Telegram Web Link
በአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና የሚሳተፈው የኢትዮጵያ ልዑክ ወደ ካሜሩን አቀና

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 12፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ23ኛው የአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና የሚሳተፈው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ልዑክ ወደ ካሜሩን ዱዋላ አቀና፡፡

23ኛው የአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና በካሜሩን አስተናጋጅነት በዱዋላ እንደሚካሄድ ከኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌደሬሽን ያገኘነው መረጃ አመላክቷል፡፡

የኢትዮጵያ ልዑክም ዛሬ ጠዋት ወደ ካሜሩን ያቀና ሲሆን÷ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌደሬሽን የሥራ ኃላፊዎች በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ተገኝተው አሸኛኘነት አድርገውለታል፡፡
በአዲስ አበባ የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና መሰጠት ጀመረ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 12፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የ2016 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና በተለያዩ የፈተና ጣቢያዎች መሰጠት መጀመሩን የአዲስ አበባ ከተማ አሥተዳደር ትምህርት ቢሮ አስታወቀ፡፡

በ183 ጣቢያዎች ፈተናው መሰጠት መጀመሩን የቢሮው ኃላፊ ዘላለም ሙላቱ (ዶ/ር) ገልጸዋል፡፡

ፈተናው ያለምንም እንከን እንዲጠናቀቅ በሁሉም የፈተና ጣቢያዎች የፈተና አስፈጻሚዎችን ጨምሮ በቂ የጸጥታ አካላት መመደባቸውንም አስታውቀዋል።

ተማሪዎች ለፈተናው ብቁ እንዲሆኑ የማጠናከሪያ ትምህርትን ጨምሮ ደረጃቸውን የሚመጥን ሞዴል ፈተና መሰጠቱን አስታውሰዋል፡፡
ታማሚ አሳፍሮ ወደ ሆስፒታል ሲጓዝ የነበረ አምቡላንስ ተገልብጦ የ3 ሰዎች ህይወት አለፈ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 12፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ከዳሰነች ወረዳ ታማሚ አሳፍሮ ለተሻለ ሕክምና ወደ ጂንካ አጠቃላይ ሆስፒታል ሲጓዝ የነበረ አምቡላንስ ተገልብጦ የሦስት ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ አራት ሰዎች ከባድ ጉዳት ደረሰባቸው፡፡

አደጋው የደረሰው በደቡብ ኦሞ ዞን በና ፀማይ ወረዳ አርጎ ቀበሌ አርጎ ቁልቁለት አካባቢ መሆኑን የዳሰነች ወረዳ ኮሙኒኬሽን ጽሕፈት ቤት መረጃ አመላክቷል፡፡

ከባድ ጉዳት የደረሰባቸው ወገኖችም በጂንካ አጠቃላይ ሆስፒታ የሕክምና ዕርዳታ እያገኙ ሲሆን÷ የአደጋው መንስኤ በመጣራት ላይ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡
ሰሜን ኮሪያ ሩሲያ ከዩክሬን ጋር ለምታደረግው ጦርነት ድጋፍ እንደምታደርግ ገለጸች

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 12፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት ሰሜን ኮሪያ ፒዮንግያንግ የገቡት የሩሲያ ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ኪም ጆንግ ኡን በወታደራዊ ትርዒት የታጀበ ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል፡፡ ፑቲን ባለፈው መስከረም ወር ኪም ጆንግ ኡን ባቀረቡላቸው ግብዣ መሰረት ነው ከ24 ዓመታት በኋላ ወደ ሰሜን ኮሪያ ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት ያቀኑት፡፡ ሁለቱ መሪዎች…

https://www.fanabc.com/archives/250361
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
"በኢትዮጵያ በተለያዩ ሥነ-ምኅዳሮች ከ6 ሺህ በላይ የዕጽዋት ዝርያዎች ይገኛሉ። ከእነዚህ መካከልም 12 በመቶ ገደማ በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙ ሲሆን÷ የተቀሩት እኛም ጋር፤ ከኛም ሀገር ውጪ የሚገኙ ናቸው።"- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የንቅናቄ መድረክ እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 12፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት የ2016 የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የንቅናቄ መድረክ በዓድዋ ድል መታሰቢያ እየተካሄደ ነው። በመድረኩ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፣ የሰላም ሚኒስትር ብናልፍ አንዱዓለም፣ የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር)፣ የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች…

https://www.fanabc.com/archives/250376
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ማስታወቂያ!

ጤናችን በምርታችን !


በሀገራችን የመጀመሪያ የሆነው የሀገር ውስጥ የህክምና ግብዓት ምርትና ኢኖቬሽን ኤግዚብሽን ከ ሰኔ 15 - 20 /2016 ዓ.ም በአዲስ አበባ ሚሊኒየም አዳራሽ ይካሄዳል፡፡

በዚህ ታላቅ ኤግዚብሽን ፤-

• በሀገራችን በባህላዊ እና በዘመናዊ መድሀኒት፤
• በህክምና መገልገያ መሳሪያ
• የጤና እና የግል ንጽህና መጠበቂያ ማምረት ላይ የተሰማሩ ከአነስተኛ አስከ ከፍተኛ አምራች ድርጅቶች ምርቶቻቸውን ያስተዋውቃሉ፤
• የቴክኖሎጂ እና የፈጠራ ውጤቶች ይቀርባሉ
• የሀገር ውስጥና አለም ዓቀፍ የንግድ ትስስሮች እና የልምድ ልውውጦች ይደረጋሉ፡፡
• ዓለም ዓቀፋዊ ተሞክሮዎችና አሰራሮችላይ ያተኮረ የፓናል ውይይቶች ይካሄዳሉ፤
እርስዎ፡- መጥው ሲጎበኙ ሀገራችን እያከናወነች ያለውን እና ወደፊት የምትደርስበትን የህክምና ግብዓት አምች ኢንደስትሪ ዘርፍ ሁለንተናዊ እድገት ይመለከታሉ፤ በርካታ ኢንቨስትመንት እድሎችም እንዳሉ ይገነዘባሉ፡፡

ይምጡ፤ ይካፈሉ፤ ይጎብኙ

ጤና ሚኒስቴር ከመድኃኒትና የህክምና መገልገያ አምራች ዘርፍ ማህበራት ጋር በመተባበር
ለበለጠ መረጃ 011 518 6262 / 952 ላይ ይደውሉ!! ድህረ ገጻችንን ይጎብኙ!!
https://pharma-exhibition.moh.gov.et/
#ጤናችን በምርታች
#our health by our products
Website: moh.gov.et
Facebook: Ministry of Health,Ethiopia
Twitter: twitter.com/FMoHealth
YouTube: @FMoHealthEthiopia
Tiktok: @mohethiopia
"ሰው ሀገሩን ምን ያህል ይወዳል? ሲባል መልሱ "በበጎ ፈቃድ የሚያገለግላትን ያህል" ነው።

"በጎነትና አብሮነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል የሚካሄደውን የ2016 ዓ.ም ሀገር አቀፍ የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ንቅናቄን ዛሬ አስጀምረናል፡፡

የበጎ ፈቃድ አገልግሎት መርሐ-ግብር ብቻ ሳይሆን እንደ ኢትዮጵያ ባለ በብዝሃነት የደመቀ ሀገር ውስጥ ለጋራ ዕድገት እና የብልጽግና ግባችን መሳካት ወሳኝ መሳሪያ ነው።

ይህ አገልግሎት ዜጎች ጊዜያቸውን፣ ጉልበታቸውን፣ ዕውቀታቸውንና ክህሎታቸውን ለሀገራቸው ዕድገት ያላቸውን ትብብርና ትጋት የሚያንጸባርቁበት ተግባር ነው።

በመሆኑም በዘንድሮ የክረምት ወራትም አገልግሎቱ ከታጠረበት የክረምት ወቅት በዘለለ የሁልጊዜ ተግባር ሆኖ የሚቀጥልበትን ስልት በመንደፍ፤ታዳጊዎችና ወጣቶች ወደፊት የሚረከቧትን ብቻ ሳይሆን አሁን የሚኖሩባትንም ሀገር የሚገነቧት ራሳቸው መሆናቸውን በተግባር የሚያሳዩበት እንዲሆን ጥሪዬን አቀርባለሁ፡፡" ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
በሁመራ እና አካባቢው የተቋረጠውን ኃይል መልሶ ለማገናኘት እየተሰራ ነው

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 12፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በሁመራ እና አካባቢው በተፈጥሯዊ አደጋ ምክንያት የተቋረጠውን ኃይል መልሶ ለማገናኘት የሚያስችል ስራ መጀመሩን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል አስታወቀ፡፡ ከሽሬ- ሁመራ በተዘረጋው ባለ 230 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ላይ በደረሰ ተፈጥሯዊ አደጋ ኃይል መቋረጡን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ምዕራብ ሪጅን የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ…

https://www.fanabc.com/archives/250381
2024/09/28 12:16:41
Back to Top
HTML Embed Code: