የደብረ ምሕረት አቡን ቤት ቅዱስ ገብርኤል ቅኔ ምስክር ጉባኤ ቤት ደቀ መዛሙርትን አስመረቀ።
በማእከለዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት የደብረ ምሕረት አቡን ቤት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም የቅኔ ምስክር ጉባኤ ቤት 21 ደቀ መዛሙርትን ታኅሣሥ 27 ቀን 2017 ዓ.ም አስመርቋል ።
በመርሐ ግብሩ ላይ የማእከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ዮሐንስ ፣የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ሥልጣናት ቆሞስ አባ ዮሴፍ ፣ ከተለያዮ ቦታዎች የመጡ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን እንዲሁም በርካታ ሕዝበ ክርስቲያን ተግኝተዋል።
የቀዳሜ አድባራት አበራ ቅዱስ ጊዮርጊስ የቅኔ ምስክር መምህር ወላደ አእላፋት ጌድዎን አበበ ና ተመራቂ ደቀ መዛሙርቱ ቅኔ አቅርበዋል።
ብፁዕነታቸው ባስተላለፉ መልእክት ጉባኤ ቤቱ ያለበትን ችግር ተቋቁሞ በርካታ ደቀ መዛሙርትን እያፈራ በመሆኑ ትኩረት የሚፈልግ ጉባኤ ቤት ነው ብለዋል።
ጉባኤ ቤቱ የቦታ ጥበት እና ከከተማ በሚለቀቅ ፍሳሽ ከፍተኛ ችግር እየደረሰበት በመሆኑ በዘመናዊ መልኩ ለመገንባት የሕንጻ ዲዛይኑ ተሰርቶ መጠናቀቁም ተጠቁሟል።
በማኅበረ ቅዱሳን የጎንደር ማእከል ጽሕፈት ቤት ኃላፊ የሆኑት ፍቃደ ፈጠነ በጉባኤ ቤቱ ዘርፈ ብዙ ችግሮች መኖሩን ጠቅሰው ግንባታው ተጀምሮ በታቀደለት ዕለት እንዲጠናቀቅ ከሀገር ውጭና በሀገር ውስጥ የሚኖሩ ምእመናን ተሳትፎ ያስፈልጋል ብለዋል።
በማእከለዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት የደብረ ምሕረት አቡን ቤት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም የቅኔ ምስክር ጉባኤ ቤት 21 ደቀ መዛሙርትን ታኅሣሥ 27 ቀን 2017 ዓ.ም አስመርቋል ።
በመርሐ ግብሩ ላይ የማእከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ዮሐንስ ፣የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ሥልጣናት ቆሞስ አባ ዮሴፍ ፣ ከተለያዮ ቦታዎች የመጡ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን እንዲሁም በርካታ ሕዝበ ክርስቲያን ተግኝተዋል።
የቀዳሜ አድባራት አበራ ቅዱስ ጊዮርጊስ የቅኔ ምስክር መምህር ወላደ አእላፋት ጌድዎን አበበ ና ተመራቂ ደቀ መዛሙርቱ ቅኔ አቅርበዋል።
ብፁዕነታቸው ባስተላለፉ መልእክት ጉባኤ ቤቱ ያለበትን ችግር ተቋቁሞ በርካታ ደቀ መዛሙርትን እያፈራ በመሆኑ ትኩረት የሚፈልግ ጉባኤ ቤት ነው ብለዋል።
ጉባኤ ቤቱ የቦታ ጥበት እና ከከተማ በሚለቀቅ ፍሳሽ ከፍተኛ ችግር እየደረሰበት በመሆኑ በዘመናዊ መልኩ ለመገንባት የሕንጻ ዲዛይኑ ተሰርቶ መጠናቀቁም ተጠቁሟል።
በማኅበረ ቅዱሳን የጎንደር ማእከል ጽሕፈት ቤት ኃላፊ የሆኑት ፍቃደ ፈጠነ በጉባኤ ቤቱ ዘርፈ ብዙ ችግሮች መኖሩን ጠቅሰው ግንባታው ተጀምሮ በታቀደለት ዕለት እንዲጠናቀቅ ከሀገር ውጭና በሀገር ውስጥ የሚኖሩ ምእመናን ተሳትፎ ያስፈልጋል ብለዋል።
❤18👍11
በማኅበረ ቅዱሳን ዲላ ማእከል አቡነ ጎርጎርዮስ ት/ቤት የልደት በዓልን ምክንያት በማድረግ ለነዳያን የምግብና የስጦታ መርሐ ግብር ተካሄደ።
በዲላ አቡነ ጎርጎርዮስ ት/ቤት በተቋቋመው የበጎ አድራጎት ማኅበር ኮሚቴ ከተለያዩ ምእመናን የአልባሳትና የምግብ ግብዓቶችን በማሰባሰብ ድጋፍ ለሚፈልጉ ወገኖቻችን የማዕድ ማጋራትና የአልባሳት ስጦታ አካሂዷል።
የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓልን ምክንያት በማድረግ በተከናወነው በዚህ መርሐ ግብር ላይ የዲላ ወለሜ ደብረ ሰላም ቅዱስ ዑራኤል ደብር አስተዳዳሪ የሆኑት መልአከ ሰላም ቀሲስ አምሳሉ "በጎ ኅሊና ይኑርህ " በሚል መሪ ቃል ትምህርተ ወንጌል የሰጡ ሲሆን የማኅበረ ቅዱሳን የዲላ ማእከል የአቡነ ጎርጎርዮስ ት/ቤት ርእሰ መምህር በሆኑት አቶ ታደለ በጌዴኦ ቋንቋ የመርሐ ግብሩን ዓላማ እና መልእክት አስተላልፈዋል።
በዲላ አቡነ ጎርጎርዮስ ት/ቤት በተቋቋመው የበጎ አድራጎት ማኅበር ኮሚቴ ከተለያዩ ምእመናን የአልባሳትና የምግብ ግብዓቶችን በማሰባሰብ ድጋፍ ለሚፈልጉ ወገኖቻችን የማዕድ ማጋራትና የአልባሳት ስጦታ አካሂዷል።
የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓልን ምክንያት በማድረግ በተከናወነው በዚህ መርሐ ግብር ላይ የዲላ ወለሜ ደብረ ሰላም ቅዱስ ዑራኤል ደብር አስተዳዳሪ የሆኑት መልአከ ሰላም ቀሲስ አምሳሉ "በጎ ኅሊና ይኑርህ " በሚል መሪ ቃል ትምህርተ ወንጌል የሰጡ ሲሆን የማኅበረ ቅዱሳን የዲላ ማእከል የአቡነ ጎርጎርዮስ ት/ቤት ርእሰ መምህር በሆኑት አቶ ታደለ በጌዴኦ ቋንቋ የመርሐ ግብሩን ዓላማ እና መልእክት አስተላልፈዋል።
👍23❤6🙏1
የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በዓል የእንኳን አደረስዎ መርሐ ግብር ተከናወነ።
ጥር ፩ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም
የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በዓል የእንኳን አደረስዎ መርሐ ግብር በጽርሐ ተዋሕዶ ተካሂዷል።
በመርሐ-ግብሩ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ የየመምሪያ ኀላፊዎች የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሥራ ኃላፊዎች፣ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ሠራተኞች የአድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
የአዲስ አበባ ገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች በጽሑፍ የተደገፈ የእንኳን አደረሰዎ መልእክት ያስተላለፉ ሲሆን በዓሉን የተመለከተ ዝማሬ በሊቃውንት ቀርቧል።
ቅዱስ ፓትርያርኩም በመርሐ ግብሩ ለተገኙት እንግዶች የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላልፈዋል።
ምንጭ የኢ/ኦ/ተ/ቤ መገናኛ ብዙኃን አገልግሎት ስርጭት ድርጅት/EOTC
ጥር ፩ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም
የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በዓል የእንኳን አደረስዎ መርሐ ግብር በጽርሐ ተዋሕዶ ተካሂዷል።
በመርሐ-ግብሩ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ የየመምሪያ ኀላፊዎች የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሥራ ኃላፊዎች፣ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ሠራተኞች የአድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
የአዲስ አበባ ገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች በጽሑፍ የተደገፈ የእንኳን አደረሰዎ መልእክት ያስተላለፉ ሲሆን በዓሉን የተመለከተ ዝማሬ በሊቃውንት ቀርቧል።
ቅዱስ ፓትርያርኩም በመርሐ ግብሩ ለተገኙት እንግዶች የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላልፈዋል።
ምንጭ የኢ/ኦ/ተ/ቤ መገናኛ ብዙኃን አገልግሎት ስርጭት ድርጅት/EOTC
👍16❤7🕊1