Telegram Web Link
ግዕዝ ክፍል 15

✟ልሣነ ግእዝ፥ክፍል 15✟

አቀድም አእኩቶቶ ለእግዚአብሄር
...
✍️በክፍል 14 ትምህርታችን የ8ቱን አርእስት አረባብ አይተናል።ያ አረባብ ለአብዛኛዎቹ ግሦች ቢያገለግልም በተለያየ አካሄድ ከዚያ የተለየ አረባብ ያላቸው ብዙ ናቸው

✍️በዚህ ክፍል ላቀርበው የፈለግሁት ቅጽል (Adjective) የሚሆኑትን ውስጠዘ እና ከዚያ በላይ ያሉትን ነው።
የስምንቱ አርእስት ውስጠዘዎች
ቀደሰ
ቅዱስ
ቅድስት
ቅዱሳን
ቅድስት
✟ቀተለ
ቅቱል
ቅትልት
ቅቱላት
ቅቱላን
✟ዴገነ
ዲጉን
ዲጉናን
ዲግንት
ዲጉናት
✟ባረከ
ቡሩክ
ቡርክት
ቡሩካን
ቡሩካት
✟ጦመረ
ጡሙር
ጡሙራን
ጡምርት
ጡሙራት
✟ክህለ
ክሁል
ክሁላን
ክህልት
ክሁላት
✟ተንበለ
ትንቡል
ትንቡላን
ትንብልት
ትንቡላት
...
ይህ ውስጠ ዘ ነው።
ሳልስ ውስጠ ዘ ሲሆን
ቀዳሲ፥ቀታሊ፥ዴጋኒ.... ጸሐፊ እያለ ይቀጥላል

ጥያቄ
የሚከተሉትን ቃላት ውስጠ ዘ አውጣ
1ኛ ሰደደ
2ኛ ሴሰየ

ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን

መሠረተ፡ግእዝ

@learnGeez1
@learnGeez1
@learnGeez1 👈
#ግዕዝ_ክፍል 16

✟ልሣነ ግእዝ፥ክፍል 16
አቀድም አእኩቶቶ ለእግዚአብሄር

መጣ ብለን ይመጣል ይምጣ ... የሚለውን አይተናል አሁን ይህን በ10ሩ መራሕያን ደግሞ መግለጽ አለብን ይህም ማለት ትመጣለች ይመጣሉ ይምጡ ትምጣ.... ወዘተ የሚለውን ለማወቅ የሚረዳን አካሄድ ከዚህ ቀጥሎ ያለው ነው።ቀደስን ለምሳሌ እንየው
1 ውእቱ=ቀደሰ=አመሰገነ
ይቄድስ=ያመሰግናል
ይቀድስ=ያመሰግን ዘንድ
ይቀድስ ያመስግን
ልክ እንደዚህ እያደረጋችሁ ትተረጉሙታላችሁ እንላ የግእዙ አመሰራረት ላሳያችሁ
2 ውእቶሙ=ቀደሱ፦ይቄድሱ፥ይቀድሱ፥ይቀድሱ
3 ውእቶን=ቀደሳ፦ይቄድሳ፥ይቀድሳ፥ይቀድሳ
4 ይእቲ=ቀደሰት፦ትቄድስ፥ትቀድስ፥ትቀድስ
5 አንተ=ቀደስከ፦ትቄድስ፥ትቀድስ፥ቀድስ
6 አንቲ=ቀደስኪ፦ትቄድሲ፥ትቀድሲ፥ቀድሲ
7 አንትሙ=ቀደስክሙ፦ትቄድሱ፥ትቀድሱ፥ቀድሱ
8 አንትን=ቀደስክን፦ትቄድሳ፥ትቀድሳ፥ቀድሳ
9 አነ=ቀደስኩ፦እቄድስ፥እቀድስ፥እቀድስ
10 ንሕነ=ቀደስነ፦ንቄድስ፥ንቀድስ፥ንቀድስ
...
ይላል ሁለተኛ መደቦች ትእዛዝ አንቀጻቸው ላይ "ይ" ን አስወግደው ይረባሉ።
በአነ ጊዜ በ "ይ" ምትክ "እ" ለንሕነ "ን" እንደሆነ ሁለተኛ መደቦች በሙሉ በ ይ ምትክ "ት"ን አድርገው እንደገቡ አስተውል።

አተረጓጎሙ ግልጽ ሊሆንልን ይገባል።የውእቱ ይቄድስ ይቀድስ ይቀድስ ያመሰግናል ያመሰግን ዘንድ ያመስግን ተብሎ ከተተረጎመ የአንተ ትቄድስ ትቀድስ ቀድስ ... ታመሰግናለህ ታመሰግን ዘንድ አመስግን ማለት እንደሆነ አስተውል... የሌላውንም በየራሱ እንዲሁ አድርገህ ተርጉም።የ ቀደሰን እንዲህ አደረግን እንጂ የሌሎችም እንዲሁ ነው።በክፍል 15 ያለውን መሰረት ሳይለቁ ይረባሉ።
ምሳሌ ውእቱ ባረከ ይባርክ ይባርክ ይባርክ ብለን እርሱ ያመስግን ያመሰግን ዘንድ ያመስግን ብለን ነበር።ስለዚህ ለ እኔ ሲሆን ባረኩ እባርክ እባርክ እባርክ እልና ትርጉሙን አመሰገንኩ አመሰግናለሁ አመሰግን ዘንድ ላመስግን ብየ መተርጎም።ማለት ነው።

ሌላ የመጨረሻ ምሳሌ ውእቱ ክህለ ብለን ይክህል ይክሀል ይክሀል ብለን ነበር ትርጉሙ ይችላል ይችል ዘንድ ይቻል ነው።ስለዚህ ይህን እናንተ ቻላችሁ ለማለት አንትሙ ክህልክሙ ይላክ ክህልክሙ ትክህሉ ትክሀሉ ከሀሉ እላለሁ ትርጉሙ የላይኛውን መሰረት አይለቅም ይኽውም ቻላችሁ ትችላላችሁ ትችሉ ዘንድ ቻሉ ይላል።
✍️ምናልባት ከክፍል 15 የውስጠ ዘ ትርጉም።የአንዱን ልስራውና የሌላውን ይህን መሰረት አድርጋችሁ መተርጎም ትችላላችሁ
ቅቱል ብሎ የገደለ ገዳይ የሚገድል
ቅትልት ብሎ የገደለች ገዳይ የምትገድል
ቅቱላን ብሎ የገደሉ ገዳዮች የሚገድሉ ይላል
ቅቱላት ብሎ የገደሉ ገዳዮች ይላል ለሴቶች ስለዚህ ከክፍል 15 ያሉትን የሌሎችንም በዚህ መሰረት መተርጎም ቀላል ነው አንዱን ልተርጉመው
ምሳሌ:- ትንቡል=የለመነ፥ለማኝ፥የሚለምን
ትንብልት=የለመነች፥ለማኝ፥የምትለምን
ትንቡላን=የለመኑ ለማኞች የሚለምኑ
ትንቡላት ለሴቶች የለመኑ እያልክ
መፍታት ትችላለህ።ስለዚህ ቀላል ነው ማለት ነው

ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን

መሠረተ፡ግእዝ

@learnGeez1
@learnGeez1
@learnGeez1 👈
ግዕዝ ክፍል 17

✟ልሣነ ግእዝ፥ክፍል 17✟
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
፨፨ስለ ግሥ የመጨረሻው ክፍል፨፨
በነገራችን ላይ ግስን ካልተውነው አየተወንም ራሱን የቻለ እስከ 1000 ክፍልም ብንማር ብዙ መንገድ ስላለው ለመወሰን ያዳግታል።ቢሆንም ግን መሰረታዊ የሆነው ነገር እስካሁን ባሉት ክፍሎ አይተናል።
ሣልስ ቅጽል ቦዝ አንቀጽን አርእስት አንቀጹን ግን ስላላየን ስለ እነርሱ ጥቂት ብለን ነገረ ግሥን ብንደመድመው የተሻለ ነው።
✍️ቀተለ=ገደለ
ቀታሊ=የገደለ
ቀታልያን=የገደሉ
ቀታሊት=የገደለች
ቀታልያት=የገደሉ
...
ዴገነ ዴጋኒ ዴጋንያን ዴጋኒት ዴጋንያት
ክህለ ከሀሊ ከሀልያን ከሀሊት ከሀልያት
ጦመረ ጦማሪ ጦማርያን ጦማሪት ጦማርያት
...
.
እያለ ይሄዳል ትጉሙን በቀተለ አካሄድ ራሳችሁ ተርጉሙት አያቅትም።
ቦዝ አንቀጽ የሚባለው አመስግኖ ጽፎ ገድሎ.... ወዘተ ለማለት የሚረዳን ነው።ስለዚህም ቀቲሎ ቀዲሶ ተንቢሎ... እያለ ይሄዳል።
..
አርእስት አንቀጽ ገደለ ከሚለው መግደልን አመሰገነ ከሚለው ማመስገንን ለመነ ከሚለው መለመንን ...። ወዘተ ለማውጣት የእያንዳንዱን እንየው።
ቀተለ=ገደለ፥ቀቲል/ቀቲሎት=መግደም
ቀደሰ=አመሰገነ፥ቀድሶ/ቀድሶት=ማመስገን
ክህለ=ቻለ፥ክሂል/ክሂሎት=መቻል
ተንበለ=ለመነ፥ተንብሎ/ተንብሌት=መለመን
ጦመረ=ጻፈ፥ጦምሮ/ጦምሮት=መጻፍ
ገብረ=ሰራ፥ገቢር/ገቢሮት=መስራት
...
..
እያለ ይቀጥላል
ነገረ ግሥን ከዚህ እንቋጨውና ወደ ቀጣዩ 3 ክፍሎች ነገ እንጀምራለን።የነገ ሰው ይበለን
ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን።አሜን

መሠረተ፡ግእዝ
@learnGeez1
@learnGeez1
@learnGeez1 👈
ግዕዝ ክፍል 18

✟ልሣነ ግእዝ፥ክፍል 18✟
ይትባረክ እግዚአብሔር አምላከ እስራኤል ዘተሠሃለነ ወገብረ መድኃኒተ ለህዝበ ዚአሁ፦ለወገኖቹ መድኃኒትን ያደረገ ያባቶቻችን አምላክ ልዑል እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን

፨ባለቤት/subjec፤ተሳቢ/object፤ማሰሪያ አንቀጽ/Verb፨
ባለቤት የምንለው አረፍተ ነገሩ የሚናገርለት ሰው ወይም ነገር ነው።ይህም ማን ብለን ስንጠይቅ የምናገኘው መልስ ነው።ለምሳሌ እግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን ፈጠረ ብንል።ማን ፈጠረ?ብለን ስንጠይቅ እግዚአብሔር የሚል መልስ እናገኛለን።
✍️ተሳቢ/object ምን ማንን ምንን ብለን ስንጠይቅ የምናገኘው መልስ ነው።ለምሳሌ ከላይ ካለው ዓረፍተ ነገር እግዚአብሔር ሰማይና ምድርን ፈጠረ ስንል።ምንን ፈጠረ ስንል ሰማይንና ምድርን እንላለን ሰለዚህ ሰማይና ምድር ተሳቢ ይባላሉ።
በባለቤት ጊዜ ባለቤት በሚሆነው ቃል ላይ ም ዓይነት የፊደል ቅርጽ ለውጥ አይመጣም።ይህም ማለት እግዚአብሔር ያው እግዚአብሔር እንዳለ ነው።ተሳቢ ላይ ግን ለውጥ አለ።በግእዙ እግዚአብሔር ፈጠረ ሰማየ ወምድረ ነው የሚል።ስለዚህ ሲሳብ ምድር ወደ ምድረ ሰማይ ወደ ሰማየ ተለውጧል።አንድ ቃል ተሳቢ ሲሆን የሚያመጣውን የቅርጽ ለውጥ ቀጥለን እንመልከት።
1 በሳድስ የሚጨርስ ቃል ተሳቢ ሲሆን ወደ ሳድሱ ወደ ግእዝ ይቀየራል ከላይ እንዳየነው።ምድር የሚለው ምድረ... ሰማይ የሚለው ሰማየ እንዳለው
2 በካዕብ የሚጨርሱ ግሶች ተሳቢ ሲሆኑ ወደ ሳብእ ይቀየራሉ ይህም ማለት ቤቱ ይል የነበረው ቤቶ ይላል።እሙ ይል የነበረው እሞ ይላል።ቅዱስ ያሬድ እሞ ወላዲቶ ኪያሃ ረሰየ እንዲል።በዚህ አጋጣሚ በቀጣይ ክፍሎች ቅዱሳት መጻሕፍትን እንዴት መተርጎም እንደምንችል እናያለን
3 በሣልስ የሚጨርስ ግስ ሲሳብ ኃምስ ይሆናል።ለምሳሌ ቀዳሲ ይል የነበረው ቀዳሴ ይላል ማለት ነው።
4 በኃምስ በራብእ በሳብእ የሚጨርሱ ቃላት ሲሳቡ ባሉበት ይቀራሉ ይህም ማለት በራብእ ለምሳሌ ራማ የሚለው ሲሳብ ያው ራማ በኃምስ ውዳሴ የሚለው ሲሳብ ያው ውዳሴ መሰንቆ ሲሳብ ያው መሰንቆ ይላል
✍️ግሥ/verb ይህ ስለ ዓረፍተ ነገሩ ድርጊት ሁኔታ በደንብ የሚገልጽልን ነው።ይህም ማለት ከላይ ፈጠረ ያለው ነው።

ቀጣይ ክፍል በሰፊው እገልጻለሁ
ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን

መሠረተ፡ግእዝ

@learnGeez1
@learnGeez1
@learnGeez1 👈 #ሼር አድርጉ
ግዕዝ ክፍል 19

✟ልሣነ ግእዝ፥ክፍል 19✟
ይእዜኒ ለሰላም ንትልዋ መድኃኒነ ተወልደ ነዋ፦ከዛሬ ጀምሮ ፍቅርን ሰላምን እንያዝ መድኃኒታችን ተወልዷልና ይላል ቅዱስ ያሬድ
፨ከክፍል 18 የቀጠለ፨
የመጠሪያ ስሞች ሲሳቡ °ሃ° ፊደልን ይጨምራሉ... ማርያምን ውደድ ብትል ማርያምሃ ትላለህ ማለት ነው።ስለዚህ ጊዮርጊስ እግዚአብሔርን ለመነ ለማለት ብትፈልግ።ለመነ የተባለ ማን ነው?ስትል ጊዮርጊስ የሚል መልስ ታገኛለህ ስለዚህ ጊዮርጊስ የዓረፍተ ነገሩ ባለቤት ነው።ማንን ለመነ ስትል እግዚአብሔርን የሚል መልስ ታገኛለህ ስለዚህ እግዚአብሔር ተሳቢ ነው።ማሰሪያው ለመነ ነው።ስለዚህ ጊዮርጊስ ሰአለ እግዚአብሔርሃ፥ሰአለ እግዚአብሔርሃ ጊዮርጊስ፥እግዚአብሔርሃ ሰአለ ጊዮርጊስ ትላለህ ማለት ነው።አበበ እንጀራ በላ ቢልብህ ደግሞ አበበ ባለቤት እንጀራ ተሳቢ በላ ማሰሪያ አንቀጽ ስለሆነ አበበ በልአ ኅብስተ ወይም ኅብስተ በልአ አበበ ወይም አበበ ኅብስተ በልአ እያልክ መመስረት ትችላለህ ማለት ነው።
✍️ንኡስ አገባብ/Adverb ይህ ግስ ነው የሚያጎለምስ ለምሳሌ ፊላታኦስ ዛሬ መጣ ብትል ዛሬ ስለ መምጣቱ ተጨማሪ መረጃ ስለሚሰጥህ አንቀጽ አጎላማሽ ይባላል በቅኔ ቤት።ስለዚህ ፊላታኦስ መጽአ ይእዜ፥ይእዜ መጽአ ፊላታኦስ ይላል እንጂ ይእዜ ፊላታኦስ መጽአ አይባልም።በማሰሪያ አንቀጹ እና በግሱ መካከል ምንም መግባት የለበትምና።
✍️ቅጽል/Adjective ይህ ደግሞ ስምን ነው የሚያጎለምስ ለምሳሌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ጸለየ ብንል።ቅዱስ የሚለው ስለ ጊዮርጊ ተጨማሪ ነገር ስለሚነግረን ቅጽል ይባላል።ቅዱስ ጸለየ ጊዮርጊስ ግን አይልም በቅጽልና በባለቤት መካከል ምንም አይገባምና።ስለዚህ ቅዱስ ጊዮርጊስ ጸለየ፥ጸለየ ቅዱስ ጊዮርጊስ እያለ ነው የሚቀጥል።
ደቂቅ አገባብ/preposition እኒህ ደግሞ በስሞች ላይ እየወደቁ የሚያዛምዱ ናቸው ለምሳሌ ማርያም ሆይ ከሚካኤል ጋር ነይ ለማለት ንዒ ማርያም ምስለ ሚካኤል ይላል።ምስለ ከሚካኤል ላይ እንዳረፈ አስተውል።ስለዚህ ማንኛውም አረፍተ ነገር ከእነዚህ ሊወጣ አይችልም።በተወሰነ መልኩ በግርድፉም ቢሆን አይተናል።
ስለዚህ አሁን እስኪ አንድ ሙሉ አረፍተ ነገር ልስራ
ቅድስት ራሔል ከሰሎሜ ጋር ወደ ገነት ዛሬ ሄደች የሚለውን ልስራው።መጀመሪያ የአረፍተ ነገሩ ባለቤት ራሔል ናት ለራሔል የተቀጸለው ቅድስት የሚለው ነው።ጋር የሚለው በግእዝ ምስለ ነው።ገነት በግእዝ ኤዶም ነው እንዳለ ገነትም ይሆናል ወደ ኀበ ነው ዛሬ ዮም ነው ሄደ ሖረ ነው ለእርሷ ሲሆን ሖረት ይላል ስለዚህ
ቅድስት ራሔል ሖረት ዮም ኀበ ኤዶም ምስለ ሰሎሜ።ይላል ራሔል=subject,ምስለ ወደ=preposition ሔደ=verb,ዮም=Adverb። ቅድስት=Adjective እንደሆነ አስተውል ማንኛውም አረፍተ ነገር በዚህ መልኩ ይሄዳል ማለት ነው።ምናልባት ስለ አቢይ አገባብ ቀጣይ አቀርብ ይሆናል
..
ጥያቄ
ተርጉም
1 ወደ ሀገሬ ኢትዮጵያ ትላንት ሄድኩ(hint፣ትላንት=ትማልም)
2 ደጋግ ወንድሞቼ እና እህቶቼ ነገ ወደ መስቀል አደባባይ እንሄዳለን (hint፣ነገ ጌሰም፤አደባባይ አውድ፤ደጋግ ኄራን፣ እና ለማለት "ወ" ነው)
ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን

መሠረተ፡ግእዝ

@learnGeez1
@learnGeez1
@learnGeez1 👈
ግዕዝ ክፍል 20

✟ልሣነ ግዕዝ፥ክፍል 20✟
በቸርነቱ ብዛት እስካሁኑ ሰዓት ላደረሰን ለልዑል እግዚአብሔር ምስጋና ይገባል።
፨፨ማጠቃለያ፨፨

ባለጌ ነኝ የሚለው ቃል በድሮው ዘመን የሚያኮራ የሚያስጀንን ነበረ።አሁን ግን ይህ ያኔ ያኮራ የነበረው ቃል ለሌላ ሀሳብ ዋለና የሚያዋርድ ሆነ።ያን ጊዜ ያኮራ የነበረው ምን የሚል አረዳድ ስለነበረው ነው? ብለን ስንጠይቅ "ጌ" የምትለዋ ቃል "ምድር" ተብላ ትተረጎም ነበር ይላሉ(በምን ቋንቋ እንደሆነ ጌ ምድር ተብላ የተተረጎመች አላውቀውም) የሆነ ሆኖ ሐረርጌ ሲል የሐራር ምድር ጉራጌ ሲል የጉራዓ ምድር ተብሎ ይተረጎም ነበር።ስለዚህም ⁺ባለጌ⁺ ማለት ባለ መሬት ባለ ሀገር ባለ ምድር ማለት ስለነበረ ያኮራ ነበረ።አሁን ግን ይኽው ቃል ከመቼ እንደጀመረ ባላውቅም የውርደት ቃል እንደሆነ እናስተውላለን።ስለዚህ ቋንቋ በየዘመናቱ ሊሻሻል ይችላል።የግእዝ ቋንቋ በቅኔ በምሥጢር ተራቆ እንደነ ተዋነይ እስከ መሰወር ያደርሳል ይላሉ(ተዋነይ ተሰውሯል ይባላል) እንደነ ቅዱስ ያሬድ በተመስጦ ገነት ይወስዳል።ይህ የሚሆነው ግን ቋንቋን ለምስጋና ስንጠቀምበት እንጂ ለዋዛ ፈዛዛ ስንጠቀምበት አይደለም።

እንግዲህ እስካሁን ከክፍል 1 እስከ ክፍል 19 ተምረናል።ግእዝ ሰፊ ነው... እስከ ቅኔ ይደርሳል።ቋንቋን የማወቅ ጥቅሙ እግዚአብሔርን ለማመስገን ነው።በዚህ በግእዝ ቋንቋም አባቶቻችን በቅኔያቸው ትንቢት ተናግረዋ የተጣላ አስታርቀዋል መሥዋእት አሳርገውበታል።ጥልቅ እና ሰፊ ነው ቋንቋ ጠንቅቆ ቋንቋውን ለማወቅ እስከ 20 ዓመት ይፈጃል።እስካሁን የጻፍናቸው ግን እንደመግቢያ ይሆኑናል።መምህራንን በመጠየቅ መጻሕፍትን በማንበብ የግእዝ ቋንቋ ክሂሎታችንን ማሳደግ እንችላለን።ለመጨረሻ ክፍል ያሰብኩት ብዙ ጊዜ በቅዳሴም በሌላም በብዛት የሚባሉ አሉ።ቢያንስ እነርሱን ብናውቅ ነፍሳዊ ደስታ እናገኝባቸዋለን የሚል ተስፋ ስላለኝ ነው።
✍️እግዚኦ ተሠሃለነ=አቤቱ ይቅር በለን
✍️ሰአሊ ለነ ቅድስት=ቅድስት ሆይ ለምኝልን
✍️ተንሥኡ ለጸሎት=ለጸሎት ተነሱ
✍️ስግዱ ለእግዚአብሔር=ለእግዚአብሄር ስገዱ
....
...
ወዘተ ይህን የመሳሰሉ አሉ።

እውቀትን የሚገልጽ ቸሩ እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን አሜን።

መሠረተ፡ግእዝ

@learnGeez1
@learnGeez1
@learnGeez1 👈
የግእዝ ቋንቋን በነጻ ይማሩ
(ክፍል1፥)

በማንኛውም ቋንቋ ቃላት የሀሳብ የድርጊት የአካል የዓይነት የመልክ የአቋም እና የመሳሰሉት ነገሮች ውክልና ናቸው።ዛሬ የቀተለን ጓዝ እንይ።
1 ቀተለ=ገደለ=kill/killed
2 ይቀትል=ይገድላል=will kill
3 ይቅትል=ይገድል ዘንድ=to kill
4 ይቅትል=ይግደል=kill
5 ቀቲል/ቀቲሎት=መግደል=killing
6 ቀታሊ/ቅቱል/መቅትል=የገደለ=killer
7 ቀታልያን/ቅቱላን/መቅትላን=የገደሉ=killers
8 ቀታሊት/ቅትልት/መቅትልት=የገደለች=killer
9 ቀታልያት/ቅቱላት/መቅትላት=የገደሉ=killers
10 ቀትል=ጦርነት=War
ሌሎች የቀተለ ሠራዊቶች ሁሉ ቀተለን መስለው ይረባሉ።የቀተለ ቤት የሚባለው መጀመሪያው መካከለኛውና መጨረሻው ሦስቱም ግእዝ ሲሆን በሆሄያት ጥናት ሀ ግእዝ ሁ ካእብ ሂ ሣልስ ሃ ራብእ ሄ ኃምስ ህ ሳድስ ሆ ሳብእ ይባላሉ።የቀተለ ቤት ሁሉም ግእዝ ነው ማለት ቀ ግእዝ ተ ግእዝ ለ ግእዝ ነው እያልን ነው ማለት ነው።ይህ ቀተለ ለወደፊት /future ሲሆን በግእዝ ካልዓይ አንቀጽ ይባላል።ይኽውም ይቀትል ይላል።በዚህ ጊዜ "ይ"ን መጀመሪያ ይጨምርና "ቀ"ን ባለበት አድርጎ "ተ እና ለ" ግን ወደ ሳድስ "ት እና ል" እንደተቀየሩ አስተውል። ስለዚህ በካልዓይ አንቀጽ የመጀመርያውን ሆሄ "ቀ"ን ግእዝ አድርጎ ሌላውን ሳድስ ያደርጋል ማለት ነው።ይቅትል የሚለው ዘንድ አንቀጽ ይባላል "ይ"ን ጨምሮ ሁሉንም ሳድስ ማድረግ ነው።ሦስተኛ ይቅትል ትእዛዝ አንቀጽ ይባላል ከዘንድ አንቀጽ ጋር ተመሳሳይ ነው።

ቅቱል የሚለው በግእዝ ቋንቋ ውስጠ ዘ ይባላል ለአንድ ወንድ የገደለ ማለት ነው።ለሴት ደግሞ ቅትልት ይላል የገደለች ማለት ነው።በእንግሊዘኛ ሁለቱም killer ይላል ባለቤቱ ካልተገለጸ በእንግሊዘኛ አይታወቅም።ቅቱላን የሚለው ለብዙ ወንዶች ሲሆን ቅቱላት የሚለው ለብዙ ሴቶች ነው።

መቅትል መስተቅትል መስተቃትል አፈታቱ እንደ ቅቱል ነው።መቅትላን መስተቅትላን መስተቃትላን አፈታቱ እንደ ቅቱላን ነው።መቅትልት መስተቅትልት መስተቃትልት እንደ ቅትልት ነው።መቅትላት መስተቅትላት መስተቃትላት እንደ ቅቱላት ነው።ከዚያ ቀተልት የሚል መድበል ይወጣል።ቀተልት የሚፈታው እንደ ቅቱላትና እንደ ቅቱላን ነው።ቀትል የሚለው ዘመድ ዘር ይባላል።ዘመድ ዘር ባእድ ዘር ምእላድ ጥሬ ዘር የሚባሉት ከግሥ የሚወጡ ስሞች ናቸው።በእንግሊዘኛው add ከሚለው verb addition የሚል noun እንደሚወጣው ያለ ነው።ቀተለ ገደለ ከሚለው ቀትል ግድያ ጦርነት የሚል ስም ይወጠዋል።ቀቲል ቀቲሎት መግደል ወይም killing ነው ብለናል ይህ አርእስት አንቀጽ ይባላል Gerund ወይም infinitive ከሚባለው ጋር ይመሳሰል ይመስለኛል።
መልመጃ
ሶምሶን አንበሳ ገደለ የሚለውን በግእዝ ለመተርጎም።ሶምሶን ቀተለ አንበሳ ይላል በእንግሊዘኛ Somson kills a Lion ይላል። ይገድላል ስንል ሶምሶን ይቀትል አንበሳ Somson will kill a Lion ይላል።አንበሳ ግደል ለማለት ደግሞ kill a lion ይላል።ሶምሶን አንበሳ ይገድል ዘንድ ወደ ጫካ ሄደ የሚለው።ሶምሶን ሖረ ኀበ ደብር ይቅትል አንበሳ somson is going to Forrest to kill a lion ይላል።ገዳይ ለማለት Somson is a killer ቀታሊ ውእቱ ሶምሶን ይላል። እንግሊዘኛዋን ካበላሸሁ Dawit Muluneh ያስተካክለኝ።

የእለቱ ጥያቄ
ከላይ በሰራሁት መሰረት የሚከተሉትን ቃላት ስራ
1ኛ ነገደ=ሄደ=Go/went
2ኛ ከነፈ=በረረ=Fly
.
.
ወስብሀት ለእግዚአብሔር አሜን

መሠረተ፡ግእዝ

@learnGeez1
@learnGeez1
@learnGeez1 👈
የግእዝ ቋንቋ ክፍል 2
በክፍል 1 የቀተለን ዝርዝር አይተን ነበር ዛሬ የሌሎችን አርእስት እናያለን።
1 ቀደሰ=አመሰገነ
2 ይቄድስ=ያመሰግናል
3 ይቀድስ=ያመሰግን ዘንድ
4 ይቀድስ=ያመስግን
5 ቀድሶ/ሶት=ማመስገን
6 ቀዳሲ/ቅዱስ=የሚያመሰግን ወንድ
7 ቀዳስያን/ቅዱሳን=የሚያመሰግኑ ወንዶች
8 ቀዳሲት/ቅድስት=የምታመሰግን ሴት
9 ቀዳስያት/ቅዱሳት=የሚያመሰግኑ ሴቶች
10 መቀድስ/መስተቀድስ/መስተቃድስ=የሚያመሰግን
11 መቀድሳን/መስተቀድሳን/መስተቃድሳን=የሚያመሰግኑ
12 መቀድስት/መስተቀድስት/መስተቃድስት=የምታመሰግን
13 መቀድሳት/መስተቀድሳት/መስተቃድሳት=የሚያመሰግኑ
14 ቀደስት=የሚያመሰግኑ
15 መቅደስ=ማመስገኛ መመሰጋገኛ መመስገኛ ማመሰጋገኛ ማስመስገኛ
16 ቅዳሴ=ምስጋና
17 ቅድስና=ቅድስና
እያለ ይረባል የቀደሰ ቤት የሚባለው መካከለኛው ፊደል ጠብቆ የሚነበበው ነው።የቀደሰ ቤት ቀደሰን መስሎ ይረባል
1 ተንበለ=ለመነ
2 ይተነብል=ይለምናል
3 ይተንብል=ይለምን ዘንድ
4 ይተንብል=ይለምን
5 ተንብሎ/ተንብሎት=መለመን
6 ተንባሊ/ትንቡል=የለመነ
7 ተንባልያን/ትንቡላል=የለመኑ
8 ተንባሊት/ትንብልት=የለመነች
9 ተንባልያት/ትንቡላት=የለመኑ
10 መተንብል/መስተተንብል/መስተተናብል=የለመነ
11 መተንብላን/መስተተንብላን/መስተተናብላን=የለመኑ
12 መተንብልት/መስተተንብልት/መስተተናብልት=የለመነች
13 መተንብላት/መስተተንብላት/መስተተናብላት=የለመኑ
14 ተንበልት=የለመኑ
15 ትንባሌ=ልመና
የተንበለ ቤት የሚባለው ቅድመ መድረሻውን ሳድስ አድርጎ ሌላውን ግእዝ ያደረገ ሁሉ ነው። ተንበለ ከሚለው "ን" ቅድመ መድረሻ ሳድስ እንደሆነች አስተውል።
1 ባረከ=አመሰገነ
2 ይባርክ=ያመሰግናል
3 ይባርክ=ያመሰግን ዘንድ
4 ይባርክ=ያመስግን
5 ባርኮ/ባርኮት=ማመስገን
6 ባራኪ/ቡሩክ=ያመሰገነ
7 ባራክያን/ቡሩካን=ያመሰገኑ
8 ባራኪት/ቡርክት=ያመሰገነች
9 ባራክያት/ቡሩካት=ያመሰገኑ
10 መባርክ/መስተባርክ=ያመሰገነ
11 መባርካን/መስተባርካን=ያመሰገኑ
12 መባርክት/መስተባርክት=ያመሰገነች
13 መባርካት/መስተባርካት=ያመሰግኑ
14 ባረክት=ያመሰገኑ
15 በረከት=በረከት
16 ቡራኬ=ቡራኬ
የባረከ ቤት የሚባለው መነሻውን ራብእ ያደረገ ግስ ነው።ይህን የመሰለ ግስ እንደ ባረከ ይወርዳል ማለት ነው።
1 ጦመረ=ጻፈ
2 ይጦምር=ይጽፋል
3 ይጦምር=ይጽፍ ዘንድ
4 ይጦምር=ይጻፍ
5 ጦምሮ/ጦምሮት=መጻፍ
6 ጦማሪ/ጡሙር=የጻፈ
7 ጦማርያን/ጡሙራን=የጻፉ
8 ጦማሪት/ጡምርት=የጻፈች
9 ጦማርያት/ጡሙራት=የጻፉ
10 ጦመርት=የጻፉ
11 መጦምር/መስተጦምር/መስተጡዋምር=የጻፈ
12 መጦምራን/መስተጦምራን/መስተጡዋምራን=የጻፉ
13 መጦምርት/መስተጦምርት/መስተጡዋምርት=የጻፈች
14 መጦምራት/መስተጦምራት/መስተጠዋምራት=የጻፉ
15 ጦመርት=የጻፉ
16 ጦማር=ጽሑፍ/ደብዳቤ
የጦመረ ቤት ጦመረን መስሎ ነው የሚረባው መነሻው ሳብእ የሆነ ግስ የጦመረ ግስ ይባላል።
1 ገብረ=ሠራ
2 ይገብር=ይሠራል
3 ይግበር=ይሠራ ዘንድ
4 ይግበር=ይስራ
5 ገቢር/ገቢሮት=መስራት
6 ገባሪ/ግቡር=የሰራ
7 ገባርያን/ግቡራን=የሰሩ
8 ገባሪት/ግብርት=የሰራች
9 ገባርያት/ግቡራት=የሰሩ
10 ገበርት=የሰሩ
11 መግብር/መስተግብር/መስተጋብር=የሰራ
12 መግብራን/መስተግብራን/መስተጋብራን=የሰሩ
13 መግብርት/መስተግብርት/መስተጋብርት/የሰራች
14 መግብራት/መስተግብራት/መስተጋብራት=የሰሩ
15 ግብር=ሥራ
16 ተግባር/ምግባር=ሥራ
የገብረ ቤት የሚባል ሦስት ፊደል ሆኖ መካከሉ ሳድስ የሆነ ሲሆን የሚረባ ገብረን መስሎ ነው።

ጥያቄ
የሚከተሉትን ግስ አርባ
1 ናፈቀ (ባረከ)
2 ሠምረ (ገብረ)
3 ደመረ (ቀደሰ)

መሠረተ፡ግእዝ

@learnGeez1
@learnGeez1
@learnGeez1 👈
የግእዝ ቋንቋ ክፍል 3
ስምንቱን የግስ አርእስት ያወቀ ሰው ማንኛውም ግስ ቢመጣለት ዘርዝሮ መጻፍ ማንበብ መተርጎም ይችላል።በክፍል 1 ከስምንቱ አንዱ የሆነው ቀተለን በክፍል 2 ቀደሰ፥ተንበለ፣ባረከ፥ጦመረ እና ገብረን ጽፈናል።አሁን ቀሪዎቹን እንጽፋለን።ይህን ካወቀን የግእዝን መሰረታዊ ነገሮች አወቅን እንባላለን።
1 ቀዳማይ አንቀጽ=ክህለ=ቻለ
2 ካልዓይ አንቀጽ=ይክህል/ይክል=ይችላል
3 ሣልሳይ/ዘንድ አንቀጽ=ይክሀል=ይችል ዘንድ
4 ትእዛዝ አንቀጽ=ይክሀል=ይቻል
5 ንዑስ/አርእስት አንቀጽ=ክሂል/ክሂሎት=መቻል
ሣልስ ቅጽል/ውስጠዘ
6 ከሀሊ/ክሁል=የቻለ
7 ከሃልያን/ክህልት=የቻሉ
8 ከሀሊት/ክህልት=የቻለች
9 ከሃልያት/ክሁላት=የቻሉ
መስም ቅጽል
10 መክህል/መስተክህል/መስተካህል=የቻለ
11 መክህላን/መስተክህላን/መስተካህላን=የቻሉ
12 መክህልት/መስተክህልት/መስተካህልት=የቻለች
13 መክህላት/መስተክህላት/መስተካህላት=የቻሉ
መድበል
14 ከሀልት=የቻሉ
አስተውል ውስጠዘ እና መስም ውስጠ ዘ ተመሳሳይ ትርጉም ነው ያላቸው።መድበል ደግሞ እንደ ቅቱላን እንደ ቅቱላት እና ቁጥር 13 እና ቁጥር 11 እንዳሉት ይተረጎማል።ለብዙ ነው የሚሆን።
1 ቆመ=ቆመ
2 ይቀውም=ይቆማል
3 ይቁም=ይቆም ዘንድ
4 ይቁም=ይቁም
5 ቀዊም/ሞት=መቆም
6 ቀዋሚ/ቅውም=የቆመ
7 ቀዋምያን/ቅውማን=የቆሙ
8 ቀዋሚት/ቅውምት=የቆመች
9 ቀዋምያት/ቅውምት=የቆሙ
10 መቀውም/መስተቀውም/መስተቃውም=የቆመ
11 መቀውማን/መስተቀውማን/መስተቃውማን=የቆሙ
12 መቀውምት/መስተቀውምት/መስተቃውምት=የቆመች
13 መቀውማት/መስተቀውማት/መስተቃውማት=የቆሙ
14 ቀወምት=የቆሙ
15 ተቅዋም/ምቅዋም=መቆሚያ
16 ቁመት=አቋቋም/መቆም
17 ቆም=ቁመት
የቆመ ቤት እንደጦመረ ቤት በሳብዕ ይጀምራል ነገር ግን የቆመ ቤት የሚባለው 2 ፊደል ብቻ ያለውን ቃል ነው።ስለዚህ 2 ፊደል ሆኖ በሳብዕ የሚጀምር ቆመን መስሎ ይረባል ማለት ነው።
1 ሤመ=ሾመ
2 ይሠይም=ይሾማል
3 ይሢም=ይሾም ዘንድ
4 ይሢም=ይሹም
5 ሠይም/ሠይሞት=መሾም
6 ሠያሚ/ሥዩም=የሾመ
7 ሠያምያን/ሥዩማን=የሾሙ
8 ሠያሚት/ሥይምት=የሾመች
9 ሠያምያት/ሥዩማት=የሾሙ
10 መሠይም/መስተሠይም/መስተሣይም=የሾመ
11 መሠይማን/መስተሠይማን/መስተሣይማን=የሾሙ
12 መሠይምት/መስተሠይምት/መስተሣይምት=የሾመች
13 መሠይማት/መስተሣይምት/መስተሣይማት=የሾሙ
14 ሠየምት=የሾሙ
15 ሢመት=ሹመት
የሤመ ቤት የሚባለው ሁለት ፊደል ሆኖ በኃምስ ከጀመረ ነው።አረባቡም ይህን ይመስላል።
1 ዴገነ=ተከተለ
2 ይዴግን=ይከተላል
3 ይዴግን=ይከተል ዘንድ
4 ይዴግን=ይከተል
5 ዴግኖ/ዴግኖት=መከተል
6 ዴጋኒ/ዲጉን=የተከተለ
7 ዴጋንያን/ዲጉናን=የተከተሉ
8 ዴጋኒት/ዲግንት=የተከተለች
9 ዴጋንያት/ዲጉናት=የተከተሉ
10 መዴግን/መስተዴግን/መስተዲያግን=የተከተለ
11 መዴግናን/መስተዴግናን/መስተዲያግናን=የተከተሉ
12 መዴግንት/መስተዴግንት/መስተዲያግንት=የተከተለች
13 መዴግናት/መስተዴግናት/መስተዲያግናት=የተከተሉ
14 ዴገንት=የተከተሉ
የዴገነ ወይም የሴሰየ ቤት የሚባለው በኃምስ የሚጀምር ግስ ሁሉ ነው።2 ፊደል ከሆነ የሤመ ቤት ነው።ከ2 በላይ ሲሆን የዴገነ ቤት ስለሆነ ዴገነን መስሎ ይዘረዘራል።
1 ማህረከ=ማረከ
2 ይማሀ/ሃርክ=ይማርካል
3 ይማህርክ=ይማርክ ዘንድ
4 ይማህርክ=ይማርክ
5 ማህርኮ/ማህርኮት=መማረክ
6 ማህራኪ/ምህሩክ=የማረከ
7 ማህራክያን/ምህሩካን=የማረኩ
8 ማህራኪት/ምህርክት=የማረከች
9 ማህራክያት/ምህሩካት=የማረኩ
10 መማህርክ/መስተማህርክ/መስተማሀ/ሃርክ=የማረከ።
11 መማህርካን/መስተማህርካን/መስተማሀ/ሃርካን=የማረኩ
12 መማህርክት/መስተማህርክት/መስተማሀ/ሃርክት=የማረከች
13 መማህርካት/መስተማህርካት/መስተማሀ/ሃርካት=የማረኩ
14 ምህርካ=ምርኮ
ከባረከ የሚለየው ይህ ማህረከ 4 ፊደል ነው ባረከ 3 ፊደል ነው።ሁለቱም በራብእ ይጀምራሉ። ስለዚህ ሌላውን የግእዝ ግስ ሁሉ ክፍል 1 ክፍል 2 እና ክፍል 3 ያሉትን ከተረዳን።ሌላው ቃል እኒህን መስሎ ስለሚረባ ሁሉንም ማርባት እንችላለን ማለት ነው።

መሠረተ፡ግእዝ

@learnGeez1
@learnGeez1
@learnGeez1 👈
የግእዝ ቋንቋ ክፍል 4
መራሕያን (pronounce)
የግእዝ ቋንቋ 10 መራሕያን አሉት።መራሕያን ማለት መሪዎች
ማለት ነው።ለግእዝ ቋንቋ ዋና ነገሮች ናቸው።3 ዓይነት
አገልግሎት አላቸው።1ኛ የስም ምትክ ሆነው ሲያገለግሉ
1 ውእቱ=እርሱ=he
2 ውእቶሙ/እሙንቱ=እነርሱ=they
3 ውእቶን/እማንቱ=እነርሱ=they
4 ይእቲ=እርሷ=She
5 አንተ=አንተ=you
6 አንቲ=አንቺ=you
7 አንትሙ=እናንተ=you
8 አንትን=እናንተ=you
9 አነ=እኔ=I
10 ንሕነ=እኛ=We
በእንግሊዘኛ አንቺ አንተ እናንተ ስትል ተመሳሳይ youን
እንደተጠቀመ ስናይ።በግእዝ ግን ሴቶችን እናንተ ስንልና
ወንዶችን እናንተ ስንል እንኳ ልዩነት አለው።ወንዶችን አንትሙ
እንላለን ሴቶችን አንትን እንላለን።ወንዶችን እነርሱ ስንል
እሙንቱ ውእቶሙ ስንል ሴቶችን እነርሱ ስንል ግን ውእቶን
እማንቱ እንላለን።ከላይ ያለው ትርጉማቸው የስም ምትክ ሆነው
ሲያገለግሉ ሲሆን ብዙ ጊዜ ከማሰሪያ አንቀጽ በፊት ሲመጡ
የሚተረጎሙበት ነው።ቀጥለን ነባር አንቀጽ ሲሆኑ እንዴት
እንደሚተረጎሙ እንይ
1 ውእቱ=ነው፥ነበር፥አለ=Is,Was
2 ውእቶሙ=ናቸው፥ነበሩ፣አሉ=are,were
3 ይእቲ=ናት፥ነበረች፥አለች=is,was
4 ውእቶን=ናቸው፥ነበሩ፥አሉ=are,were
5 አንተ=ነህ፣ነበርክ፥አለህ=are,were
6 አንትሙ=ናችሁ፥ነበራችሁ፥አላችሁ=are,were
7 አንቲ=ነሽ፥ነበርሽ፥አለሽ=are,were
8 አንትን=ናችሁ፥ነበራችሁ፥አላችሁ=are,were
9 አነ=ነኝ፥ነበርኩ፥አለሁ=am,was
10 ንሕነ=ነን፥ነበርን፥አለን=are,were
ተብለው ይተረጎማሉ እንዲህ ተብለው ለመተርጎም ከማሰሪያ
አንቀጹ (verb) እና ከባለቤቱ በኋላ መምጣት
አለባቸው።ሦስተኛ አመልካች ቅጽል (Demonstrative
pronounce) ሆነው ሲያገለግሉ የሚኖራቸው ትርጉም
እንደሚከተለው ነው።
1 ውእቱ=ያ=that
2 ውእቶሙ=እነዚያ=those
3 ይእቲ=ያች=
4 ውእቶን=እነዚያ=those
5 አንተ=አንተ=you
6 አንቲ=አንቺ=you
7 አንትሙ=እናንተ=you
8 አንትን=እናንተ=you
9 አነ=እኔ=me
10 ንሕነ=እኛ=we
ይላል።መራሕያን አመልካች ቅጽል ሆነው ለማገልገል ከስም
በፊት መምጣት አለባቸው።ይህም ለምሳሌ ያ ቃል ሥጋ ሆነ ሲል
ውእቱ ቃል ሥጋ ኮነ ይላል ዮሐ.1፥14 ውእቱ ቃል ከሚለው ስም
በፊት ስለመጣ የሚተረጎም ያ ተብሎ ነው።ሌላው የስም ምትክ
ሆነው ሲያገለግሉ ከማሰሪያ አንቀጹ ይቀድማሉ ያልነው ምሳሌ
ይእቲ ተአቢ እምኪሩቤል ሲል እርሷ ከኪሩቤል ትበልጣለች
ማለት ነው።ይእቲ እርሷ ተብሎ የተተረጎመበት ምክንያት የስም
ምትክ ስለሆነ ነው።ነባር አንቀጽ (Auxiliary Verb) ሆነው
ሲያገለግሉ ምሳሌ ማርያም ይእቲ ሙዳየ መና ከሚለው ይእቲ
ማርያም ከሚለው ስም በኋላ ስለመጣ ትርጉም ናት ነበረች
የሚል ይሆናል።ሌላ ምሳሌ ቀዳሚሁ ቃል ውእቱ ሲል ውእቱ ቃል
ከሚለው ስም በኋላ ስለመጣ በመጀመሪያ ቃል ነበር ተብሎ
ይተረጎማል።

ከእነዚህ መራሕያን ነጠላ (Singulars) የሚባሉት
ውእቱ፥አነ፥ይእቲ፥አንተ፥አንቲ ሲሆኑ ብዙ (Plurals) የሚባሉት
ውእቶሙ/እሙንቱ፥ውእቶን/እማንቱ፥አንትሙ፥አንትን፥ንሕነ
ናቸው።በሴት እና በወንድ (Gerund) ሲከፈል ደግሞ
ውእቱ፥አንተ፥ውእቶሙ፥አንትሙ የወንድ (Masculine)
ሲሆኑ።አንቲ፥ይእቲ፥ውእቶን፥አንትን ደግሞ የሴት (Feminine)
ናቸው።አነ እና ንሕነ ጾታ አይለዩም ማለት ሴትም እኔ ትላለች
ወንድም እኔ ይላልና። በመደብ ሲከፈሉ ደግሞ አነ እና ንሕነ
አንደኛ መደብ (1st person) ሲባሉ አንተ፥አንቲ፥አንትሙ፥አን
ትን ደግሞ ሁለተኛ መደብ (2nd person) ሲሆኑ። ውእቱ፥ይእቲ፥ውእቶሙ፤ውእቶን ሦስተኛ መደብ (3rd person)
ይባላሉ።በቅኔ ቤት አንደኛ እና ሁለተኛ መደቦች ቅርብ ሲባሉ
ሦስተኛ መደብ ሩቅ ይባላል።

መሠረተ፡ግእዝ

@learnGeez1
@learnGeez1
@learnGeez1 👈
የግእዝ ቋንቋ ክፍል 5
ድርብ መራሕያንና ተሳቢ መራሕያን
1 ኪያሁ=እርሱን=him
2 ኪያሆሙ=እነርሱን=them
3 ኪያሃ=እርሷን=her
4 ኪያሆን=እነርሱን=them
5 ኪያከ=አንተን=you
6 ኪያክሙ=እናንተን=you
7 ኪያኪ=አንቺን=you
8 ኪያክን=እናንተን=you
9 ኪያየ=እኔን=me
10 ኪያነ=እኛን=us
ይላል እነዚህ ተሳቢ (object) መራሕያን ይባላሉ።በምሳሌ ለማየት አንተን እናመሰግናለን ለማለት ኪያከ ንሴብሕ ይላል።እርሱን ውደዱት ለማለት አፍቅርዎ ኪያሁ ይላል።ከዚህ በታች ያሉት ድርብ መራሕያን ናቸው።
1 ለሊሁ=እርሱ ራሱ=himself
2 ለሊሆሙ=እነርሱ ራሳቸው=themselves
3 ለሊሃ=እርሷ ራሷ=herself
4 ለሊሆን=እነርሱ ራሳቸው=themselves
5 ለሊከ=አንተ ራስህ=yourself
6 ለሊክሙ=እናንተ ራሳችሁ=yourselves
7 ለሊኪ=አንቺ ራስሽ=yourself
8 ለሊክን=እናንተ ራሳችሁ=yourselves
9 ለልየ=እኔ ራሴ=myself
10 ለሊነ=እኛ ራሳችን=ourselves
ይላል በምሳሌ ቅዱስ ዮሐንስ ስለጌታ ሲናገር ለልየ ርኢኩ እኔ ራሴ አየሁ ብሏል።ሌላ ምሳሌ ለሊከ ብከ ተከደንከ ብሎ አንተ ራስህ ተብሎ ይተረጎማል።አቤቱ አንተን እናመሰግንሀለን ስንልኮ ኪያከ እግዚኦ ነአኩት ነው የምንለው። ሌላው በዚህ ርእስ ልናየው ያሰብኩት አእማድ የሚባለውን ነው።
አእማድ
አእማድ የሚባሉ 5 ናቸው።እኒህም አድራጊ ተደራጊ ተደራራጊ አደራራጊ አስደራጊ ናቸው። ይህም ለምሳሌ ገደለ ብለን አስገደለ ተገዳደለ ለማለት አእማድን ማወቅ ይገባል።የቀተለን እንይ
ቀተለ=ገደለ
አቅተለ=አስገደለ
ተቃተለ=ተጋደለ
ተቀትለ=ተገደለ
አስተቃተለ=አገዳደለ
ይላል ስለዚህ ሌላው ግስም እንዲሁ አለው። በእርግጥ ለአንዳንድ ቃላት 5ቱ ላይኖራቸው ይችላል።2 ብቻ ያላቸውም ይኖራሉ።ለምሳሌ ሞተ ለሚለው ተሞተ አይባልም።ስለዚህ እንደአማርኛው እያየን ማድረግ እንችላለን ማለት ነው።

መሠረተ፡ግእዝ

@learnGeez1
@learnGeez1
@learnGeez1 👈
የግእዝ ቋንቋ ክፍል 6
የግስ ዝርዝር በ10ሩ መራሕያንን አሁን እንየው አንድን ግሥ በሴት በወንድ በአንድ በብዙ እንዴት መግለጽ እንደምንችል እንማማራለን።ይህም እርሱ መጣ እርሷ መጣች እነርሱ መጡ አንተ መጣህ እኔ መጣሁ እያልኩ የማበዛበት መንገድ ነው።
1ኛ በውእቱ/እርሱ ጊዜ ምንም የሚቀየር ፊደል የለም።ይህም ቀደሰ ብሎ አመሰገነ ይላል
2ኛ በውእቶሙ/እነርሱ ጊዜ የግሡን መጨረሻ ፊደል ካእብ ማድረግ ነው ይህም ቀደሱ/አመሰገኑ ይላል።
3ኛ በይእቲ/እርሷ ጊዜ መጨረሻ ላይ "ት"ን መጨመር ነው።ቀደሰት አመሰገነች ይላል።
4ኛ በውእቶን/እነርሱ ጊዜ የመጨረሻውን ፊደል ወደ ራብእ መቀየር ነው።ቀደሳ አመሰገኑ ይላል።
5ኛ በአንተ ጊዜ መድረሻውን ወደ ሳድስ ቀይሮ "ከ"ን መጨመር ነው።ቀደስከ አመሰገንክ ይላል
6ኛ በአንትሙ ጊዜ መድረሻውን ሳድስ አድርጎ "ክሙ"ን መጨመር ነው።ቀደስክሙ አመሰገናችሁ ይላል።
7ኛ በአንቲ ጊዜ መድረሻውን ሳድስ አድርጎ "ኪ"ን መጨመር ነው።ቀድስኪ አመሰገንሽ ይላል።
8ኛ በአንትን ጊዜ መድረሻውን ሳድስ አድርጎ "ክን"ን መጨመር ነው።ቀደስክን አመሰገናችሁ ይላል።
9ኛ በአነ ጊዜ መድረሻውን ሳድስ አድርጎ "ኩ"ን መጨመር ነው።ቀደስኩ አመሰገንኩ ይላል።
10ኛ በንሕነ ጊዜ መድረሻውን ሳድስ አድርጎ "ነ"ን መጨመር ነው።ቀደስነ አመሰገንን ይላል።
የተለየ አካሄድ ከሌላቸው ግሦች ውጭ ማንኛውም ግስ እንደዚህ ይረባል።የተለየ አካሄድ ያላቸው ግሦች እንኳ ከአንድ እስከ አራት በጠቀስነው ልዩነት የላቸውም።ልዩነት ያላቸው ከ5 እስከ 10 ባሉት አንደኛ እና ሁለተኛ መደቦች ነው።ስለዚህ ቀጥለን የምንመለከተው የሚለዩበትን ብቻ ነው።በአነባበብ ደረጃ የአንትን ዝርዝር ተጥሎ ይነበባል።ሌላው ተነስቶ ይነበባል።የተለየ አካሄፍ ያላቸውን ከዚህ ቀጥለን እንመለከታለን።
በ"ነ" የሚጨርሱ ግሦች ሁሉም እንደመጀመሪያው አካሄድ ሲረቡ በንሕነ ጊዜ ግን ለምሳሌ ወጠነ ጀመረ ብሎ ወጠንነ አይልም "ን" ተውጦ "ነ" ጠብቆ ይነበብና ወጠነ ይላል።ከውእቱ ወጠነ የሚለየው "ነ" ጠብቆ በመነበቡ ነው።
በ"ቀ፥ከ፥ገ" የሚጨርሱ ግሦች ደግሞ በአንተ፥አንቲ፣አንትሙ፥አንትን፥አነ ላይ "ክ"ን ውጠው እየጠበቁ ይነበባሉ።ይህም ለምሳሌ ሰበከ የሚለው ግሥ የመጨረሻው ፊደል "ከ" ስለሆነ በአነ ሰበክኩ ሳይል "ክ"ን ውጦ "ኩ" ጠብቆ ይነበብና ሰበኩ ይላል።አጥመቀ በሚለው አጥመቅኩ ሳይል "ኩ"ን ውጦ አጥመቁ ብሎ "ቁ" ጠብቆ ይነበባል። ኀደገ ተወ ከሚለውም ኀደግኩ ሳይል "ኩ"ን ውጦ ኀደጉ ብሎ "ጉ" ጠብቆ ይነበባል።ስለዚህ
አንተ=ሰበከ=አጥመቀ=ኀደገ
አንትሙ=ሰበክሙ=አጥመቅሙ=ኀደግሙ
አንቲ=ሰበኪ=አጥመቂ=ኀደጊ
አንትን=ሰበክን=አጥመቅን=ኀደግን
አነ=ሰበኩ=አጥመቁ=ኀደጉ ይላል
በሌሎች መራሕያን ግን ከመጀመርያው አካሄድ አይለዩም።
ሦስትና ከዚያ በላይ ፊደል ባለው በ "ሀ እና አ" በሚጨርስ ግስ ጊዜም በአነ፥ንሕነ፥አንተ፤አንትሙ፥አንትን፤አንቲ ጊዜ ቅድመ መድረሻውን ራብእ እያደረገ ይዘረዘራል።
አነ=መጻእኩ=መራሕኩ
ንሕነ=መጻእነ=መራሕነ
አንተ=መጻእከ=መራሕከ
አንትሙ=መጻእክሙ=መራሕክሙ
አንቲ=መጻእኪ=መራሕኪ
አንትን=መጻእክን መራሕክን ይላል።
አስተውል ይህ ሕግ ሦስትና ከዚያ በላይ ፊደል ባለው እንጂ ሁለት ፊደል ባላቸው ግሦች አይሰራም።በ"ሀ እና አ" የሚጨርስ 2 ፊደል ያለው ግሥ እንደመጀመርያው አካሄድ ይረባል።
የገብረ ቤቶችም በአነ፥ንሕነ፣አንተ፣አንትሙ፣አንቲ፥አንትን ጊዜ ቅድመ መድረሻቸውን ግእዝ አድርገው ይዘረዘራሉ።ይኽውም
አነ=ገበርኩ=ሠመርኩ
ንሕነ=ገበርነ=ሠመርነ
አንተ=ገበርከ=ሠመርከ
አንትሙ=ገበርክሙ=ሠመርክሙ
አንቲ=ገበርኪ=ሠመርኪ
አንትን=ገበርክን=ሠመርክን ይላል።
የክህለ ቤት ሆኖ በ"የ" የሚጨርስ ግስም በ1ኛና በ2ኛ መደቦች "የ"ን ጎርዶ ቅድመ መድረሻውን ሣልስ አድርጎ ይዘረዘራል።
ርእየን እንመንከት
አነ=ርኢኩ
ንሕነ=ርኢነ
አንተ=ርኢከ
አንትሙ=ርኢክሙ
አንቲ=ርኢኪ
አንትን=ርኢክን ይላል

ስለዚህ የግስ ዝርዝር ይህን ይመስላል።

መሠረተ፡ግእዝ
@learnGeez1
@learnGeez1
@learnGeez1 👈
የግእዝ ቋንቋ ክፍል 7
የስም ዝርዝር በመራሕያን።ይህ ደግሞ አንድን ስም ባለቤትነቱ የማን እንደሆነ የሚታወቅበት ነው።ይህም ማለት ምሳሌ ሀገሬ ሀገርሽ ሀገራችሁ እያልን በ10ሩ መራሕያን የምንገልጽበት ነው።3 አካሄዶች አሉት።
አንደኛ አካሄድ በሳድስ በሚጨርሱ ስሞች
1ኛ በውእቱ ጊዜ መድረሻውን ወደ ካዕብ መቀየር ነው።ሀገር ብሎ ሀገሩ ትርጉም ሀገሩ ይላል።
2ኛ በይእቲ ጊዜ መድረሻውን ራብዕ ያደርጋል ሀገራ ብሎ ትርጉም ሀገሯ ይላል
3ኛ በውእቶሙ ጊዜ መድረሻውን ሳብእ አድርጎ "ሙ"ን ይጨምራል ሀገሮሙ=ሀገራቸው ይላል።
4ኛ በውእቶን ጊዜ መድረሻውን ሳብእ አድርጎ "ን"ን ይጨምራል።ሀገሮን=ሀገራቸው ይላል።
5ኛ በአንተ ጊዜ "ከ"ን በአንትሙ ጊዜ "ክሙ"ን በአንቲ ጊዜ "ኪ"ን በንሕነ ጊዜ "ነ"ን በአንትን ጊዜ "ክን"ን በአነ ጊዜ "የ"ን መጨመር ነው።
አነ=ሀገርየ=ሀገሬ
ንሕነ=ሀገርነ=ሀገራችን
አንቲ=ሀገርኪ=ሀገርሽ
አንትሙ=ሀገርክሙ=ሀገራችሁ
አንትን=ሀገርክን=ሀገራችሁ
አንተ=ሀገርከ=ሀገርህ
ይላል ማለት ነው።
ሁለተኛ አካሄድ ከሳድስ ውጭ በሚጨርሱ ስሞች
1ኛ በውእቱ ጊዜ "ሁ"ን መጨመር ነው። መሰንቆሁ=መሰንቆው
2ኛ በውእቶሙ ጊዜ "ሆሙ"ን መጨመር ነው።መሰንቆሆሙ=መሰንቋቸው
3ኛ በውእቶን ጊዜ "ሆን"ን መጨመር ነው።መሰንቆሆን=መስንቋቸው
4ኛ በይእቲ ጊዜ "ሃ"ን መጨመር ነው።መሰንቆሃ=መሰንቆዋ ይላል
5ኛ በአንተ፥አንቲ፥አንትሙ፥አንትን፣አነ፥ንሕነ ጊዜ እንደ መጀመሪያው አካሄድ ነው ምንም ልዩነት የለውም።
የውእቱ የይእቲ እርባታ ተጥሎ የውእቶን የአንትን እርባታ ወድቆ ይነበባል።የሌሎቹ ግን ተነስቶ ይነበባል።

የስም ዝርዝር ከምሉ በጥቂቱ ይህን ይመስላል። የነገ ሰው ይበለን

ነሐሴ 11/2013 ዓ.ም

መሠረተ፡ግእዝ

@learnGeez1
@learnGeez1
@learnGeez1 👈
ቦዝ አንቀጽ ክፍል 8
በቅኔ ቤት ቸልታ ይባላል።በአማርኛ ሰርቶ አሠርቶ ተሠርቶ በልቶ እያለ የሚሄደው ነው። ለምሳሌ ሶምሶን አንበሳ ገድሎ ወደ ቤተሰቡ ሄደ ቢል ገድሎ የሚለው ቦዝ አንቀጽ ይባላል።በእንግሊዘኛ Having killed a lion,Somson went to his family ይላል።having+vp ነው።ስለዚህ ይህ ቦዝ በአስሩ መራሕያን ይወርዳል።
1 ውእቱ=ቀቲሎ=ገድሎ
2 ውእቶሙ=ቀቲሎሙ=ገድለው
3 ይእቲ=ቀቲላ=ገድላ
4 ውእቶን=ቀቲሎን=ገድለው
5 አንተ=ቀቲለከ=ገድለህ
6 አንትሙ=ቀቲለክሙ=ገድላችሁ
7 አንቲ=ቀቲለኪ=ገድለሽ
8 አንትን=ቀቲለክን=ገድላችሁ
9 አነ=ቀቲልየ=ገድየ
10 ንሕነ=ቀቲለነ=ገድለን
ይላል።ሌላው ግሥ ሁሉ ይህን መስሎ ይሄዳል።በእርግጥ የተለየ አካሄድ ያላቸው ጥቂት ግሦች አሉ።ነገር ግን የግሡ 95% እንደላይኛው ስለሚሄድ ለጊዜው የተጻፈውን ብቻ መያዙ ይሻላል።ይህ በአምስቱ አእማድም ይዘረዘራል ይህም ማለት ገድሎ አስገድሎ ወዘተ እያለ ይረባል።
ቀቲሎ=ገድሎ
አቅቲሎ=አስገድሎ
ተቀቲሎ=ተገድሎ
ተቃቲሎ=ተገዳድሎ
አስተቃቲሎ=አገዳድሎ
እያለ ይሄዳል።እኒህም እያንዳንዳቸው በ10ሩ መራሕያን ይዘረዘራሉ።

ምሳሌ
መዊቶ አድኃነነ ሲል ሞቶ አዳነን ማለት ነው።

ጥያቄ
የሚከተሉትን ቃላት አማረኛውን ወደ ግእዝ ግእዙን ወደ አማርኛ ቀይር
1ኛ አግኝቶ አጣ (hint ረከበ=አገኘ፥ኀጥአ=አጣ)
2ኛ ተሰቅሎ አዳነን (hint ተሰቅለ=ተሰቀለ)
3ኛ አገዳድላ ሸሸች (አስተቃተለ=አገዳደለ፤ጎየት=ሸሸች)
4ኛ ተኀጺቦ ጽቡር (ጽቡር=ጭካ፥ተኀጽበ=ታጠበ)
5ኛ ቀዲሶ በልአ

መሠረተ፡ግእዝ

@learnGeez1
@learnGeez1
@learnGeez1 👈
የግእዝ ቋንቋ ክፍል 9
የግእዝ መጠይቃን ቃላት
የአንድን ነገር ምንነት ማንነት መቼነት የትነት እንዴትነት እና ስንትነት ወዘተ በጥልቀት ለማወቅ የምንጠቀማቸው ቃላት ናቸው።
1 አይቴ=የት=Where
2 ማእዜ=መች/ቼ=When
3 ምንት=ምን=What
4 እፎ=እንዴት=how
5 ስፍን/እስፍንቱ=ስንት=how money
6 ለምንት=ለምን=why
7 መኑ=ማን=who
እኒህን የመሰሉ ቃላት በቅኔ ቤት ንዑስ አገባቦች ናቸው።በሙያቸው ደግሞ አንቀጽ አጎላማሽ (adverb) ናቸው።
እንዴት አደርክ ለማለት እፎ ኀደርከ
እንዴት ዋላችሁ ለማለት እፎ ወአልክሙ ይላል።

ማእዜ ትመጽእ ሲል መቼ ትመጣለህ? ማለት ነው።አይቴ ሀገርከ ሀገርህ የት ነው ይላል። እስኪ እኒህን ከዚህ ቀጥሎ ባለው ንግግር ወይም Conversation እንየው።ኤዶምና ያሬድ በአጋጣሚ ይጠያየቃሉ።ኤዶም ተወልዳ ያደገችው ባህርዳር ሲሆን ያሬድ ደግሞ አክሱም ነው።
ኤዶም፦እፎ ከረምከ
እንዴት ከረምክ?
ያሬድ፦እግዚአብሔር ይሰባሕ
እግዚአብሔር ይመስገን
ኤዶም፦መኑ ስምከ
ስምህ ማን ይባላል
ያሬድ=አነ ውእቱ ያሬድ፡ወመኑ ስምኪ
እኔ ያሬድ ነኝ።የአንችስ ስም ማን ነው?
ኤዶም፦አይቴ ሙላድከ ወማእዜ መጻእከ
የትውልድ ቦታህ የት ነው?መቼ መጣህ
ያሬድ፦ብሔረ አክሱም ሙላደ ያሬድ ማህሌታይ ውእቱ።ትማልም መጻእኩ
የተወለድኩት ማህሌታይ ያሬድ ከተወለደበት አክሱም ሲሆን ትላንት ነው የመጣሁት።
ኤዶም፦እፎ ርኢካ ለባህርዳር
ባህርዳርን እንዴት አየሀት
ያሬድ፦ሠናይት ይእቲ
ደስ ትላለች
ኤዶም፦ለምንት መጻእከ ዝየ
ከዚህ ለምን መጣህ
ያሬድ፦ከመ እትባረክ እምቅዱሳት ገዳማት ክብራን ገብርኤል ወዳጋ እስጢፋኖስ።
ከቅዱሳት መካናት ከክብራን ገብርኤል ከዳጋ እስጢፋኖስ እባረክ ዘንድ መጣህ።
ኤዶም፦ሠናይ ምጽአትከ ኦ እኁየ
ወንድሜ አመጣጥህ መልካም ነው
ያሬድ፦ኦ እኅትየ ኤዶም ምንት ትርጓሜሁ ለጣና እስኩ ንግርኒ።ወእስፍንቱ ገዳማት ሀለው በውስጠ ጣና።
እህቴ ኤዶም እስኪ ንገሪኝ የጣና ትርጓሜ ምንድን ነው?በውስጡስ ምን ያህል ገዳማት አሉ?
ኤዶም፦በከመ ነገረኒ መምህረ ቅኔ ዘዋሸራ ጣና ብሂል ጸአና ብሂል።አመ ትመጽእ እግዝእትነ ማርያም ምስለ ወልዳ ኀበ ዛ ሀገር ተጽኢና በደመና ይቤሉ ሕዝብ ጸአና በደመና።ወእምዝ እምብዝኅ መዋእል ጸአና ተወለጠ ኀበ ጣና። የዋሸራው የቅኔ መምህር እንደነገረኝ ጣና ማለት ጸአና ማለት ነው።እመቤታችን ማርያም ከልጇ ጋር በደመና ተጭና በመጣች ጊዜ ህዝቡ ጸአና ሲል ይህ በዘመን ብዛት ጣና ተባለ።
ያሬድ፦እግዚአብሔር የሀበኒ ተፈሣሕኩ እስመ አእመርኩኪ።
እግዚአብሔር ይስጥልኝ ስላወቅኩሽ ደስ ብሎኛል

ሳስበው ሳስበው የኤዶምና የያሬድ ንግግር ያልቅ አይመስለኝም።እናቋርጠው።

የእለቱ ጥያቄዎች
ግእዙን ወደ አማርኛ አማርኛውን ወደ ግእዝ ተርጉም።

1ኛ ማእዜ ንበልእ (ንበልእ=እንበላለን)
2ኛ ሰው ምንድን ነው? (ሰብእ=ሰው)
3ኛ ከመንፈስህ ወዴት እሄዳለሁ
4ኛ ለምን ተወለድን? (ተወለድነ=ተወለድን)

መሠረተ፡ግእዝ
@learnGeez1
@learnGeez1
@learnGeez1 👈
የግእዝ ቋንቋ ክፍል 10
አገባብ ክፍል 1
አገባብ ደቂቅ አገባብ ዐቢይ አገባብ ንኡስ አገባብ ተብሎ ይከፈላል።ከዚህ በጥቂቱ ደቂቅ አገባብን እንመልከት።
1 ዲበ፥መልእልተ፥ላእለ=በ....ላይ (on)
2 ውስተ=በ....ውስጥ (in)
3 ማእከለ=በ...መካከል (between)
4 ቅድመ=በ....ፊት (before)
5 ድኅረ=በ....ኋላ (after)
6 ምስለ=ከ....ጋራ (with)
7 ታሕተ=በ....ታች (under)
8 በ=በ
9 ለ=ለ (to)
10 እምነ=ከ (from)
11 እስከ=እስከ (until)
12 ኀበ፥መንገለ=ወደ (to)
13 ወ=እና (and)
14 እንበለ=በስተቀር (unless)
15 ከመ=እንደ (like)
16 በእንተ=ስለ
እንግዲህ እነዚህን በዓረፍተ ነገር እንዴት እንደምንጠቀም እንመልከት።
ምሳሌ 1 ምስለ ፍቁር ወልዳ=ከተወደደው ልጇ ጋር
ምሳሌ 2 ናጥሪ የዋሀተ ከመ ሐዋርያት= እንደሐዋርያት የዋሀትን ገንዘብ እናድርግ።
ምሳሌ 3 ንሰግድ ቅድመ እግዚአብሔር= በእግዚአብሔር ፊት እንሰግዳለን
ምሳሌ 4 መጽአ ድኅረ ነቢያት=ከነቢያት በኋላ መጣ
ምሳሌ 5 ተሰቅለ መልእልተ መስቀል በመስቀል ላይ ተሰቀለ
ምሳሌ 6 እምነ ጎጃም ኀበ ላሊበላ=ከጎጃም ወደ ላሊበላ
ምሳሌ 7 ፍቅር እስከ መቃብር=ፍቅር እስከ መቃብር።
ምሳሌ 8 ንገኒ ለእግዚአብሔር= ለእግዚአብሔር እንገዛለን።
ምሳሌ 9 ያስተጋብአነ በደብረ ጽዮን= በደብረ ጽዮን ይሰብስበን
ምሳሌ 10 በእንተ ጊዮርጊስ መሐረነ ክርስቶስ ስለ ጊዮርጊስ ብለህ ክርስቶስ ሆይ ማረን ይላል።

እንዲህ እንዲህ እያላችሁ በራሳችሁ ተለማመዱ።

ጥያቄ
ግእዙን ወደ አማርኛ አማርኛውን ወደ ግእዝ ተርጉም።
1 ወደ ግሼን ማርያም ሄደ (ሄደ=ሖረ)
2 ከረኀብ ጦር ይሻላል (ይሻላል ይሄይስ)
3 ሰላም ለኩልክሙ
4 ምስለ መንፈስከ
5 አፈቅራ እምልብየ


መሠረተ፡ግእዝ
@learnGeez1
@learnGeez1
@learnGeez1 👈
የግእዝ ቋንቋ ክፍል 11
አገባብ ክፍል 2
ዐበይት አገባቦች የሚባሉት ማሰሪያ የሚያስለቅቁ ናቸው።
1 አመ፣ሶበ፣ጊዜ=በ...ጊዜ
2 ዘ፥እንተ፥እለ=የ
3 እስመ፥አምጣነ፥አኮኑ=ና
4 እንዘ=ሲ፥ሳ፥እየ
5 ባሕቱ፥ዳእሙ=ነገር ግን
6 አላ=እንጂ
በዓረፍተ ነገር ስንመለከታቸው ግልጽ እንዲሆኑልን።ጌታ በተሰቀለ ጊዜ ፀሐይ ጨለመ የሚለውን ወደ ግእዝ ለመለወጥ አመ ተሰቅለ እግዚእነ ፀሐይ ጸልመ።በተሰቀለ ጊዜ ያሰኘው አመ ተሰቅለ ስላለ ነው።

ዘ የ ነው ያልነው ደግሞ ክርስቶስ ውእቱ ዘመጽአ ውስተ ዓለም።ወደ ዓለም የመጣ ክርስቶስ ነው።የመጣ ያለው ዘመጽአ እንደሆነ አስተውል።

አላ አድኅነነ=አድነን እንጂ ይላል እንጂ ያሰኘው አላ እንደሆነ አስተውል።

እየሳቁ ሞቱ የሚለውን ወደ ግእዝ ለመቀየር እንዘ ይስሕቁ ሞቱ ይላል።እየሳቁ ከሚለው እየን ያመጣው እንዘ መሆኑ አስተውል።

መኖርን እንወዳለን ግን ሞት አለ የሚለውን ወደ ግእዝ ቋንቋ ለመለወጥ ናፈቅር ሀልዎ ዳእሙ ሞት ሀሎ ይላል።ግን የሚለውን ያመጣው ዳእሙ ነው።

እለ የ ሲሆን ለብዙዎች ነው።እንተ ለሴት ሲሆን ዘ ለሁሉም ይሆናል።እለሞቱ በፍቅር ሲል በፍቅር የሞቱ ማለት ነው።የሞቱ ሲል የን ያመጣው እለ ነው።ሙሴ እንተርእየ ሲል ሙሴ ያያት ይላል ያያት ሲል የን ያመጣው እንተ ነው።

ወዶኛልና አዳነኝ ስንል በግእዝ እስመ አፍቀረኒ አድኃነኒ እንላለለ።ወዶኛልና ስንል ናን በግእዝ እስመ እንላታለን።

ጥያቄ
ግእዙን ወደ አማርኛ አማርኛውን ወደ ግእዝ ቀይር
1 እለትነብሩ ተንስኡ
2 ማርያም እንተናፈቅራ
3 እያነቡ እስክስታ (አንብዐ=አነባ፥ ዘፈን=እስክስታ)
4 አላ ንዒ ሊተ
5 ንፈቅድ ሀብተ ዳእሙ ኢተክህለነ

መሠረተ፡ግእዝ
@learnGeez1
@learnGeez1
@learnGeez1 👈
የግእዝ ቋንቋ ክፍል 12
የግእዝ ቁጥር
በነገራችን ላይ የራሱ የሆነ ቁጥር አለው ለዚህም 20 መስራች ቁጥሮች አሉ።20ው መስራች ቁጥሮች ከታወቁ ሌላውን በቀላሉ ማወቅ እንችላለን።
1=፩=አሐዱ=one
2=፪=ክልኤቱ=two
3=፫=ሠለስቱ=three
4=፬=አርባእቱ=four
5=፭=ኀምስቱ=five
6=፮=ስድስቱ=six
7=፯=ሰብዓቱ=seven
8=፰=ሰመንቱ=eight
9=፱=ተስዓቱ=nine
10=፲=አሠርቱ=ten
20=፳=እሥራ=twenty
30=፴=ሠላሳ=thirty
40=፵=አርብዓ=forty
50=፶=ኀምሳ=fifty
60=፷=ስድሳ/ስሳ=sixty
70=፸=ሰብዓ=seventy
80=፹=ሰማንያ=eighty
90=፺=ተስዓ=ninety
100=፻=ምእት=hundred
1000=፲፻=አሠርቱ ምእት=thousand
10000=፼=እልፍ=አሥር ሺ
100000=፲፼=አእላፍ=መቶ ሺ
1000000=፻፼=አእላፋት=ሚልየን
10000000=፲፻፼=ትእልፊት=አሥር ሚልየን
100000000=፼፼=ትእልፊታት=መቶ ሚልየን
1000000000=፲፼፼=ምእልፊት=ቢልየን
10000000000=፻፼፼=ምእልፊታት=አስር ቢልየን
እኒህን ቁጥሮች ከያዝን በኋላ ማንኛውንም ቁጥር በግእዝ መጻፍ ማንበብ ማወቅ እንችላለን።
ከ1 እስከ 100 ያለ
79 በግእዝ ሲጻፍ 70+9=፸+፱=፸፱ ይላል ሲነበብ ሰብዓ ወተስዓቱ ይላል።
ከ100-10000 ያለ
246 በግእዝ ሲጻፍ 2×100+40+6= ፪×፻+፵+፮=፪፻፵፮ ይላል ሲነበብ ክልኤቱ ምእት አርብዓ ወስድስቱ ይላል።
5298 በግእዝ ሲጻፍ= 50×100+2×100+90+9=፶×፻+፪×፻+፺+፰= ፶፻፪፻፺፰ ይላል ሲነበብ ኃምሳ ምእት ወክልኤቱ ምእት ተስዓ ወተስዓቱ ይላል።
ከ10000 በላይ ላለ ቁጥር
ለምሳሌ 144000 ሕጻናት በሄሮድስ ተገደሉ።
14×10000+40×100=፲፬×፼+፵×፻=፲፬፼፵፻ አሠርቱ ወአርባእቱ እልፍ ወአርብዓ ምእት ይላል ማለት ነው።ስለዚህ እንዲህ እንዲህ እያደረግን እስከምንፈልገው መቁጠር እንችላለን

ጥያቄ
የሚከተሉትን ቁጥሮች ወደ ግእዝ ቀይር
1, 2013 ዓ.ም
2, 7513 ዓ.ዓ
3, 5500
4, 94828
5,47294959
ቁጥሩን ከእነ ስሙ አስቀምጡት

መሠረተ፡ግእዝ
@learnGeez1
@learnGeez1
@learnGeez1 👈
የግእዝ ቋንቋ ክፍል 13
ስለፊደል።በግእዝ ቋንቋ እያንዳንዱ ፊደላት የወከሉት ሀሳብ አለ።ሥላሴና ሥጋዌን ያስረዳሉ
ሀ=ሀልዎቱ ለአብ እምቅድመ ዓለም
ሁ=ኪያሁ ተወከሉ=በእርሱ(ጌታ) ታመኑ
ሂ=አስተይዎ ብሂዐ=እርሾ (ጌታን) አጠጡት
ሃ=ሃሌ ሉያ=ቅድመ ዓለም ያለ የሚኖር
ሄ=በኩለሄ ሀሎ=በሁሉ ቦታ አለ (ጌታ)
ህ=ህልው እግዚአብሔር=እግዚአብሔር አለ
ሆ=ኦሆ ይቤ ወመጽአ=እሽ ብሎ መጣ
ሐ=ሐመ ወሞተ በእንቲአነ=ስለእኛ ታሞ ሞተ
ሑ=ሰብሑ ለስመ እግዚአብሔር=እግዚአብሔርን አመስግኑ
ሒ=መንጽሒ (የሚያነጻ እግዚአብሔር )
ሓ=መፍቀሬ ንስሓ=ንስሓን የሚወድ
ሔ=ሔት=እግዚአብሔር ሕያው ነው።
ሕ=ሕያው እግዚአብሔር
ሖ=ንሴብሖ ለእግዚአብሔር=እግዚአብሔርን እናመስግነው።
ኀ=ኀብአ ርእሶ=ራሱን ሰወረ
ኁ=እኁዝ አቅርንቲሁ
ኂ=ዘልማዱ ኂሩት=ቸርነት ልማዱ
ኃ=ኃያል በኃይሉ
ኄ=ኄር እግዚአብሔር=ቸር እግዚአብሔር
ኅ=ኅብስት ለርኁባን=ለተራቡት ምግብ
ኆ=ኆኅተ ገነት=የገነት ደጃፍ
ለ=ለብሰ ሥጋ ዚአነ=የእኛን ሥጋ ተዋሐደ
ሉ=ሣህሉ ለእግዚአብሔር=የእግዚአብሔር ቸርነቱ።
ሊ=ከሀሊ እግዚአብሔር=ሁሉን ቻይ እግዚአብሔር።
ላ=ላሜድ=ልኡል እግዚአብሔር
ሌ=መቅለሌ እጹብ=ጭንቀትን የሚያቀል
ል=መስቀል ዘወልደ አብ=የጌታ መስቀል
ሎ=ዘሀሎ እምቅድም=አስቀድሞ ያለ
መ=መንክር ግብሩ ለእግዚአብሔር= የእግዚአብሔር ስራው ድንቅ ነው።
ሙ=ሙጻአ ሕግ
ሚ=ዓለመ ኀታሚ=ዓለምን የሚያሳልፍ
ማ=ፌማ=መንፈስ ቅዱስ
ሜ=ሜም=ምኡዝ እግዚአብሔር
ም=አምላከ ሰላም=የሰላም አምላክ
ሞ=ሞተ በሥጋ=በሥጋ ሞተ
ሰ=ሰብአ ኮነ ከማነ=እንደ እኛ ሰው ሆነ
ሱ=ፋሲልያሱ
ሲ=ዘይሴሲ ለኩሉ ዘሥጋ=ፍጥረትን ሁሉ የሚመግብ
ሳ=ሳምኬት=ስቡሕ እግዚአብሔር
ሴ=ለባሴ ሥጋ=ሥጋን የተዋሐደ
ስ=ልብስ ለዕሩቃን=ለታራቆቱት ልብስ
ሶ=መርሶ ለአሕማር=የመርከቦች ወደብ
ሠ=ሠረቀ በሥጋ እምድንግል=ከድንግል በሥጋ ተወለደ
ሡ=መንበረ ንግሡ=የንግሥናው ዙፋን
ሢ=ሢመተ መላእክት=የመላእክት መሾም
ሣ=ሣህል ወርትእ=ምሕረትና ቅንነት
ሤ=ሤሞሙ ለካህናት=ካህናት ሾማቸው
ሥ=ንጉሥ እግዚአብሔር
ሦ=አንገሦ ለአዳም=አዳምን አነገሠው
ረ=ረግዐ ሰማይ ወምድር በጥበቡ=ሰማይና ምድር በጥበቡ ረጋ።
ሩ=በኩሩ ለአብ=የአብ በኩር
ሪ=ዘይሰሪ አበሳ=በደልን ይቅር የሚል
ራ=ጌራ መድኃኒት=የመድኃኒት ቦርቦርቴ
ሬ=ሬስ=ርኡስ እግዚአብሔር
ር=ርግብ መንፈስ ቅዱስ
ሮ=ፈጠሮ ለዓለም=ዓለምን ፈጠረው
ቀ=ቀዳሚሁ ቃል ውእቱ=በመጀመሪያ ቃል ነበር
ቁ=ጽድቁ ለኃጥእ
ቂ=ፈራቂሁ ለዓለም
ቃ=ቃልየ አጽምእ=ቃሌን ስማኝ
ቄ=ሰዋቄ ኃጥአን
ቅ=ጻድቅ እግዚአብሔር
ቆ=ቆፍ=ቅሩብ እግዚአብሔር
በ=በትሕትናሁ ወረደ ለቤዛ ኩሉ ዓለም=ዓለምን ለማዳን በትሕትናው ወረደ/ሰው ሆነ
ቡ=ጥበቡ ለአብ=የአብ ጥበቡ
ቢ=ረቢ ነአምን ብከ=ጌታ ሆይ በአንተ እናምናለን
ባ=ባዕድ እም አማልንተ ሐሰት=ከሐሰት አማልክት የተለየ
ቤ=ቤት=ባዕል እግዚአብሔር
ብ=ብርሃነ ቅዱሳን ፍጹማን=የቅዱሳን ብርሃን
ቦ=አልቦ ባእድ አምላክ ዘእንበሌሁ=ከእርሱ በቀር ሌላ አምላክ የለም።
ተ=ተሰብአ ወተሰገወ እማርያም እምቅድስት ድንግል=ከድንግል ማርያም ፍጹም ሰው ሆነ።
ቱ=መዝራእቱ ለአቡ=የአብ ክንዱ
ቲ=ተአኳቲ እግዚአብሔር=ተመስጋኝ እግዚአብሔር።
ታ=ታው=ትጉህ እግዚአብሔር
ቴ=ከሣቴ ብርሃን=ብርሃንን የሚገልጽ
ት=ትፍሥሕት ወሐሴት=ፍጹም ደስታ
ቶ=ነአምን ልደቶ ለክርስቶስ=የክርስቶስን ልደት እናምናለን
ነ=ነሥአ ደዌነ ወጾረ ሕማመነ
ኑ=ዛኅኑ ለባሕር=የባሕር ጸጥታው
ኒ=ኮናኒ እግዚአብሔር=ፈራጅ እግዚአብሔር
ና=መና እስራኤል=የእስራኤል መና
ኔ=መድኃኔዓለም ወጣኔ ኩሉ=ሁሉን የጀመረ ጌታ
ን=መኮንን እግዚአብሔር
ኖ=ኖላዊ እግዚአብሔር=ቸር እረኛ እግዚአብሔር ይላል።
በግእዝ ቋንቋ በሀሌታው ሀ የሚጻፈው በሐመሩ ሐ ወይም በብዙኀኑ ሀ ከተጻፈ እና።በእሳቱ ሰ የተጻፈው በንጉሡ ሰ ከተጻፈ እንዲሁም በጸሎቱ ጸ የሚጻፈው በፀሐዩ ፀ ከተጻፈ የትርጉም ልዩነት ስለሚያመጣ መጠንቀቅ ይገባል።ለምሳሌ
ሠዐለ=ሣለ
ሰአለ=ለመነ
ሠረቀ=ወጣ
ሰረቀ=ሰረቀ
እያለ የተለያየ ትርጉም ስላለው ጠንቅቀህ ጻፍ።

ምንጭ፦መጽሐፈ ግስ ወሰዋስው መርኆ መጻሕፍት
ሊቀ ሊቃውንት ያሬድ ሽፈራው

መሠረተ፡ግእዝ
@learnGeez1
@learnGeez1
@learnGeez1 👈
የግእዝ ቋንቋ ክፍል 14
ስለ ፊደል ክፍል 2።የግእዝ ቋንቋ እያንዳንዳቸው ፊደላት ምስጢረ ሥላሴ ነገረ ድኅነትን ስጋዌን የሚያስረዱ ናቸው።
አ=አአኲቶ ወእሴብሖ ለእግዚአብሔር=እግዚአብሔርን ፈጽሜ አመሰግነዋለሁ።
ኡ=ሙጻኡ ለቃል
ኢ=ለሊሁ ተንሣኢ ወለሊሁ አንሣኢ=ራሱ ተነሽ ራሱ አስነሽ
ኣ=ኣሌፍ ፈጣሬ ኩሉ ዓለም ቀዳማይ ወደኃራይ
ኤ=አምጻኤ ዓለማት እግዚአብሔር=ዓለማትን የፈጠረ እግዚአብሔር
እ=እግዚአብሔር እግዚእ=ጌታ እግዚአብሔር
ኦ=እግዚኦ=አቤቱ
ዐ=ዐቢይ እግዚአብሔር=እግዚአብሔር ታላቅ ነው።
ዑ=ነዋ በግዑ ለእግዚአብሔር=የእግዚአብሔር በግ እነሆ
ዒ=ለሊሁ ሠዋዒ ወለሊሁ ተሠዋኢ=ራሱ የሚሰዋ ራሱ የሚሰዋ
ዓ=ዓይነ ኩሉ ነፍስ ይሴፎ ኪያከ=ሰው ሁሉ አንተን ተስፋ ያደርጋል።
ዔ=ዐቢይ እግዚአብሔር
ዕ=ብፁዕ እግዚአብሔር
ዖ=ሞዖ ለሞት ወተንሥአ=ሞትን አሸንፎ ተነሳ
ከ=ከሀሊ እግዚአብሔር
ኩ=ዐርኩ ለመርአዊ
ኪ=ኪያሁ ንሰብክ=እርሱን እናስተምራለን
ካ=ካፍ=ከሀሊ እግዚአብሔር
ኬ=ሰባኬ ወንጌል ነዋ በማእከለ አኃው
ክ=ክብሮሙ ለመላእክት=የመላእክት ክብራቸው
ኮ=ዘረዳእኮ ለአብርሃም=አብርሃምን የረዳሀው
ወ=ወረደ እምሰማያት=ከሰማያት ወረደ
ው=ጼው ለምድር=የምድር ጨው
ዊ=ናዝራዊ
ዋ=ዋው=ዋሕድ እግዚአብሔር
ዌ=ዜናዌ ትፍሥህት=ደስታን የሚናገር
ው=ሥግው ቃል=ሰው የሆነ ቃል
ዎ=ቤዘዎ ለዓለም=ዓለምን አዳነው
ዘ=ዘኲሎ ይእኅዝ እግዚአብሔር=ሁሉን የሚይዝ እግዚአብሔር
ዙ=ምርኩዙ ለሐንካስ=የአንካሳ ምርኩዝ
ዚ=ናዛዚ=የሚያረጋጋ
ዛ=ዛይ=ዝኩር እግዚአብሔር
ዜ=አኃዜ ዓለም በእራኁ=ዓለምን በመዳፉ የያዘ
ዝ=ሐዋዝ ሕገ እግዚአብሔር=የእግዚአብሔር ሕግ መልካም ነው
ዞ=አግዓዞ ለአዳም=አዳምን ነጻ አወጣው።
የ=የማነ እግዚአብሔር ገብረት ኃይለ
ዩ=ዕበዩ ለእግዚአብሔር=የእግዚአብሔር ታላቅነት
ዪ=መስተስረዪ=የሚያስተሰርይ
ያ=አንተ ኬንያሁ=አንተ ጠቢቡ
ዬ=ዐሣዬ ሕይወት=ሕይወትን የሚሰጥ
ይ=ሲሳይ ለርኁባን=ለተራቡት ምግብ
ዮ=ዮድ=የማነ እግዚአብሔር
ደ=ደመረ መለኮቶ ምሥለ ሥጋነ ወሥጋነ ምስለ መለኮቱ።
ዱ=ፈዋሴ ዱያን=የታመሙትን የሚፈውስ
ዲ=ቃለ ዓዋዲ
ዳ=ዳሌጥ=ድልው እግዚአብሔር
ዴ=ዐማዴ ሰማይ ወምድር=ሰማይና ምድርን ያጸና
ድ=ወልድ ዋሕድ
ዶ=ፈነወ ዋሕዶ ወተሰበአ=አንድያ ልጁን ላከ
ገ=ገባሬ ሰማያት ወምድር=ሰማይና ምድርን የፈጠረ
ጉ=ለአስካለ ሕይወት ሐረጉ
ጊ=ጊዜ ገቢር ለእግዚአብሔር
ጋ=ጋሜል=ግሩም እግዚአብሔር
ጌ=ጽጌ ቅዱሳን=የቅዱሳን አበባ
ግ=ሐጋጌ ሕግ=ሕግን የደነገገ
ጎ=ሰርጎሙ ለሐዋርያት=የሐዋርያት ጌጣቸው
ጠ=ጠቢብ እግዚአብሔር
ጡ=ውስጡ ለሰብእ እግዚአብሔር
ጢ=መያጢሆሙ ለኃጥኣን=ኃጥአንን የሚመልስ
ጣ=የውጣ እንተ አሐቲ ሕርመታ
ጤ=ጤት=ጠቢብ እግዚአብሔር
ጥ=ስሉጥ ወርኡስ እግዚአብሔር
ጦ=ሦጦ ለመንፈስ ቅዱስ ላእሌነ
ጰ=ጰራቅሊጦስ መንፈሰ ጽድቅ=እውነተኛ መንፈስ መንፈስ ቅዱስ
ጱ=ኮጱ መዓዛ ሰብእ
ጲ=ሠራጲሁ ለዓለም
ጳ=ጳጳሰ ወንጌል
ጴ=አክራጴ ኃጢአት
ጵ=ጵርስፎራ
ጶ=ጶሊስ
ጸ=ጸጋ ወጽድቅ እግዚአብሔር=እግዚአብሔር እውነት እና ሀብት ነው።
ጹ=ገጹ ለአብ
ጺ=ሐዋጺ ነፍሰ ትሑታን=የትሑታንን ነፍስ የሚጎበኝ
ጻ=ጻዴ=ጻድቅ እግዚአብሔር
ጼ=አእቃጼ ሰኮና
ጽ=ጽንሑ ተስፋሁ ለአብ
ጾ=ጾም ትፌውስ ቁስለ ነፍስ=ጾም የነፍስን ቁስል ታድናለች።
ፀ=ፀሐየ ጽድቅ እግዚአብሔር
ፁ=ዮም ሠረፁ ጽጌ በረከት
ፂ=መላፂ ዘክልኤ አፉሁ
ፃ=ፋፃ መንፈስ ቅዱስ
ፄ=ሕፄሁ ለዳዊት
ፅ=ዕፀ አብርሃም ዘሠፀረ ለምሥዋእ
ፆ=ማዕፆ አፉሆሙ ለጻድቃን
ፈ=ፈጠረ ዓለመ በጥበቡ=ዓለምን በጥበቡ ፈጠረ
ፉ=ምዕራፉ ለዓለም
ፊ=ፊደለ ወንጌል
ፋ=አልፋ ወኦ
ፌ=ኀዳፌ ነፍሳት=የነፍሳት መምህር
ፍ=ፍኖት ለኀበ አቡሁ
ፎ=ፎራ ኅብስተ ቁርባን
ፐ=ፖፖኤል ስሙ ለእግዚአብሔር
ፑ=ኖፑ አስካለ ወንጌል
ፒ=ፒላሳሁ
ፓ=ፓንዋማንጦን
ፔ=እግዚአብሔር
ፕ=ሮፕ=ጽኑዕ እግዚአብሔር
ፖ=በቀዳሚ ገብረ እግዚአብሔር ሰማየ ወምድረ ወበደኃሪ የኀልፎ ለዓለም።

ምንጭ፦መጽሐፈ ግስ ወሰዋስው መርኆ መጻሕፍት
ሊቀ ሊቃውንት ያሬድ ሽፈራው

መሠረተ፡ግእዝ
@learnGeez1
@learnGeez1
@learnGeez1 👈
2024/10/02 04:29:48
Back to Top
HTML Embed Code: