መጋቢት ፳፯ ቀን ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል በተሰቀለ ጊዜ፤ የተሰቀለው የክብር ባለቤት ሰማይን የፈጠረ ነውና ፀሐይ ጨልማለች፣ ጨረቃ ደም ሆኗል፣ ከዋክብት ረግፈዋል። የተሰቀለው የክብር ባለቤት ምድርንም የፈጠረ ነውና በምድር የቤተ መቅደሱ መጋረጃ ከላይ እስከ ታች ለሁለት ተቀዷል፤ ምድር ተናውጣ ዐለቶች ተሠንጥቀዋል፤ መቃብራት ተከፍተዋል፤ ከ፭፻ በላይ ሙታን ተነሥተዋል (ማቴ ፳፯ )፡፡
ከጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለት መታሰቢያ ጋር ቤተ ክርስቲያን በ15ኛው መ.ክ.ዘ የነበሩትን አቡነ መብዓ ጽዮንን ታስባለች፡፡ አቡነ መብዓ ጽዮን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስን ‹‹ በዕለተ ዓርብ የተቀበልከውን መከራ ግለጽልኝ ››ብለው በጸለዩ ጊዜ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዕለተ ዓርብ የተቀበላቸውን መከራዎች ሁሉ አሳያቸው፡፡
የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ከርስቶስን መከራ ካዩበት ቀን ጀምሮ ሕማሙን መከራውን ግርፋቱን እስራቱን በጠቅላላ አሥራ ሦስቱን ሕማማተ መስቀል በማሰብ ጀርባቸውን በአለንጋ ይገርፉ ፤ ራሳቸውን በዘንግ ይመቱ ነበር፡፡
የጌታችንን ሕማማተ መስቀል እያሰቡ ዘወትር ስለሚያለቅሱ ዐይናቸው ጠፍቶ ነበር፡፡ ነገር ግን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የብርሃን ጽዋ ይዛ መጥታ ዐይናቸውን ቀብታ አድናቸዋለች፡፡ በዚህ የተነሣ ‹‹በትረ ማርያም›› እየተባሉ እንደሚጠሩ ገድላቸው ያስረዳል፡፡ በዚህ መሠረት ጥቅምት ፳፯ ቀን ለአቡነ መብዓ ጽዮን ቃልኪዳን የገባበት ቀን በመሆኑ በየዓመቱ ጥቅምት ፳፯ ቀን ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ዝክረ ጥንተ ስቅለቱ ጋር ይከበራል፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ከጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለት መታሰቢያ ጋር ቤተ ክርስቲያን በ15ኛው መ.ክ.ዘ የነበሩትን አቡነ መብዓ ጽዮንን ታስባለች፡፡ አቡነ መብዓ ጽዮን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስን ‹‹ በዕለተ ዓርብ የተቀበልከውን መከራ ግለጽልኝ ››ብለው በጸለዩ ጊዜ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዕለተ ዓርብ የተቀበላቸውን መከራዎች ሁሉ አሳያቸው፡፡
የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ከርስቶስን መከራ ካዩበት ቀን ጀምሮ ሕማሙን መከራውን ግርፋቱን እስራቱን በጠቅላላ አሥራ ሦስቱን ሕማማተ መስቀል በማሰብ ጀርባቸውን በአለንጋ ይገርፉ ፤ ራሳቸውን በዘንግ ይመቱ ነበር፡፡
የጌታችንን ሕማማተ መስቀል እያሰቡ ዘወትር ስለሚያለቅሱ ዐይናቸው ጠፍቶ ነበር፡፡ ነገር ግን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የብርሃን ጽዋ ይዛ መጥታ ዐይናቸውን ቀብታ አድናቸዋለች፡፡ በዚህ የተነሣ ‹‹በትረ ማርያም›› እየተባሉ እንደሚጠሩ ገድላቸው ያስረዳል፡፡ በዚህ መሠረት ጥቅምት ፳፯ ቀን ለአቡነ መብዓ ጽዮን ቃልኪዳን የገባበት ቀን በመሆኑ በየዓመቱ ጥቅምት ፳፯ ቀን ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ዝክረ ጥንተ ስቅለቱ ጋር ይከበራል፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
👍8🙏7
በአሜሪካን ሀገር በሳን ሆዜ ከተማ አዲስ ግቢ ጉባኤ ተመሠረተ፡፡
በዉጭ ዓለም ላለችው ቤተ ክርስቲያን ተረካቢ ለማፍራት እንዲሁም የከፍተኛ ትምህርት ቤት ተማሪዎች መንፈሳዊ ሕይወታቸውን ና ክርስትናቸውን ጠብቀው እንዲቆዩ የግቢ ጉባኤዎችን ማጠናከር አስፈላጊ በመሆኑ በማኅበረ ቅዱሳን የሳን ሆዜ ንዑስ ማእከል የቤይ ኤሪያ ግቢ ጉባኤ ምሥረታ ተካሂዷል፡፡
ግቢ ጉባኤው ጠንካራ ሆኖ እንዲቀጥልም ውይይት የተካሄደ ሲሆን የግቢ ጉባኤ ተሳትፎ በተማሪዎቹ ዘንድ ከፍተኛ ፍላጎት ያለ መሆኑን በማውሳት ለተግባራዊነቱ የሁሉም ኦርቶዶክስ ክርስቲያን ድርሻ መሆኑም ተጠቁሟል::
ግቢ ጉባኤ ለቤተ ክርስቲያን የሚጠቅሙ ነገ በምድረ አሜሪካ ቁልፍና ታዋቂ ካምፓኒዎች ውስጥ ተቀጥረው ቤተ ክርስቲያንን የሚደግፉ በሥነ ምግባር የታነጹ ኦርቶዶክስ ባለሙያዎችን የሚያፈራ ኦርቶዶክሳዊ ተቋም ነውም ተብሏል በመርሐ ግብሩ፡፡
በተለይም በቤይ ኤርያ እና አካባቢው የሚኖሩ ወላጆች ለከፍተኛ ተቋም ተማሪዎቻቸው ጊዜ ሰጥተው በግቢ ጉባኤ አገልግሎት ላይ ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርጉ እና በቀጣይነትም ከዚህ በተሻለ ትጋት እንዲሳተፉ መምህራኑ አደራ ብለዋል፡፡
በዉጭ ዓለም ላለችው ቤተ ክርስቲያን ተረካቢ ለማፍራት እንዲሁም የከፍተኛ ትምህርት ቤት ተማሪዎች መንፈሳዊ ሕይወታቸውን ና ክርስትናቸውን ጠብቀው እንዲቆዩ የግቢ ጉባኤዎችን ማጠናከር አስፈላጊ በመሆኑ በማኅበረ ቅዱሳን የሳን ሆዜ ንዑስ ማእከል የቤይ ኤሪያ ግቢ ጉባኤ ምሥረታ ተካሂዷል፡፡
ግቢ ጉባኤው ጠንካራ ሆኖ እንዲቀጥልም ውይይት የተካሄደ ሲሆን የግቢ ጉባኤ ተሳትፎ በተማሪዎቹ ዘንድ ከፍተኛ ፍላጎት ያለ መሆኑን በማውሳት ለተግባራዊነቱ የሁሉም ኦርቶዶክስ ክርስቲያን ድርሻ መሆኑም ተጠቁሟል::
ግቢ ጉባኤ ለቤተ ክርስቲያን የሚጠቅሙ ነገ በምድረ አሜሪካ ቁልፍና ታዋቂ ካምፓኒዎች ውስጥ ተቀጥረው ቤተ ክርስቲያንን የሚደግፉ በሥነ ምግባር የታነጹ ኦርቶዶክስ ባለሙያዎችን የሚያፈራ ኦርቶዶክሳዊ ተቋም ነውም ተብሏል በመርሐ ግብሩ፡፡
በተለይም በቤይ ኤርያ እና አካባቢው የሚኖሩ ወላጆች ለከፍተኛ ተቋም ተማሪዎቻቸው ጊዜ ሰጥተው በግቢ ጉባኤ አገልግሎት ላይ ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርጉ እና በቀጣይነትም ከዚህ በተሻለ ትጋት እንዲሳተፉ መምህራኑ አደራ ብለዋል፡፡
👍27❤20
የማኅበረ ቅዱሳን ስብከተ ወንጌል እና ሐዋርያዊ አገልግሎት ሦስት አብያተ ክርስቲያናትን አስገንብቶ አስመረቀ።
ማኀበረ ቅዱሳን በአሪና ደቡብ ኦሞ ዞኖች ሀገረ ስብከት ጥቅምት 23፣24 እና 25 ቀን 2017 ዓ.ም ሦስት አብያተ ክርስቲያናትን አስገንብቶ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት አድርጓል፡፡
የማኅበረ ቅዱሳን ስብከተ ወንጌል እና ሐዋርያዊ አገልግሎት አብያተ ክርስቲያናቱን ያስገነባው ባለድርሻ እና ተባባሪ አካላትን በማስተባበር ሲሆን የሦስቱ አብያተ ክርስቲያናት ሙሉ የግንባታ ወጪ 15 ሚልዮን 4 መቶ ሺህ ብር መሆኑ እና ወጪውንም በአሜሪካን ሀገር የሚገኙ የስብከተ ወንጌል ቤተሰቦች መሸፈናቸው ተገልጿል።
አብያተ ክርስቲያናቱ የተገነቡት ቀደም ባሉት ጊዜያት የቅድመ ጥምቀት ትምህርት ተሰጥቷቸው አምነው ለተጠመቁ አዳዲስ አማንያን እና በቅርበት ቤተ ክርስቲያን ባለመኖሩ ከምስጢራተ ቤተ ክርስቲያን እና ሥርዓተ አምልኮ ለመካፈል ሲቸገሩ ለነበሩ ምእመናን ነው ።
የተመረቁት ሦስቱ አብያተ ክርስቲያናት የወልባክ ቅዱስ ገብርኤል ፣ የጉዶ አሸከር አቡነ ተክለ ሃይማኖት እና የተንቤል ቅዱስ መርቆርዮስ አብያተ ክርስቲያናት ናቸው።
የአብያተ ክርስቲያናቱ ቅዳሴ ቤት ተከብሮ አገልግሎት በጀመረበት ዕለት ቀደም ባሉት ጊዜያት የቅድመ ጥምቀት ትምህርት ሲሰጣቸው የነበሩ 784 አዳዲስ አማንያን ተጠምቀው የቅድስት ሥላሴ ልጅነትን አግኝተዋል ።
በምርቃት መርሐግብሩ የአሪ እና የደቡብ ኦሞ ዞኖች ሀገረ ስብከት ልዑካን ፣ የማኀበረ ቅዱሳን ዋና ሥራ አስፈጻሚ እና ሌሎች ልዑካን እና የጂንካ ማእከል አባላት እንዲሁም የጽርሐ ጽዮን የሐዋርያት አንድነት የኑሮ ማኀበር ፣ የላፎቶ ደብረ ትጉኃን ሰ/ት/ቤት እና ጥሪ የተደረገላቸው የስብከተ ወንጌል ቤተሰቦች እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
ማኀበረ ቅዱሳን በአሪና ደቡብ ኦሞ ዞኖች ሀገረ ስብከት ጥቅምት 23፣24 እና 25 ቀን 2017 ዓ.ም ሦስት አብያተ ክርስቲያናትን አስገንብቶ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት አድርጓል፡፡
የማኅበረ ቅዱሳን ስብከተ ወንጌል እና ሐዋርያዊ አገልግሎት አብያተ ክርስቲያናቱን ያስገነባው ባለድርሻ እና ተባባሪ አካላትን በማስተባበር ሲሆን የሦስቱ አብያተ ክርስቲያናት ሙሉ የግንባታ ወጪ 15 ሚልዮን 4 መቶ ሺህ ብር መሆኑ እና ወጪውንም በአሜሪካን ሀገር የሚገኙ የስብከተ ወንጌል ቤተሰቦች መሸፈናቸው ተገልጿል።
አብያተ ክርስቲያናቱ የተገነቡት ቀደም ባሉት ጊዜያት የቅድመ ጥምቀት ትምህርት ተሰጥቷቸው አምነው ለተጠመቁ አዳዲስ አማንያን እና በቅርበት ቤተ ክርስቲያን ባለመኖሩ ከምስጢራተ ቤተ ክርስቲያን እና ሥርዓተ አምልኮ ለመካፈል ሲቸገሩ ለነበሩ ምእመናን ነው ።
የተመረቁት ሦስቱ አብያተ ክርስቲያናት የወልባክ ቅዱስ ገብርኤል ፣ የጉዶ አሸከር አቡነ ተክለ ሃይማኖት እና የተንቤል ቅዱስ መርቆርዮስ አብያተ ክርስቲያናት ናቸው።
የአብያተ ክርስቲያናቱ ቅዳሴ ቤት ተከብሮ አገልግሎት በጀመረበት ዕለት ቀደም ባሉት ጊዜያት የቅድመ ጥምቀት ትምህርት ሲሰጣቸው የነበሩ 784 አዳዲስ አማንያን ተጠምቀው የቅድስት ሥላሴ ልጅነትን አግኝተዋል ።
በምርቃት መርሐግብሩ የአሪ እና የደቡብ ኦሞ ዞኖች ሀገረ ስብከት ልዑካን ፣ የማኀበረ ቅዱሳን ዋና ሥራ አስፈጻሚ እና ሌሎች ልዑካን እና የጂንካ ማእከል አባላት እንዲሁም የጽርሐ ጽዮን የሐዋርያት አንድነት የኑሮ ማኀበር ፣ የላፎቶ ደብረ ትጉኃን ሰ/ት/ቤት እና ጥሪ የተደረገላቸው የስብከተ ወንጌል ቤተሰቦች እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
👍38❤25🙏1
የማኅበረ ቅዱሳን አዳማ ማእከል በከተማው ከሚገኙ የመንፈሳውያን ማኅበራት ኅብረት እና ከሰ/ት/ቤቶች አንድነት ጋር በመተባበር የደም ልገሳ እና የጽዳት መርሐ ግብር አከናወነ።
ኅዳር 1 ቀን 2017 ዓ.ም የማኅበረ ቅዱሳን አዳማ ማእከል ከመንፈሳውያን ማኅበራት ኅብረት እና ከሰ/ት/ቤት አንደንት ጋር በመተባበር በከተማዋ ሠፊ ንቅናቄ የተደረገበት የጽዳት እና የደም ልገሳ መርሐ ግብር አከናውኗል።
የአዳማ ከተማ መስተዳደር እና የከተማው ደም ባንክ ጋር በተባባሪነት በተሳተፉበት የደም ልገሳ መርሐ ግብር ላይ አቶ በሪሶ ዶሪ የአዳማ ከተማ መስተዳድር ከንቲባ ጽ/ቤት ኃላፊ፣ አቶ ሀብታሙ ግዛው የአዳማ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ም/ኃላፊ እና አቶ ኤልያስ ታደሰ የአዳማ ከተማ ጸጥታ ዘርፍ እና የሃይማኖቶች ጉዳይ ኃላፊን ጨምሮ ከ2000 በላይ የአዳማ ማእከል አባላት፣ የግቢ ጉባኤያት ተማሪዎች ፤የአዳማ ከተማ የሰ/ት/ቤቶች አባላት እና በአዳማ ከተማ የሚገኙ የመንፈሳውያን ማኅበራት አባላት ተገኘተው ደም ለግሰዋል።
" መልካም ሥራ ለመሥራት አንታክት" ገላ 6፥9 በሚል መሪ ቃል የተከናወነው መርሐ ግብር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እና ምእመናን በአገራዊ ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ንቁ ተሳትፎ የሚያሳይ እንደሆነ ተጠቅሷል።
ኅዳር 1 ቀን 2017 ዓ.ም የማኅበረ ቅዱሳን አዳማ ማእከል ከመንፈሳውያን ማኅበራት ኅብረት እና ከሰ/ት/ቤት አንደንት ጋር በመተባበር በከተማዋ ሠፊ ንቅናቄ የተደረገበት የጽዳት እና የደም ልገሳ መርሐ ግብር አከናውኗል።
የአዳማ ከተማ መስተዳደር እና የከተማው ደም ባንክ ጋር በተባባሪነት በተሳተፉበት የደም ልገሳ መርሐ ግብር ላይ አቶ በሪሶ ዶሪ የአዳማ ከተማ መስተዳድር ከንቲባ ጽ/ቤት ኃላፊ፣ አቶ ሀብታሙ ግዛው የአዳማ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ም/ኃላፊ እና አቶ ኤልያስ ታደሰ የአዳማ ከተማ ጸጥታ ዘርፍ እና የሃይማኖቶች ጉዳይ ኃላፊን ጨምሮ ከ2000 በላይ የአዳማ ማእከል አባላት፣ የግቢ ጉባኤያት ተማሪዎች ፤የአዳማ ከተማ የሰ/ት/ቤቶች አባላት እና በአዳማ ከተማ የሚገኙ የመንፈሳውያን ማኅበራት አባላት ተገኘተው ደም ለግሰዋል።
" መልካም ሥራ ለመሥራት አንታክት" ገላ 6፥9 በሚል መሪ ቃል የተከናወነው መርሐ ግብር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እና ምእመናን በአገራዊ ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ንቁ ተሳትፎ የሚያሳይ እንደሆነ ተጠቅሷል።
👍31❤4