Telegram Web Link
ዶክተር አሸብር
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
Join the Kifiya AI Mastery Training Program!

Apply by August 16, 2024👉 apply.10academy.org

Learn more about the training program at https://10academy.org/kifiya/learn-more
Forwarded from Sheger Press️️
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
Join the Kifiya AI Mastery Training Program!

Apply by August 16, 2024👉 apply.10academy.org

Learn more about the training program at https://10academy.org/kifiya/learn-more
በአዲስ አበባ ከተማ ጤፍ በተለያዩ የንግድ ተቋማት እስከ 18 ሺህ ብር እየተሸጠ መሆኑ ተነገረ  

ጤፍ በአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ባዘጋጃቸው የንግድ ማዕከላት  ላይ እስከ 12ሺህ ብር የሚሸጥ መሆኑ ተገልጿል ። ይሁን እና  በህገወጥ መልኩ  የጤፍ ዋጋ ላይ ጭማሪ የሚያደርጉ ተቋማት ላይ  ከፍተኛ የሆነ የቁጥጥር  እና  እርምጃ  እየተወሰዱ  መሆኑ  ተገልጿል ።

ከሃምሌ 22 ጀምሮ የዶላር ጭማሪ መኖሩን ምክንያት አድርገው በህገወጥ መልኩ ምርት በመደበቅ እና ዋጋ ጨምረው የተገኙ 768 የንግድ ተቋማት ላይ እርምጃ መውሰዱን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር   ንግድ ቢሮ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር የሆኑት አቶ አቶ ሰውነት አየለ በተለይም ለብስራት  ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ተናግረዋል።

እርምጃ ከተወሰደባቸው 768 ተቋማት መካካል 345 የሚሆኑት ያለአግባብ ዋጋ በመጨመር  423  ደግሞ  ምርት ሸሽገው የተገኙ  መሆናቸው ተገልጿል ።በአሁን ሰዓት እርምጃ ተወስዶባቸው  የነበሩ ተቋማት ይቅርታ ጠይቀው እና በተተመነላቸው ዋጋ ለመሸጥ ውል ፈርመው  ተቋማቸው አገልግሎት መስጠት የጀመረ ሲሆን የተወሰኑት ባለመስማማታቸው እስካሁን አገልግሎት መስጠት እንዳልጀመሩ ተጠቁሟል  ።

በአሁን ሰዓት በገበያ ማዕከላት ኪሎ 115 እስከ 135 ብር እንደ ደረጃው እየተሸጠ መሆኑን የገለጹልን ቢሆንም አለአግባብ  ጭማሪ በማድረግ  ከ18ሺህ ብር ጀምሮ እየሸጡት የሚገኙ  ህገወጥ ነጋዴዎች መኖራቸውን  አቶ ሰውነት አየለ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ተናግረዋል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
አርቲስት መኮንን ላዕከ:

"ለዚህ ኦሎምፒክ ውድቀት መንስኤ የሆኑትን ሰዎች አውቀናቸዋል ካወቅናቸው ሳንፈራ አጋልጠን እኛ ብቻ ሳይሆን እነሱም አንገታቸውን መድፋት አለባቸው።"

"ሁልጊዜ EBC ይጀምራል አይጨርስም አሁን ግን ትክክለኛ ለውጥ እንፈልጋለን።"

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
አትሌት ታምራት ቶላ የኮማንደርነት ማዕረግ ተሠጠው፣ 7 ሚሊየን ብር ተሸለመ

👉 የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን በፓሪሱ ኦሊምፒክ በማራቶን ውድድር ለሀገሩ የወርቅ ሜዳሊያ ላስገኘው አትሌት ታምራት ቶላ የኮማንደርነት ማዕረግ ሰጥቷል፡፡

👉 ለአትሌት ትግስት አሰፋ የምክትል ኮማንደርነት፣

👉ለአትሌት ለሜቻ ግርማ የዋና ኢንስፔክተር፣

👉ለአትሌት ሲሳይ ለማ የዋና ኢንስፔክተር እንዲሁም

👉ለአትሌት መገርቱ ዓለሙ የረዳት ኢንስፔክተርነት ማእረግ መስጠቱ ታውቋል።

✍️በዚህ ምሽት ፕሬዝደንት ሳህለወርቅ በብሔራዊ ቤተመንግስቱ በፓሪስ ኦሊምፒክ ለተሳተፈው የኢትዮጵያ ልዑክ የእውቅናና የሽልማት መርሐ ግብር እየተካሄዱለት ይገኛሉ።

በስነ ስርዓቱ አትሌት ታምራት ቶላ 7 ሚሊዮን ብር እና የወርቅ ኒሻን ተሸልሟል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
በህወሓት እና ጊዜያዊ አስተዳደሩ መካከል ያሉ ቁርሾዎች በክልሉ ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ከፍተኛ ስጋት ደቅኗል” ኢዜማ

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማሕበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) በህወሓት እና በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር መካከል “አሉ” ያላቸው ቁርሾዎች በክልሉ ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ከፍተኛ ስጋት መደቀናቸውን አስታወቀ።

ፓርቲው ዛሬ ባወጣው መግለጫ፣ የፌደራል መንግስት እና የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የዜጎችን ሰላም እና ደህንነትን ከምንም ጉዳይ በፊት ትኩረት እንዲሰጡ አሳስቧል።

ኢዜማ በዚህ መግለጫው “በአንድ የፖለቲካ ፓርቲ የውስጥ አሰራር እና ሒደት ላይ አሰተያየት መስጠት” ፍላጎቱ አለመሆኑን ጠቅሶ፣ ነገር ግን “እብሪተኛ” ሲል በሚነቅፈው ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ምክንያት በትግራይ ክልል እና አጎራባች ክልሎች ውስጥ በሚገኙ ንፁሐን ዜጎች ላይ ይዞ ሊመጣ የሚችለው አደጋ ቀላል አለመሆኑን ገልጿል።

አክሎም፣ ህወሓት እንደፓርቲ ሕልውናውን ለማስቀጠል እያደረገው “ነው” ባለው ሂደት ሳቢያ፣ እንዲሁም የፓርቲው አመራሮች የእርስ በእርስ ሽኩቻ፤ በህወሓት እና ጊዜያዊ አስተዳደሩ መካከል “አሉ” ባላቸው ቁርሾዎች የተነሳ በክልሉ ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ከፍተኛ ስጋት “ደቅኗል” ሲል ኢዜማ በመግለጫው አትቷል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል የመክፈቻ ንግግር አድርጉው ነበር።

በመክፈቻ ንግግራቸው ህወሓት ፈረሰ ማለት የፕሪቶርያው ውል ፈረሰ ማለት ነው ሲሉ ተደምጠዋል

ድርጅቱ ህጋዊ እውቅና እንዳያገኝና ጉባኤ እንዳያካሂድ የሚያደናቅፍ ከፍተኛ አመራር በድርጅቱ ውስጥ ተፈጥሯል ያሉት ሊቀመምበሩ

የዚህ ጉባዔ ዋና ዓላማ ድርጅቱን አድኖ ህዝቡን ከጥፋት ማዳን ነው።

ድርጅታችንና ህዝባችን የሚድኑት በዚህ ጉባዔ ነው።
ሙሉ በሙሉ እንድንድን በዴሞክራሲያዊ መንገድና ክርክርና ውይይት ሙሉ ብቃት ያላቸው አመራር ሊመረጡ ይገባል።

ይሄ ጉባኤ የድርጅቱም የህዝቡም የሞት ሽረት ጉዳይ ነው።>>ማለታቸውን ከፓርቲው ገፆች ለማየት ተችሏል።


@sheger_press
@sheger_press
Dogs‼️

እንደ ኖትኮይን ላንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ላንሰራው ነው።

ዛሬ የመጨረሻ ቀን ነው በፍፁም እንዳያመልጣቹ።

ዛሬ ብጀምሩ ራሱ ከ20 ሺ በላይ መስራት ትችላላቹ።

ያልጀመራቹ በዚ ጀምሩ👇👇

https://www.tg-me.com/dogshouse_bot/join?startapp=qA4t5KguQWKX0tWVVEhxSQ
https://www.tg-me.com/dogshouse_bot/join?startapp=qA4t5KguQWKX0tWVVEhxSQ


ስለ አሰራሩ ለማወቅ ይህን ቻናል ተቀላቀሉ👇👇
https://www.tg-me.com/+fzeZ2gn56UE3NTI0
https://www.tg-me.com/+fzeZ2gn56UE3NTI0
ህውሀት‼️

ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) በተለያዩ ወገኖች ተቃውሞ እና ትችት የተሰነዘረበትን የጠቅላላ ጉባኤ የመክፈቻ ስነ ስርዓት፤ ዛሬ ማክሰኞ ነሐሴ 07፤ 2016 በመቐለ ከተማ በሚገኘው የሰማዕታት ሐውልት አዳራሽ አካሄዷል። ፓርቲው ጠቅላላ ጉባኤውን ያካሄደው ምክትል ሊቀመንበሩ አቶ ጌታቸውን ረዳን ጨምሮ 14 የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ባልተገኙበት ነው። 

ህወሓት ከስድስት ዓመት በኋላ የጠራው የዛሬው ጠቅላላ ጉባኤ፤ ከዚህ ቀደም የነበሩ የአከባበር ሂደቶች ያልታዩበት ነበር። ጠቅላላ ጉባኤውን ያስተናገደችው የመቐለ ከተማ፤ በመሰል ስብሰባዎች ወቅት የሚታየው መጨናነቅ አልተስተዋለባትም። ወዳጅ ሀገራት ፓርቲዎችም ሆነ የሀገር ውስጦቹ አጋር ፓርቲዎችም፤ እንደ ድሮው የድጋፍ ንግግር ለማሰማት ወደ ከተማይቱ አልመጡም።

የፓርቲው ጠቅላላ ጉባኤ እንደሚካሄድ ያበስሩ የነበሩ ግዙፍ “ቢልቦርዶች” በበርካታ ቦታዎች አልተሰቀሉም። በከተማይቱ ሶስት ቦታዎች የተተከሉት አነስተኛ የማስታወቂያ ሰሌዳዎችም፤ የሰውን ትኩረት ያን ያህል ሲስቡ አልታዩም። የጠቅላላ ጉባኤው ስሜት ይበልጥ ጎላ ብሎ የተስተዋለው፤ የህወሓት ጽህፈት ቤት በሚገኝበት እና በስብሰባው አዳራሽ አቅራቢያ ነው።

ወደ ሰማዕታት ሐውልት አዳራሽ ሲገባ የነበረው ስሜት ግን በውጭ ከሚታየው የተለየ ነበር። በቀይ ኮፍያ፣ በቢጫ የአንገት ልብስ እና በነጭ ቲሸርት የደመቁት የጉባኤተኛው ተሳታፊዎች፤ ከመድረክ ለሚተላለፉ ዝግጅቶች በእጃቸው የያዟቸውን ባንዲራዎች በማውለብለብ ድጋፋቸውን በጋለ ስሜት ሲሰጡ ታይተዋል።

@sheger_press
@sheger_press
ሆ ቢገባው ይህ ብር ስንት ለተቸገሩ ወገኖቻችን ሊሆን እንደሚችል አልተረዳውም።

“ ሁለት ሚልዮን ብር ለእኔ እንደ ስድብ ስለሆነ መመለስ እፈልጋለሁ“ አሰልጣኝ ገመዶ ደደፎ

በፓሪስ ኦሎምፒክ ውድድር የተሳተፈው የኢትዮጵያ ልዑክ ቡድን በዛሬው ዕለት በብሔራዊ ቤተ-መንግሥት የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በተገኙበት ግብዣ ተደርጎለት ነበር።

በግብዣ እና ሽልማት ዝግጅቱ ላይ በውድድሩ ለኢትዮጵያ ሜዳልያዎች ያስገኙ አትሌቶች እና አሰልጣኞች ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

በውድድሩ ለሀገራችን ብቸኛውን ወርቅ ያስገኘው አትሌት ታምራት ቶላ ሰባት ሚልዮን ብር እና የወርቅ ኒሻን ሽልማት ተበርክቶለታል።

የታምራት ቶላ እና ትግስት አሰፋ አሰልጣኝ ገመዶ ደደፎ በበኩሉ የሁለት ሚልዮን ብር ሽልማት ለመቀበል ፍቃደኛ ሳይሆን ቀርቷል።

በዝግጅቱ ላይ መልዕክቱን ያስተላለፈው አሰልጣኝ ገመዶ ደደፎ “ ፕሬዝዳንታችን እኛ አሰልጣኞች ለረጅም ጊዜ ለፍተናል ፣ ልፋታችንን አይመጥንም “ ብሏል።

አያይዞም “ ለኔ ሁለት ሚልዮን የስድብ ያህል ስለሆነ እርስዎን ካላስከፋዎት ይሄንን ሽልማቴን መመለስ እፈልጋለሁ ፣ ለሚመጣው ሁሉ እቀባለለሁ “ ሲል ተናግሯል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
Telegram‼️

ተወዳጁ የSocial media platform Telegram በወንድማማቾቹ Pavel Durovና Nikoli Durov ከተመሰረተ እነሆ ዛሬ 11ኛ ዓመቱን ይዟል።

በ2013 ዋና መስርያ ቤቱን ጀርመን በርሊን በማድረግ ስራውን የጀመረው ቴሌግራም ለተወሰኑ አመታት ምንም አይነት ገቢ የማያስገባና በየወሩ ከ1 ሚሊዮን ዶላር በላይ ለስራ ማስኬጅ የሚያስወጣ Social media platform ነበር።

ከሌሎች የማህበራዊ ሚድያ መተግበሪያዎች በተሻለ የተጠቃሚዎቹን መረጃ ሚስጥራዊነት  እንደሚጠብቅ የሚነገርለት ይህ አፕ በአጭር ጊዜ ውስጥ በብዙዎች ዘንድ በመወደድ ስኬት ማስመዝገብ ጀመረ።

ከመንግስታዊ ተፅዕኖም ነፃ በመሆኑና ከዋና ተገዳዳሪው ዋትሳፕ የተሻለ ብዙ ፊቸሮች ስለጨመረ በብዙዎች ዘንድ ለመወደድ በቃ።

http://www.tg-me.com/sheger_crypto
http://www.tg-me.com/sheger_crypto
ያለ ስምምነት ተጠናቀቀ‼️

ለሁለት ቀናት በሱማሊያ እና ኢትዮጵያ መካከል ሲደረግ የነበረዉ ድርድር ያለስምምነት ተጠናቀቀ::

ዉይይቱ በቱርኪዬ አሸማጋይነት በሁለት ዙር የተካሄደ ሲሆን አላማዉም በኢትዮጵያ እና በሶማሊያ መካከል የተፈጠረውን ዉጥረት አርግቦ ጉዳያቸውን በንግግር እንዲፈቱት ነበር።

የሶማሊያ የዉጪ ጉዳይ ሚኒስትር አህመድ ሞአሊም ፊቂ በኤክስ ገጻቸዉ ላይ እንዳሰፈሩት ሶማሊያ ኢትዮጵያ ከሶማሊላንድ ጋር የገባችዉን ስምምነት አንቀበልም ብለዋል።

የኢትዮጵያ መንግስት የማይዘዉን ለማግኘት እየሄደበትት ያለዉን መንገድ ሶማሊያ አትቀበለዉም ሲሉ ኢትዮጵያ የባህር በርን በሶማሊላንድ በኩል አታገኝም ለማለት ሞክረዋል። ሶማሊያ ሉዓላዊነቷን ለማስጠበቅ እንደምትሰራ ገልጸዉ የምታላላዉ አቋም እንደሌላትም አሳስበዋል።

ሶማሊያ ድንበሯን እንደምታስጠብቅ የገለጹት የዉጪ ጉዳይ ሚኒስትሩ ፥ ሀገራዊ አንድነቷንም ለማረጋገጥ መንግስታቸዉ እንደሚሰራ ባወጡት መግለጫ ተናግረዋል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
መንግሥት እና ፋኖን ለማቀራረብ የሚጥረው የሰላም ካውንስል “ውጤት ማምጣት አልቻልኩም” አለ‼️

በአማራ ክልል በመንግሥት ኃይሎች እና በፋኖ  መካከል እየተካሄደ አንድ ዓመት የሆነውን ውጊያ በንግግር ለማስቆም በሚል ዓላማ የተቋቋመው የሰላም ካውንስል እንቅፋቶች እንደገጠሙት አስታወቀ።

ሁለቱ ወገኖች ለንግግር እንዲቀመጡ ለማመቻቸት እያደረገው ባለው ጥረት በተለይም የፋኖ አደረጃጀት ወጥ አለመሆን ለሚያደርጉት ጥረት ፈተና እንደሆነ የካውንስሉ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ እያቸው ተሻለ ለቢቢሲ ተናግረዋል።

“ከአንዱ አዎንታዊ [ምልሽ] ሲገኝ፤ ከሌላኛው አሉታዊ ይሆናል። . . . አንደኛው ጋር ጥሩ ነገር ሲገኝ ሌላኛው ጋር ደግሞ ተቃራኒ መግለጫ ሲሰጥ ይሰማል” ያሉት ኃላፊው፤ ወጥ አደረጃጀት አለመኖር የፋኖ ኃይሎች ለድርድር እንዲቀመጡ ለማመቻቸት እንቅፋት ሆኗል ብለዋል።

ምናልባት ድርድር መባሉን ተከትሎ [የፋኖ ኃይሎች] በፍጥነት ወደ ድርድር ይመጣሉ የሚል ተስፋ አድርገን ነበር። በእርግጥ አሁንም ቢሆን ሁለት ወደሚመስል አደረጃጀት ለመምጣት እሞከሩ ነው” በማለት አሁንም ተስፋቸው እንዳልተሟጠጠ ተናግረዋል።

Via BBB
@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
"የኢትዮጵያ ህዝብና ክብርት ፕሬዝዳንትን ይቅርታ መጠየቅ እፈልጋለሁ" አሰልጣኝ ገመዶ ደደፎ

አሰልጣኝ ገመዱ ደደፎ የተሰጠውን የሁለት ሚልዮን ብር ሽልማት ያልተቀበልኩት “ ለሙያው የተሰጠው ክብር አነስተኛ በመሆኑ ነው “ ሲል ተናግሯል።
"ለአሰልጣኝ የሚሰጠው ክብር አነሰተኛ ነው" ያለው አሰልጣኙ "እኛ የብር ችግር የለብንም ፤ ለእኔ ከ ገንዘቡ ስሙ ይሻለኛል እንደ ታምራት ኒሻኑን ቢሰጡኝ በቂ ነበር" ብሏል።

"የሰው ልጅ ይሳሳታል" ያለው አሰልጣኝ ገመዶ ደደፎ " በብዙ ችግሮች የመጣው ነገር ስሜታዊ አድርጎኝ ነው” ብሏል።

“ የኢትዮጵያን ህዝብ እና ክብርት ፕሬዝዳንትን ይቅርታ መጠየቅ እፈልጋለሁ" በማለትም ተናግሯል።
አሰልጣኙ በመጨረሻም አሁንም ቢሆን ነገሮች ካልተስተካከሉ ሁለት ሚልዮን ብሩን እንደማይቀበል ሲገልጽ ነገሮች ከተስተካከሉ ሽልማቱን እንደሚቀበል ተናግሯል።

© ሸገር ስፖርት ሬዲዮ

@ethio_mereja_news
አንድ የእርዳታ ድርጅት ሰራተኛ በሰሜን ወሎ ዞን ዳውንት ወረዳ ለገንዘብ ተብሎ ከታገተ በኋላ ግድያ እንደተፈፀመበት ታወቀ

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የእርዳታ ማስተባበርያ ቢሮ አንድ የሰብአዊ እርዳታ ድርጅት ሰራተኛ በሰሜን ወሎ ዞን ዳውንት ወረዳ ለገንዘብ ተብሎ ከታገተ በኋላ ግድያ እንደተፈፀመበት ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስታወቀ።

ቢሮው ባወጣው በዚህ መግለጫው ያሬድ መለሰ የተባለ Action for Social Development and Environmental Protection Organization (ASDEPO) በሚባል ድርጅት የሚሰራ ግለሰብ ገንዘብ በጠየቁ ታጣቂች ከታገተ በኋላ ግድያ ተፈፅሞበታል።

"በስራ ባልደረባችን ያሬድ ላይ ወንጀለኞች የፈፀመትን ይህን ግድያ አጥብቀን እናወግዛለን። የምገባ ስርዐት ባለሙያ የነበረው ያሬድ ጠንካራ እና ስራውን የሚወድ የሰብአዊ ድርጅት ሰራተኛ ነበር" ያሉት የቢሮው የኢትዮጵያ አስተባባሪ ራሚዝ አላክባሮቭ ማንኛውም ጥቃት፣ ማስፈራርያ እና ዝርፊያ ተቀባይነት የሌላቸው ድርጊቶች ናቸው ብለዋል።

የአሁኑ ጥቃትን ጨምሮ በያዝነው የፈረንጆች አመት ብቻ ስምንት የሰብአዊ ድርጅቶች ሰራተኞች ኢትዮጵያ ውስጥ መገደላቸው ታውቋል፣ ከዚህም ውስጥ አብዛኛው በማዕከላዊ እና ሰሜን ጎንደር የተፈፀመ መሆኑ ተመላክቷል።

በተያያዘ ዜና የአለም ምግብ ፕሮግራም የእርዳታ ምግብ የጫኑ ሁለት ተሽከርካሪዎቹ በኦሮሚያ ክልል በሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች እንደተቃጠሉበት እንዲሁም በጎንደር እና ባህር ዳር መስመር ሲጓዝ የነበረ አንድ የድርጅቱ ተሽከርካሪ ላይ በቅርቡ በተፈፀመ ጥቃት ምክንያት የተመድ ሰራተኞች በመስመሩ እንቅስቃሴ ማድረግ ማቆማቸውን መሠረት ሚድያ ከሰአታት በፊት ዘግቦ ነበር።


ከመሠረት ሚድያ የተወሰደ
በእጅዎ ያለው ጥሬ ገንዘብ ዋጋ እያጣብኝ ነው ብለው ተጨንቀዎል?
የብር ዋጋ መቀነስ ወይም የዶላር ጭማሪ ሳያሳስብዎ የሚፈልጉትን ቤት ከ ዲኤምሲ ሪልስቴት ያግኙ

ዲኤምሲ ወቅቱን ባገናዘበ በከፍተኛ ዋጋ ቅናሽ ጥራታቸውን የጠበቁ ቤቶችን በተለያዩ ካሬ አማራጮች አቅርቦሎታል

በእጆ የያዙት ብር ዋጋ ከማጣቱ በፊት በቋሚ ንብረት ይቀይሩት።
  -በ10% ቅድመ ክፍያ
  -50/50 የብድር አማራጭ
  -ከ8-25% ቅናሽ
  -ከስቱዲዮ እስከ ባለ 4 መኝታ ቤቶች እና ከተጨማሪ የሰራተኛ ክፍልና መታጠቢያ ጋር
❇️ለበለጠ መረጃ 0977190118 ይደውሉ
ለስድስት ወራት ደብዛቸው ጠፍቶ የነበረው የአማራ ክልል ምክር ቤት አባል፤ ተይዘው ከቆዩበት ተለቀቁ!

ከስድስት ወራት በፊት “ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች ታፍነው” መወሰዳቸው የተነገረላቸው የአማራ ክልል ምክር ቤት አባል አቶ ሀብታሙ በላይነህ፤ ትላንት ማክሰኞ ነሐሴ 7፤ 2016 መለቀቃቸውን ቤተሰቦቻቸው ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ገለጹ። የአቶ ሀብታሙን ጉዳይ ሲከታተል የቆየው የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ)፤ የግለሰቡን መለቀቅ አረጋግጧል።

አቶ ሀብታሙ የአማራ ክልል ምክር ቤትን የተቀላቀሉት፤ በምዕራብ ጎጃም ዞን ከምትገኘው ቋሪት ወረዳ ተመርጠው ነው። በሰኔ 2013 ዓ.ም. በተካሄደው ምርጫ፤ እንደ እርሳቸው ሁሉ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄን (አብን) የወከሉ ሌሎች ሁለት ተወዳዳሪዎች ከቋሪት የምርጫ ክልል ተመርጠው የምክር ቤቱ አባል ሆነዋል።

አሁን በእስር ላይ የሚገኙት የቀድሞውን የአብን አመራር አቶ ክርስቲያን ታደለም ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተመረጡት፤ ከቋሪት የምርጫ ክልል ነው። የአብን የማዕከላዊ ኮሚቴ አባል የነበሩት አቶ ሀብታሙ፤ ደብዛቸው የጠፋው ከየካቲት 22፤ 2016 ጀምሮ እንደሆነ ለእርሳቸው ቅርበት ያላቸው አንድ ምንጭ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል።

በዕለቱ በአዲስ አበባ ከተማ አራት ኪሎ አካባቢ “ሰው ላግኝ ብሎ ከቤት እንደወጣ አልተመለሰም” የሚሉት እኚሁ ምንጭ፤ ከዚያን ጊዜ አንስቶ ለስድስት ወራት ያህል አቶ ሀብታሙ ያሉበት ሳይታወቅ መቆየቱን አስረድተዋል። ብሔራዊው የሰብአዊ መብቶች ተቋም ኢሰመኮ ባለፈው ግንቦት ወር መጨረሻ ባወጣው አንድ መግለጫ፤ አቶ ሀብታሙ ከየካቲት ወር መጨረሻ ጀምሮ “የት እንዳሉ እንደማይታወቅ” በተመሳሳይ አስታውቆ ነበር።

[Ethiopian Insider]

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
2024/10/01 15:39:41
Back to Top
HTML Embed Code: