Telegram Web Link
Live stream finished (36 minutes)
ቻይና በዓለም ትልቁን የትራንስፖርት ማሳለጫ ገነባች

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 12፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ቻይና በዓለም ትልቁን የትራንስፖርት ማሳለጫ በከፍተኛ ወጪ መገንባቷ ተመላክቷል፡፡ የቻይና የማሳለጫ መንገዶች ርዝማኔ በፈረንጆቹ 2023 ከ6 ሚሊየን ኪሎ ሜትሮች በላይ ማደጉ ተገልጿል፡፡ ይህም በዓለም ትልቁ የፍጥነት ባቡር፣ የፈጣን መንገድ ኔትወርክ፣ የፖስታ ኤክስፕረስ ማከፋፈያ አውታር እና ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የወደብ መገልገያ ትስስር ያለው መሆኑን…

https://www.fanabc.com/archives/250384
አስተናጋጇ ጀርመን ዛሬ ተጠባቂ ጨዋታዋን ታደርጋለች

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 12፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ትናንት የመጀመሪያው ዙር የምድብ ማጠሪያ መጠናቀቁን ተከትሎ ዛሬ ሁለተኛው ዙር የምድብ ማጣሪያ ጨዋታ ይጀመራል፡፡

በዚህም ባለፈው በስፔን 3 ለ 0 የተሸነፈችው ክሮሺያ በጣልያን 2 ለ 1 ከተረታችው አልባኒያ ጋር ቀን 10 ሠዓት ላይ ይጫወታሉ፡፡

እንዲሁም ምሽት 1 ሠዓት ላይ አስተናጋጇ ጀርመን ከሀንጋሪ የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል፡፡

የመጀመሪያውን የምድብ ማጣሪያ ሀንጋሪ በስዊዘርላንድ 3 ለ 1 መሸነፏ ይታወሳል፡፡

በጀርመን 5 ለ 1 በሆነ ሰፊ ልዩነት የተረታቸው ስኮትላንድም ዛሬ ምሽት 4 ሠዓት ላይ ስዊዘርላንድን ታስተናግዳለች፡፡

በምድብ አንድ ጀርመን ስዊዘርላንድን በማስከተል በምድቡ ቁንጮ የተቀመጠች ሲሆን÷ ምድብ ሁለትን ስፔን በቀዳሚነት ስትመራ ጣልያን ተከታዩን ደረጃ ይዛለች፡፡
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
አንድ ጉዳይ -በሁሉም የፋና የማህበራዊ ትስስር ገፆች በቅርብ ቀን ይጠብቁን! #አንድጉዳይ #Andguday
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ጋምቤላ - ምድረ ወርቅ (ሐሙስ ምሽት ይጠብቁን)
ለጤና ጠንቅ የሆነ ህገ ወጥ ጨው አከማችተው የተገኙ ድርጅቶችና ግለሰቦች በገንዘብና በፅኑ እስራት ተቀጡ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 12፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ከ 34 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት ለጤና ጠንቅ የሆነ ህገወጥ ጨው በመጋዘን አከማችተው የተገኙ 2 ድርጅቶችና 3 ግለሰቦች በገንዘብና በፅኑ እስራት ተቀጡ። የኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ ከፍተኛ ፍ/ቤት 1ኛ ወንጀል ችሎት ነው ዛሬ በነበረው የችሎት ቀጠሮ ተከሳሾቹ በጽኑ እስራትና በገንዘብ እንዲቀጡ የወሰነባቸው፡፡ ተከሳሾቹ በጨው ምርትና…

https://www.fanabc.com/archives/250409
እስከ ሰኔ 9 ቀን 2016 ድረስ 13 ነጥብ 63 ሚሊየን ሔክታር በባህላዊና በትራክተር ታርሷል – ግብርና ሚኒስቴር

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 12፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ለ2016/17 ምርት ዘመን የመኸር ወቅት እስከ ሰኔ 9 ቀን 2016 ድረስ 13 ነጥብ 63 ሚሊየን ሔክታር በባህላዊና በትራክተር መታረሱን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ። ዘንድሮ በመስኖ ስንዴ ልማት 3 ሚሊየን ሔክታር በማረስ 120 ሚሊየን ኩንታል ምርት ለማግኘት ርብርብ መደረጉን አስታውሶ፤ እስከ ሰኔ 9 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ…

https://www.fanabc.com/archives/250408
እስራኤል በሊባኖስ ወታደራዊ ዘመቻ ለማካሄድ ዝግጁ መሆኗን አስታወቀች

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 12፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) እስራኤል በሊባኖስ የሂዝቦላህ ታጣቂ ቡድን ይዞታዎች ላይ ወታደራዊ ዘመቻ ለማካሄድ መወሰኗ ተሰምቷል፡፡ ውሳኔው ሂዝቦላህ የእስራኤል ወታደራዊ ማዕከላትን የሚያሳይ በድሮን የተቀረጸ ተንቀሳቃሽ ምስል ይፋ ማድረጉን ተከትሎ የተላለፈ እንደሆነ ተነግሯል። በተጨማሪም ተንቀሳቀሽ ምስሉ የንጹሃን ዜጎችን መኖሪያ፣ የጦር መሳሪያ ማምረቻ ፋብሪካዎችን እና የሚሳኤል መከላከያ ባትሪዎችን እንደሚያሳይ አልጀዚራ ዘግቧል፡፡…

https://www.fanabc.com/archives/250418
ኢትዮጵያ በብሪክሱ መድረክ ተባብሮ የመስራት ችሎታዋንና ዓለም አቀፋዊ አጋርነቷን ማስመስከር ችላለች

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 12፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በሩሲያ ቪላዲቮስቶክ የተካሄደው የብሪክስ አባል ሀገራት ዓለም አቀፍ የፖለቲካ ፓርቲዎች ፎረም በስኬት ተጠናቋል፡፡
የጉባኤው ተሳታፊዎችም በጉባኤው ማጠናቀቂያ ላይ 24 ነጥቦችን የያዘ የአቋም መግለጫ በማውጣት ለስኬታማነቱ እንደሚሰሩ ቃል ገብተዋል።

በመድረኩ ኢትዮጵያ የላቀ የዲፕሎማሲ ድል ማስመዝገቧን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አዲሱ አረጋ ገልፀዋል።

https://www.fanabc.com/archives/250422
እየተዘጋጀ ያለው የተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ ተጨማሪ አሰራሮችን ለማካተት የሚያስችል ነው – ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 12፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በዝግጅት ሂደት ላይ ያለው የተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ የመንግሥትን ገቢ የመሰብሰብ አቅም የሚያሳድግና ከዚህ ቀደም በተጨማሪ ዕሴት ታክስ ውስጥ ያልተካተቱ አሰራሮችን ለማካተት የሚያስችል መሆኑን የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ በበጀት ዓመቱ ተግባራዊ ይደረጋል ተብሎ በሚጠበቀው የተጨማሪ እሴት ታክስ የማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ ላይ የውይይት…

https://www.fanabc.com/archives/250421
አርባ ምንጭ ከተማን ለኑሮ ምቹ ለማድረግ የኮሪደር ልማት ሥራዎች እየተከናወኑ እንደሆነ ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 12፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የአርባ ምንጭ ከተማን ጽዱ፣ ውብ፣ ለኑሮ ምቹና ለጎብኚዎች ሳቢ የሚያደርጉ የኮሪደር ልማት ሥራዎች ከ200 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ እየተካሄዱ መሆኑን የከተማዋ ማዘጋጃ ቤት ገለጸ፡፡ የማዘጋጃ ቤቱ ሥራ አስኪያጅ ገዳሙ ሻምበል፤ የኮሪደር ልማቱ ከተማዋ በተፈጥሮ የታደለቻቸው ሀብቶች ጎልተው እንዲወጡና ተመራጭነቷን ለማሳደግ እንደሚያስችል ተናግረዋል። ልማቱ ኅብረተሰቡን…

https://www.fanabc.com/archives/250427
በመከላከያ ሰራዊት አመራሮች ሲመራ የነበረው የሰላም ኮንፈረንስ ተጠናቀቀ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 12፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የመከላከያ ሰራዊት ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎችን በማሳተፍ ሲካሄድ የቆየው የሰላም ኮንፈረንስ ተጠናቅቋል፡፡

ትናንትናና ዛሬ በደሴ፣ ደብረ ብርሃን፣ ሰቆጣ እና ጎንደር ከተሞች የተካሄደው የተለያዩ የሕብረተሰብ ተወካዮች የተሳተፉበት የሰላም ኮንፍረንስ የአቋም መግለጫ በማውጣት ማምሻውን ተጠናቋል።

በአቋም መግለጫቸውም÷ በክልሉ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፈን የበኩላቸውን እንደሚወጡ አረጋግጠዋል፡፡

በኮንፈረንሱ ማጠቃለያ ተወያዮች ባወጡት የአቋም መግለጫ÷ በክልሉ ሰላም እንዲረጋገጥ ታጥቀው የሚንቀሳቀሱ ወገኖች ወደ ሰላማዊ መንገድ እንዲመጡ ጠይቀዋል።

https://www.fanabc.com/archives/250433
ማስታወቂያ

በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ኢንተርኔት ባንኪንግ አገልግሎት ይጠቀሙ፡፡
***************************************
በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ኢንተርኔት ባንኪንግ አገልግሎት በማንኛውም ሰዓት፣ በየትኛውም ቦታ እና ሀገር ሆነው ገንዘብዎን በአግባቡ ያስተዳድሩ!
- ግብሮን ለመክፈል
- የአየር ትኬት ለመቁረጥ
- ገንዘብ ለመላክ
- ደመወዝ ለመክፍል
ቀላል አማራጭ በሆነው በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ኢንተርኔት ባንኪንግ ይጠቀሙ፡፡
********************
#ኢንተርኔት ባንኪንግ #ግብሮንለመክፈል # ገንዘብ ለመላክ
የኢትዮጵያ #ንግድ ባንክ
#ሁሌም የሚተማመኑበት ባንክ!
ማስታወቂያ!


የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ በግንባታው ዘርፍ ግንባር ቀደም በመሆን ደረጃቸውን የጠበቁ የህንጻ፣ የመንገድ፣ የመስኖና ግድብ፣ የኤርፖርት እና መሰል ግዙፍ ፕሮጀክቶችን ይገነባል፡፡

በኮንስትራክሽን ዘርፍ ጥራትን መለያው አድርጎ ዘላቂና አስተማማኝ የግንባታ ሥራዎችን በመሥራት በግንባታው ዘርፍ የልማት አጋርነቱን እያስመሰከረ ይገኛል፡፡

መከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ
ስለ ድርጅቱ የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.dce-et.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/defenseconstruction
ቴሌግራም፦ https://www.tg-me.com/www.tg-me.com/DCE2020
ትዊተር፦ https://twitter.com/
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
የተመዘገበው የኢኮኖሚ እድገት ቀጣይነት እንዲኖረው ይሰራል - ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 12፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ የተመዘገበው የኢኮኖሚ እድገት ቀጣይነት እንዲኖረው ምርታማነትን የሚያሳድጉ ሥራዎች በትኩረት ይሰራሉ ሲሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡

የመንግስት የ2016 ዓ.ም የማክሮ ኢኮኖሚ አፈጻጸም ላይ ከአገልግሎቱ ሰራተኞች ጋር በተደረገ ውይይት ላይ ሚኒስትሩ እንደተናገሩት÷ እድገቱን ለማስቀጠል እየተተገበሩ ያሉ ኢንሼቲቮች በከፍተኛ ሁኔታ ማደግ አለባቸው፡፡

https://www.fanabc.com/archives/250417
ክሮሺያ እና አልባኒያ አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 12፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ17ኛው የ2024 የአውሮፓ ዋንጫ ክሮሺያ እና አልባኒያን ሁለት አቻ ተለያይተዋል፡፡

የአልባኒያን ጎል ላቺ በ11ኛው እና ጋሱላ በ95ኛው ደቂቃ ከመረብ ሲያሳርፉ÷ የክሮሺያን ጎሎች ደግሞ ክራማሪች በ74ኛው እና ጋሱላ (በራስ ላይ) በ76ኛው ደቂቃ አስቆጥረዋል፡፡

በመጀመሪያው የምድብ ማጣሪያ ጨዋታ ክሮሺያ በስፔን 3 ለ 0 እንዲሁም አልባኒያ በጣልያን 2 ለ 1 መሸነፋቸው ይታወሳል፡፡

እንዲሁም ምሽት 1 ሠዓት ላይ የ17ኛው የ2024 የአውሮፓ ዋንጫ አዘጋጇ ጀርመን ከሀንጋሪ የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል፡፡

የመጀመሪያውን የምድብ ማጣሪያ ሀንጋሪ በስዊዘርላንድ 3 ለ 1 መሸነፏ ይታወሳል፡፡

በጀርመን 5 ለ 1 በሆነ ሰፊ ልዩነት የተረታቸው ስኮትላንድም ዛሬ ምሽት 4 ሠዓት ላይ ስዊዘርላንድን ታስተናግዳለች፡፡
2024/09/28 14:14:55
Back to Top
HTML Embed Code: