 𝑨𝑵𝑫 𝑺𝑯𝑨𝑹𝑬⤴️⤴️⤴️
አንዲት አባቷ የመስጅድ ኢማም የሆነች ልጅ ነበረች። ልጁ በቁንጅናዋ ተማርኮ ዚና እንዲሰሩ ይጠይቃታል፤ ቆንጆይቱም "እሺ ነገር ግን ሁለት መስፈርቶች አሉኝ እነርሱን ካሟላህ " ትለዋለች። መስፈርቷንም በዚህ መልኩ ትነግረዋለች።
1ኛ) ትንሽ ጊዜ ስጠኝ።
2ኛ) እንደምታቀው አባቴ የመስጅድ ኢማም ነው እና ስጠኝ እስካልኩህ ግዜ ድረስ መስጅድ እየሄድክ በጀመዐ ሶላትህን ስገድ" ትለዋለች።
:
ልጁም እሺ ብሎ ተስማማ።
ቃሉንና መስፈርቱን ለመጠበቅ ሲል መስጅድ መሄድን አዘወተረ።

በመጨረሻም የሰጣት ግዜም አለቀ።
"ያንን የሰሳጠሁህን መስፈርት ተገበርከው ቃልህንስ በትክክል እያከበርክ ነው" የሚል ጥያቄ አነሳችለት።
እርሱም "አወ! እየተገበርኩ ነው ነገር ግን ቃል ያስገባሁሽን ነገር አላህ ይቅር ይበለኝ። ሁሉም ነገር ተቀይሯል። መስጅድ በምመላለስበት ሰዓት ወደ አላህ ተመልሻለሁ" አላት።

አርሷም "ማሻ አላህ! እኔም እሺ ያልኩህ ዝሙት ለመስራት ሳይሆን "ሶላት ከመጥፎና ከሚጠላ ነገር ሁሉ ትከለክላለች" በሚለው በዚህ በአላህ ቃል እርግጠኝነት ተሞልቼ ነው።

اتْلُ مَا أُوحِيَ إِلَيْكَ مِنَ الْكِتَابِ وَأَقِمِ الصَّلَاةَ ۖ إِنَّ الصَّلَاةَ تَنْهَىٰ عَنِ الْفَحْشَاءِ وَالْمُنكَرِ ۗ وَلَذِكْرُ اللَّهِ أَكْبَرُ ۗ وَاللَّهُ يَعْلَمُ مَا تَصْنَعُونَ
ከመጽሐፍ ወደ አንተ የተወረደውን አንብብ፡፡ ሶላትንም ደንቡን ጠብቀህ ስገድ፡፡ ሶላት ከመጥፎና ከሚጠላ ነገር ሁሉ ትከለክላለችና፡፡ አላህንም ማውሳት ከሁሉ ነገር በላጭ ነው፤ አላህም የምትሠሩትን ሁሉ ያውቃል፡፡
📒ሱረቱል አንከቡት (45)
http://www.tg-me.com//@arebgendamesjid
🔗SHARE 🔗SHARE  
ድንቅ አባባል

ከመልካም ስራ የመጀመሪያው
   ክፉነትን መተው ነው።🍂

➲ ከአዋቂዎችም ከሞኝም ጋር አትከራከር። አዋቂ   
     ያሸንፍሃል፤ ሞኝ ደግሞ ያበሳጭሃል።

➲ የበታቹን የናቀ ግርማ ሞገሱን (ክብሩን) ያጣል።

➲ የእውቀት መጀመሪያ ዝም ማለት፤ ከዚያም መስማት፤
     የሰማውን መያዝ፤ ከዚያም መስራት፤ በመቀጠል
      ማሰራጨት ነው።
___


*መልካም ቀን*🌺
http://www.tg-me.com//@arebgendamesjid
🔗SHARE 🔗SHARE
https://youtu.be/hHFSfgbGFfk
عن أبي ذر عن النبي ﷺ :

« أن ناسا من أصحاب النبي ﷺ قالوا للنبي ﷺ : يا رسول الله، ذهب أهل الدُّثُورِ بالأجور، يصلون كما نصلي، ويصومون كما نصوم، ويتصدقون بفضول أموالهم، قال : أوليس قد جعل الله لكم ما تصدقون؛ إن بكل تسبيحة صدقة، وكل تكبيرة صدقة، وكل تحميدة صدقة، وكل تهليلة صدقة، وأمر بالمعروف صدقة، ونهي عن منكر صدقة... ».

📜 صحيح مسلم
#شباب_عرب_غندى_مسجد
‏قال أنس رضي الله عنه :

ما نظرنا منظرًا كان أعجبُ إلينا من وجهِ النَّبي ﷺ

صحيح البخاري
#شباب_عرب_غندى_مسجد
2024/09/28 18:11:43
Back to Top
HTML Embed Code: