Telegram Web Link
የሳርዶ ቅድስት ማርያም አዳሪ አብነት ትምህርት ቤት ለመጀመሪያ ጊዜ 9 ደቀ መዛሙርትን አስመረቀ።

በኢሉ ባቡር ሀገረ ስብከት በኖኖ ሰሌ ወረዳ ቤተ ክህነት በ2013 ዓ.ም የተመረቀው ዘመናዊ አዳሪ አብነት ትምህርት ቤት የመጀመሪያ ዙር በንባብና ቅዳሴ 9 የሚሆኑ ደቀ መዛሙረትን ግንቦት 11 ቀን 2016 ዓ.ም በደማቅ ሥነ ሥርዓት አስመርቋል።

በምረቃው መርሐ ግብር ላይ ተመራቂ ደቀመዛሙርቱ ወርብ ያቀረቡ ሲሆን በሁለት ዓመት የትምህርት ቆይታቸው ከአብነት ትምህርቱ ጎን ለጎን የትምህርተ ሃይማኖት የኮርስ ሥልጠና ሲሰጣቸው እንደነበር ተገልጿል ።

በማኀበረ ቅዱሳን የገዳማትና አብነት ት/ቤቶች ዋና ክፍል ም/ኃላፊ ዲ/ን ደረጀ ጋረደው ፣ የኢሉ ባቡር ሀገረ ስብከት ተወካይ ቀሲስ ጌቱ ሠይድ፣ የኖኖ ሰሌ ወረዳ ሊቀ ካህናት ቄስ ደረጀ ፈጠነ ፣ እንዲሁም የአካባቢው ህዝበ ክርስቲያን በመረሐ ግብሩ ላይ ተገኝተዋል።

ዲ/ን ደረጀ ጋረደው እንደተናገሩት ሀገረ ስብከቱ የአገልጋይ ካህናት እጥረት ያለበት መሆኑና በርካታ አብያተ ክርስቲያናት ቀዳሽ አጥተው ተዘግተው ያሉበት በመሆኑ የእነዚህ ደቀመዛሙርት መመረቅ ትልቅ አስተዋጽኦ አለው ያሉ ሲሆን አብነት ትምህርት ቤቱ ለሌሎች ክልሎች አጎራባች ስለሆነ የተለያየ ቋንቋ ተናጋሪዎችን ማፍራት እንደሚችል ጠቁመዋል።

የተማሪዎችን ሙሉ የቀለብ ወጭ የሸፈነው ማኅበረ ቅዱሳን ሲሆን ለዚህም ከ 700 ሽህ ብር በላይ ማድረጉም ተገልጿል።
ቅዱስነታቸው የደቡብ አፍሪካ ሐዋርያዊ አገልግሎታቸውን አጠናቀው አዲስ አበባ ገቡ።
**

ብፁ
ዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ
ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣ብፁዕ አቡነ ፊሊጶስ የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዮንቨርሲቲ ፕሬዝዳንት፣የደቡብ ኦሞና
አሪ ዞኖች ሊቀ ጳጳስ፣ብፁዕ አቡነ ጢሞቴዎስ የዳውሮ-ኮንታ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ የጠቅላይ ቤተክህነት የመምሪያ ኃላፊዎች በደቡብ አፍሪካ ሲያካሒዱት የቆዩትን ሐዋርያዊ አገልግሎት አጠናቀው ዛሬ ከቀትር በኋላ አዲስ አበባ ገብተዋል።

ቅዱስነታቸውና ከቅዱስ ፓትርያርኩ ጋር ወደ ደቡብ አፍሪካ የተጓዙት የልዑካን ቡድን አባላት ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የባህርዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ክቡር መልአከ ሕይወት ቆሞስ አባ ኃይለ ገብርኤል ነጋሽ የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ፣የጠቅላይ ቤተክህነት መምሪያ ኃላፊዎች አቀባበል አድርገው
ላቸዋል።

በመቀጠልም በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም የእንኳን ደህና መጡ አቀባበል መርሐ ግብር የሚካሔድ ሲሆን በዚሁ መርሐ ግብር ላይም ቅዱስ ፓትርያርኩ ትምህርተ ወንጌል፣ቃለ ምዕዳንና ቃለ ቡራኬ ሰጥተው የአቀባበል መርሐ ግብሩ የሚጠናቀቅ ይሆናል።

ምንጭ: የ/ኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
የኢ/ኦ/ተ/ቤ መንበር ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ከየአህጉረ ስበከቱ ለተወጣጡ የሕዝብ ግንኙነት ዋና ክፍል ሓላፊዎች ለሦስት ቀናት የሚቆየው ስልጠና የውይይትና ምክክር መድረክ እያካሄደ ይገኛል።

+++++++++++++++++++++++++++

<< ተደራሽነት ያለው የሕዝብ ግንኙነት ለኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን>> በሚል መሪቃል ከግንቦት 15 እስከ ግንቦት 17 ቀን 2016 ዓ.ም የሚቆየው ይህ ስልጠና እየተሰጠ የሚገኘው በአዲስ አበባ ጁፒተር ኢንተርናሽናል ሆቴል ነው።

የስልጠና እና የውይይት መድረኩ የተዘጋጀበት ዓላማ የሕዝብ ግንኙነት ሥራን ለቤተክርስቲያን በሚያግዝ መልኩ እንዲሰሩ ለማነሰሳት ነው።
በተጨማሪም በሥራቸው ወቅት የሚያገጥማቸውን ክፍተት የሚሞሉበትን ግንዛቤ ለመፍጠር መሆኑም ተጠቁሞዋል።

በመድረኩ ላይ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የባህር ዳር እና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ማርቆስ የስብከተ ወንጌል እና ሐዋርያዊ አገልግሎት መምሪያ የበላይ ሓላፊ ፣ ብጹዕ አቡነ ዲዮስቆርዮስ፣ የደቡባዊና ደቡባዊ ምሥራቅ ትግራይ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የጠቅላይ ቤተክህነት የየመምሪያ ሓላፊዎች፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፣ ከየአህጉረ ስበከቱ የተወጣጡ የሕዝብ ግንኙነት ዋና ክፍል ሓላፊዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶች ተገኝተዋል።
በሥልጣናው ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት በመንበረ ፓትርያርክ ጽ/ቤት የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ሓላፊ ሊቀ ሥዩማን እስክንድር ገ/ክርስቶስ በዚህ የውይይት መድረክ ለድክመቶቻችን የተለያዪ ምክንያቶችን ከመደርደር ወጥተን ያለንን አቅም አሟጠን ቤተ ክርስቲያንን በጋራ ማገልገል በምንችልበት ጉዳይ ላይ ተቋማዊ ትስስር ለመፍጠር አስበናል ነው ሲሉ ተናግረዋል።

ሓላፊው እክለውም ሥልጠናው ወሳኝ እና ታማኝ የመረጃ ሥርዓት መዘርጋት በምንችልበት ሁኔታ ዙሪያ ከቀኖና ቤተ ክርስቲያን ብሎም ከሕግ ሥርዓት አንጻር ግንዛቤ የምትጨብጡበት እና ለምትሰጡት አግልግሎት ተጨማሪ ግብዓት እድታገኙ የሚያግዝ በመሆኑ ትኩረት ልትሰጡት ይገባል ሲሉም አመላክተዋል።

ብፁዕ አቡነ አብርሃም በመድረኩ ባስተላለፉት መመሪያ አገልጋዬች ሕዝብን ከሕዝብ ምእመናን ከቤተ ክርስቲያን በማቀራረብ ችግር ፈቺ የሆኑ ሃሳቦችን በማመንጨት ዘምኑን የዋጅ አገልጋዬች መሆን ይጠበቅባችሁዋል ብለዋል።

ብፁዕነታቸው አክለውም ቅድስት ቤተክርስቲያን እያጋጠማት ካለው ፈተና እንድታልፍ የሕዝብ ግንኙነት መዋቅራዊ ሠንሰለቱን ጠብቆ የመረጃ ፍሰቱ በማጠናከር ቤተ ክርስቲያን በመጠበቅ ረገድ ሰፊ ስራ መስራት እንደሚጠበቅበት ተናግረዋል።

ብፁዕ አቡነ ማርቆስ በበኩላቸው የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ አገልጋዬችን በሥልጠና እንዲታገዙ እና የተሻለ አግልግሎት እንዲሰጡ ለማድረግ የሚያከናውነው ተግባር ሊበረታታ እንደሚገባ ገልጸዋል።

በመርሐ ግበሩ ላይ የተሳተፉት ከተለያዩ አሕጉረ ስብከት የተወጣጡ የሕዝብ ግንኙነት ዋና ክፍል ሓላፊዎች ሥልጠናው አስተማሪ በመሆኑ ቀጣይነተ ሊኖረው ይጋበል ብለዋል።
ሰንበት ትምህርት ቤቶች ለቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ያላቸው አስተዋፅኦ

ክፍል አንድ


በሐዋርያት ትምህርት ላይ የተመሠረተችው ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ዋናው ተልእኮዋ የምሥራች ቃልን ለዓለም ማዳረስ ነው። ይህን የምሥራቹን ቃል ለማዳረስም በተለያየ ዘመን ብዙ ፈተናዎች ገጥሟታል፡፡ ፈተናዋን በጸሎት እና በዘመኑ በነበሩ አበው ምእመናን ጥብዓት ተሻግራ አሁን ካለንበት ዘመን ደርሳለች። ከአባቶቻችን የተረከብናትን ቤተ ክርስቲያን ከእነ ሙሉ ክብሯ ለመጠበቅ ትምህርት ላይ መሥራት ለነገ የማይባል ሥራ መሆኑ የሚያጠራጥር ባይሆንም ነገር ግን አሁን ባለንበት ዘመን ያለውን የትምህርት አሰጣጥ ሁኔታ ስንገመግመው ትኩረት የሚያሻው ጉዳይ ነው።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከሐዋርያት የተቀበለችውን ትምህርት ለማስተማር ከምትጠቀምባቸው መንገዶች አንዱ ልጆቿን በሰንበት ትምህርት ቤት መዋቅር ውስጥ እንዲታቀፉ በማድረግ አስፈላጊውን ትምህርት እንዲያገኙ በማስቻል ነው። በመሆኑም የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች መጠንከርም ሆነ መድከም ቤተ ክርስቲያናችን ላይ ያለው ተጽዕኖ ቀላል ይሆናል ተብሎ አይታሰብም። በዚህ አጭር ጽሑፍ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ለቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ያላቸውን አስተዋፅኦ ለማየት እንሞክራለን።

ሰንበት ትምህርት ቤት ማለት ምን ማለት ነው?

ሰንበት ትምህርት ቤት ማለት በቤተ ክርስቲያን መዋቅር ሥር ታቅፈው በበዓላት፣ በዕረፍት ቀናት (በሰንበታት) በመገኘት ትምህርተ ሃይማኖት የሚማሩ ተማሪዎች ስብስብ ማለት ነው።

የአገልግሎት ትርጕም

የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ሲባል ገና ተጋድሎዋን ያልፈጸመችው እና የሚደርስባትን መከራ በጸጋ በመቀበል ክርስቶስን በመከራ ለመምሰል ሥርዓተ አምልኮዋን ዘወትር የምታከናውን ሲሆን ነው፡፡ “እግዚአብሔር የሰማዕትነትን ሥራ ይሰጠን ዘንድ እንማልዳለን” ብላ በዐጸደ ነፍስ ካሉ ቅዱሳን እንዲሁም ዘወትር ያለማቋረጥ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እያሉ ከሚያመሰግኑ ቅዱሳን መላእክት ጋር አንድ የሚያደርጋት አገልግሎት ተብሎ ሊገለጽ ይችላል።
ይቆየን!
2024/09/28 00:30:26
Back to Top
HTML Embed Code: