Telegram Web Link
የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በጎፋ ዞን በመሬት መንሸራተት አደጋ ለተፈናቀሉ ዜጎች የ5 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረገ

የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በጎፋ ዞን በድንገተኛ የመሬት መንሸራተት አደጋ ለተፈናቀሉ ዜጎች ድጋፍ የሚውል የ5 ሚሊዮን ብር ድጋፍ በዛሬው እለት አሰረክቧል፡፡

የገንዘብ ድጋፉን የኮርፖሬሽኑ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ኃይለብርሀን ዜና በቦታው በመገኘት አስረክበዋል፡፡ አቶ ኃይለብሀን ዜና በወገኖቻችን ላይ በደረሰው ድንገተኛ አደጋ የኮርፖሬሽኑ አመራሮችና ሠራተኞችን ማዘናቸውን ገልጸዋል፡፡

ኮርፖሬሽኑ በመላ አገሪቱ የሚከሰቱ ሰው ሠራሽ እና ተፍጥሯዊ አደጋዎች ምክንያት ጉዳት ለደረሰባው ወገኖች የገንዘብ ድጋፍ ሲያደርግ መቆቱን አስተውሰው በ6 ዓመታት ብቻ ኮርፖሬሽኑ ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት ታሳቢ በማድረግ ያደረገው ድጋፍ ግማሽ ቢሊየን ብር መሻገሩን ተናግረዋል፡፡

በጎፋ ዞን በድንገተኛ የመሬት መንሸራተት አደጋ ለተፈናቀሉ ዜጎች መልሶ ለማቋቋም እየተደረገ ያለውን አንቅስቃሴ መደገፉን አጠናክሮ ይቀጥላልም ነው ያሉት አቶ ኃለብርኃን ዜና ፡፡

የጎፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ኢንጂነር ዳግማዊ አየለ በበኩላቸው ከፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ለተደረገው የገንዘብ ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበው ፣ ድጋፉ በአደጋው ለተጎዱ እና የተፈናቀሉ ወገኖችን መልሶ ለማቋቋም የሚደረገውን ጥረት የሚያግዝ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡

በአደጋው ለተጎዱና ለተፈናቀሉ ወገኖች ተገቢው የሆነ ሰብዓዊ ድጋፍ እየተደረገ እንደሆነ ጠቁመው ተፈናቃዮችን ከአደጋ ስጋት ነጻ ወደ ሆነ ቦታ የማስፈር ሥራ እየተሰራ እንደሆም ገልጸዋል፡፡
ኮርፖሬሽኑ ያደረገው የገንዘብ ድጋፍም ለመልሶ ማቋቋም ሥራው ትልቅ አጋዥ እንደሆነም ተናግረዋል፡፡

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
Dogs‼️

Dogs ያልጀመራቹ ብዙዎች መቆጨታቹ አይቀርም እያሉ ነው

ስለዚ ጀምሩ ያልጀመራቹ 👇👇

https://www.tg-me.com/dogshouse_bot/join?startapp=qA4t5KguQWKX0tWVVEhxSQ

https://www.tg-me.com/dogshouse_bot/join?startapp=qA4t5KguQWKX0tWVVEhxSQ
በአማራ ክልል በደቡብ ወሎ ዞን በኮምቦልቻ ከተማ ዛሬ ጠዋት ልዩ ስሙ ዶሮ እርባታ አካባቢ አንድ ግለሰብ ውሻ አርዶ በመግፈፍ ላይ እያለ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሉን ጥቆማዎች ደርሰውኛል።

ከዚህ በፊት የውሻ ስጋን ወደ ሽያጭ ሲያወጣ እንደነበር ከግለሰቡ ቃል ለመገንዘብ ተችሏል ሲሉ ምንጮች ገልጸዋል።(ayu)

@ethio_mereja_news
የ 5000ሜ ወንዶች ፍፃሜ ውድድር ከጀመረ 5 ያህል ደቂቃዎች አልፈውታል

ሀገራችን ኢትዮጵያ በርቀቱ

🇪🇹 በአትሌት ሀጎስ ገብረ ህይወት
🇪🇹 በአትሌት አዲሱ ይሁኔ
🇪🇹 በአትሌት ቢኒያም መሀሪ ተወክላለች።

መልካም እድል ለአትሌቶቻችን 🇪🇹
ሜዳሊያ ውስጥ አልገባንም።

ኢትዮጵያ በ 5000ሜ የፍፃሜ ውድድር ሜዳሊያ ማግኘት አልቻለችም።

ጆኮብ ኢንግብርስቴን ለኖርዌይ የወርቅ ሜዳሊያ ሲያስገኝ ኬንያ ብር እንዲሁ አሜሪካ ነሐስ አግኝተዋል።

5ኛ ሀጎስ ገብረ ሂወት
6ኛ ቢንያም መሀሪ
14ኛ አዲስ ይሁኔ በመሆን ውድድራቸውን አጠናቀዋል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
በድጋሚ አሁን በተደረገው የሴቶች 1500ሜትር ፍፃሜ የሜዳሊያ ሰንጠዥ ውስጥ መግባት እንዳማረን ቀርቷል።

@ethio_mereja_news
ህውሀት‼️

ህወሓት ህጋዊ ሰውነቴ እንዲመለስ እንጂ በአዲሱ አዋጅ በልዩ ሁኔታ መመዝገቡን አልቀበልም ብሏል‼️

ሙሉ መግለጫው👇

"የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ከህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) በሀምሌ 19 ቀን 2016 ዓ.ም የቀረበለትን የተሰረዘውን የህወሓት ህጋዊ ሰውነት ወደ ነበረበት የመመለስ ጥያቄ ተከትሎ በነሓሴ 03 ቀን 2016 ዓ.ም ለህወሓት የፖለቲካ ፓርቲዎች በልዩ ሁኔታ ሲመዘገቡ የሚሰጥ የህጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት” እና ”ህወሓት በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ስነ ምግባር አዋጅን ለማሻሻል በወጣው አዋጅ ቁጥር 1332/2016 መሰረት በልዩ ሁኔታ የተመዘገበ መሆኑን ስለማሳወቅ” የሚል አርእስት የተሰጠውን በቁጥር አ1162/11/15180 የተፃፈ ህወሓት ስላቀረበው ጥያቄና ቦርዱ የሰጠውን ውሳኔ የያዘ ደብዳቤ ደርሶናል።

በዚህ መሰረት፤ ህወሓት ያቀረበው ጥያቄ በቦርዱ ውሳኔም በግልፅ እንደተቀመጠው ከፕሪቶሪያው ስምምነት፣ ከህግ እና ህወሓት እያደረገ ካለው ተጨባጭ እንቅስቃሴ አንፃር የተሰረዘውን ህጋዊ ሰውነታችን ወደነበረበት እንዲመለስልን የሚል ብቻ ነው። የህወሓት ማእከላዊ ኮሚቴ ከዚህ በፊት የህወሓት ህጋዊ ሰውነት ወደ ነበረበት ስለመመለስ እና ለዚህ ጉዳይ መፍትሄ ተብሎ በፌደራል መንግስት የቀረበውን አዋጅ ቁጥር 1162/2011 የሚያሻሽል አዲስ አዋጅ ይዘት አስመልክቶ ውይይት በማድረግ አዋጁ የህወሓትን ህጋዊ ሰውነት እንደማይመልስ በመገንዘብ ከሚመለከታቸው የፌደራል አካላት ጋር ውይይት እንዲደረግ ወስኗል።

በዚህ መሰረት የህወሓት የስራ ሀላፊዎች ከክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩና ከሚመለከታቸው የፌደራል መንግስት የስራ ሀላፊዎች ጋር ተደጋጋሚ ውይይቶችን በማካሄድ የህወሓት ሕጋዊ ሰውነት እንዲመለስ መግባባት ላይ ተደርሷል። በአፍሪካ ህብረት ፓነል ውይይትም ይህ ጉዳይ ተነስቶ ህጋዊ ሰውነቱ መመለስ እንዳለበት ስምምነት ተደርሶበታል። ይህንን ተከትሎም ህወሓት ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ህጋዊ ሰውነቱን ወደነበረበት እንዲመለስለት ብቻ በሀምሌ 19 ቀን 2016 ዓ.ም ጥያቄ አቅርቧል።

ሆኖም ቦርዱ የፕሪቶሪያውን ስምምነት፣ ከዚህ በፊት በሌሎች የፌደራል ተቋማት የተሰጡትን ውሳኔዎች፣ ሌሎች ህጎች እና ከጠቅላይ ሚኒስትሩ የተደረሱ መግባባቶች ወደጎን በመተው ጥያቄውን ”በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ስነ ምግባር አዋጅን ለማሻሻል በወጣው አዋጅ” መልሷል። ከዚህ የተነሳም ጥያቄው ሌላ መልሱ ሌላ ሆነዋል።

ከዚህ ባሻገር፤
1) ምንም እንኳን ቦርዱ የህወሓት ጥያቄ ህጋዊ ሰውነት መመለስ ብቻ እንደሆነ በግልፅ ያስቀመጠ ቢሆንም ከህወሓት ጥያቄ እና እውቅና ውጪ በፍትህ ሚኒስቴር የተፃፈውን ደብዳቤ በአባሪነትና መነሻነት ጠቅሷል።

2) ህወሓት ባቀረበው ማመልከቻ ላይ በማሻሻያ አዋጁ አንቀፅ 2(2) ላይ የተቀመጡትን መቅረብ አለባቸው ተብለው የተቀመጡትን ዝርዝሮች በማሻሻያ አዋጁ መሰረት እንደቀረቡ ገልጿል። ሆኖም የፍትህ ሚኒስቴሩ ደብዳቤ ከፍ ብሎም እንደተገለፀው በህወሓት በኩል ምንም ዐይነት ጥያቄ ሳይቀርብና ከህወሓት እውቅና ውጪ የተፃፈ ነው። በይዘቱም ህወሓት አይስማማም። በህወሓት የቀረበውን ማመልከቻ እና አባሪዎቹ የሚመለከትም ህወሓት የተሰረዘውን ህጋዊ ሰውነቱ ወደነበረበት እንዲመለስ የሚያግዙ ሰነዶች ማለትም የፓርቲው ፕሮግራም፣ መተዳደሪያ ደንብ እና የጠቅላላ አመራሮቹ ዝርዝር የያዘ ሰነድ እንጅ በማሻሻያ አዋጁ መሰረት እንዲሁም አዋጅ ቁጥር 1162/2011 ዐንቀፅ 2(14) መሰረት የስራ አስፈፃሚ አባላት ስም፣ አድራሻ እና በተለየ ሁኔታ ሀላፊነት ወስደው ቃል የሚገቡበትን የተፈረመ ሰነድ ለቦርዱ አላቀረበም።

በነበረው ሂደት ቦርዱ በአዲሱ ማሻሻያ ህግ መንፈስ የራሱ ፎርም አዘጋጅቶ የህወሓት ስራ አስፈፃሚ አባላት ስም፣ ፌርማ፣ አድራሻ ሞልተው ሀላፊት ወስደው እንደሚሰሩ የሚገልፅ ሰነድ እንዲቀርብለት ጠይቆ በህወሓት በኩል ከማመልከቻው የሚጣጣም ሰነድ ካልሆነ በስተቀር በአዲሱ ህግ ወይም ቦርዱ ባቀረበው ፎርም መሰረት የተለየ ሀላፊነት ወስዶ የሚፈርምበት ምክንያት እንደሌለ ገልፆ ሳይስማማ በመቅረቱ ቦርዱ በቀረበለት ማመልከቻ ብቻ ውሳኔውን እንደሰጠ ይታወቃል።

በአጠቃላይ በቦርዱ ውሳኔ ላይ የተካተቱት ዝርዝር ይዘቶች አዲስ በወጣው ማሻሻያ ህግ መሰረት የተቀመጡና ህወሓት ካቀረበው ጥያቄ ጋር የማይገናኙ ናቸው። ስለሆነም ምንም እንኳን ቦርዱ ህወሓት በልዩ ሁኔታ ተመዝግቧል ቢልም ውሳኔው በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ስነ ምግባር አዋጅን ለማሻሻል በወጣው አዋጅ ቁጥር 1332/2016 መሰረት በልዩ ሁኔታ የተመዘገበ መሆኑን ገልጿል። ስለሆነም ድርጅታችን ህጋዊ ሰውነቱ ወደነበረበት እንዲመለስ ያቀረበውን ጥያቄ የማይመልስ በመሆኑ አልተቀበለውም። ውሳኔው በፕሪቶሪያው ስምምነት ያልተመሰረተ፣ ከዚህ በፊት በሌሎች የፌደራል ተቋማት የተሰጡትን ውሳኔዎች እንዲሁም የነበሩ ውይይቶችን የሚቃረኑ ዝርዝር ይዘቶች በህወሓት ላይ የሚጭን በመሆኑ የቀረበውን ጥያቄ እስኪመለስ ድረስ ህወሓት የፓርቲው ሕገ ደንብ በሚፈቅድለት መልኩ ተያያዥ ስራዎች ያከናውናል። የፌደራል መንግስቱም የማስተካከያ እርምጃ እንዲወስድ ጥሪ ያቀርባል"ሲል በመግለጫው ጠይቋል።

@ethio_mereja_news
ማራቶን‼️

የሴቶች ማራቶን ከተጀመር ትንሽ ቆይቷል።

ሀገራችንን ሶስት ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች ይወክሏታል።

ትዕግስት አለሙ
አማኔ በሬሶ
መገርቱ አለሙ

መልካም ዕድል
#Ethiopia

የሴቶች ማራቶን ሊጠናቀቅ ወደ 2 ኪሎ ሜትር አካባቢ ቀርቶታል።
ኢትዮጵያ በትግስት አሰፋ አማካኝነት በፓሪስ ኦሎምፒክ ሶስተኛውን ብር አግኝታለች።

🥇ሲፋን ሀሰን
🥈ትግስት አሰፋ
🥉ሄለን ኦብሪ

@ethio_mereja_news
ኢትዮጵያ የፓሪስ ውድደሯን ጨርሳለች !

በ 2024 የፓሪስ ኦሎምፒክ የተሳተፈው የ ኢትዮጵያ አትሌቲክስ ልዑክ ቡድን በድምሩ አራት ሜዳሊያዎችን ብቻ በመሰብሰብ ቆይታውን አጠናቋል።

ሜዳሊያ ያስገኙ አትሌቶች :-

🥇 ታምራት ቶላ
🥈 በሪሁ አረጋዊ ፣ ጵጌ ድጉማ እና ትግስት አሰፋ ናቸው።

ሀገራችን አሁን ባለው ወቅታዊ የሜዳሊያ ሰንጠረዥ ከአለም 4️⃣5️⃣ኛ ላይ ትገኛለች።

ቀሪ የኦሎምፒክ ውድድሮች ስላሉ ደረጃው የሚለዋወጥ ይሆናል።

ኢትዮጵያ በተከታታይ ሶስት ኦሎምፒኮች በሪዮ ፣ ቶኪዮ እና ፓሪስ አንድ ወርቅ ብቻ አግኝታለች።

በዘንድሮው የፓሪስ ኦሎምፒክ ኢትዮጵያ ሁለት ሪከርዶቿ ( በቀነኒሳ በቀለ ) እና ( ቲኪ ገላና ) ተይዞ የቆዩ ሪከርዶቹ በዩጋንዳ እና ኔዘርላንድ አትሌቶች ተሰብረዋል።Tikvahsport

@ethio_mereja_news
Dogs ‼️

List ሊደረግ ሶስት ቀን ቀረው።

100% የተረጋገጠና ሌላኛው ኖትኮይን የተባለለት።

Dogs ቢያንስ 5 ሰው ካስገባቹ 20,000 Dogs ማግኘት ትችላላቹ።

በርግጠኝነት ሌላኛው ኖትኮይን ማለት ይቻላል።

ያልጀመራቹ ቶሎ ጀምሩ👇👇

https://www.tg-me.com/dogshouse_bot/join?startapp=zBY7jyJYQW6OF9Sjuhm7mA
መንግሥት ለግል ሠራተኞች የደመወዝ ማስተካከያ እንዲደረግ አቅጣጫ እንዲሰጥ ጥያቄ ቀረበ

የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሠማኮ) መንግሥት ከሰሞኑ ይፋ ያደረገውን የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ተከትሎ ለመንግሥት ሠራተኞች የደመወዝ ማስተካከያ ይደረጋል በተባለው ልክ፣ ለግል ድርጅቶች ሠራተኞችም ማስተካከያ የሚደረግበት አቅጣጫ እንዲሰጥ ጥያቄ አቀረበ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) በቅርቡ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን በተመለከተ በሰጡት ማብራሪያ፣ ለመንግሥት ሠራተኞች አስከ 300 ፐርሰንት የደመወዝ ጭማሪ እንደሚደረግ ገልጸው፣ ለዚህም መንግሥት ለደመወዝ ጭማሪ ከ90 ቢሊዮን ብር በላይ መመደቡን ገልጸው ነበር፡፡

አስተያታቸውን ለሪፖርተር የሰጡት የኢሠማኮ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አያሌው አህመድ፣ በመንግሥት በጀት ለሚተዳደሩት የመንግሥት ሠራተኞች የደመወዝ ማስተካከያ እንደሚደረግ ቢገለጽም፣ የግል ድርጅቶችና ተቋማት በራሳቸው በጀትና ትርፍ የሚንቀሳቀሱ በመሆኑናቸው፣ በትርፋቸው ላይ ተመሥርተው ለሠራተኛ የደመወዝ ማስተካከያ እንዲያደርጉ ከመንግሥት አቅጣጫ እየተጠበቀ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ‹‹የሠራተኞችና የደመወዝ ዝቅተኛው ወለል እንዲወጣ እየወተወትን ነው፤›› ብለዋል፡፡ የመንግሥትና የግል ሠራተኞች አንዱ የተሻለ አንዱ የወደቀ የሚባል ክፍያ ሊኖር አይገባም ብለዋል፡፡

‹‹መንግሥት ጉዳዩን ሊዘነጋው አይችልም የሚል እምነት ቢኖረንም፣ መሰል አገራዊ አጋጣሚዎችና ቀውሶች በሚኖሩበት ጊዜ ባለሀብቶችንና ተቋማትን የሚመለከቱ ማሻሻያዎች በማድረግና ውይይቶች በማካሄድ አቅጣጫዎች ሊሰጡበት ይገባል፤›› ብለዋል፡፡ ‹‹ይህ የማይሆን ከሆነ ግን ለአገርም አይጠቅምም፣ የኢንዱስትሪ ሰላም አይኖርም፣ ሠራተኛውም ተረጋግቶ ሥራውን ማከናወን አይችልም፤›› ያሉት አቶ አያሌው፣ ጉዳዩ በጣም አሳሳቢ ስለሆነ መንግሥት አቅጣጫ የማይሰጥበት ከሆነ ኢሠማኮ ጥያቄውን በጽሑፍ ለመንግሥት ያቀርባል፤›› በማለት አስረድተዋል፡፡

‹‹ሠራተኛው በከፍተኛ የኑሮ ውድነት ምክንያት በልቶ ማደር አልቻለም፣ የኑሮ ውድነቱን መቋቋም አልቻለም፣ ይህን ማንም ያውቀዋል ሚስጥር አይደለም፣ አሠሪዎቹ ለሚያሠሯቸው ዜጎች ተመጣጣኝ የሆነ ክፍያ መክፈል አለባቸው፤›› ብለዋል፡፡

የሠራተኛ መብት መከበር እንዳለበት ‹‹የሚያረጋግጥ ወጥ የሆነ ሕግ ያስፈልጋል›› ያሉት አቶ አያሌው፣ የሠራተኞች ዝቅተኛ የደመወዝ ወለልና ሌሎች የሠራተኞች መብቶችና ጥቅማ ጥቅሞች ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን መንግሥት ለምን እንዳዘገያቸው አልገባኝም፤›› ሲሉም አክለዋል፡፡

የዝቅተኛ የደመወዝ ወለል ጉዳይ ላይ አሁንም መንግሥት የዘነጋው ይመስላል ያሉት ምክትል ፕሬዚዳንቱ፣ ኢሠማኮ ተጨማሪ ጥያቄ ሊያቀርብ እንደሚችል ተናግረዋል፡፡

አክለውም ከመንግሥት ተቋማት በተሻለ የሚያተርፉት የግል ተቋማት፣ ከመንግሥት የደመወዝ ጭማሪ ጋር እኩል ላለመጨመር ትልቁ ችግር የአስተሳሰብ ጉዳይ እንጂ፣ የገንዘብ እጥረት አይደለም በማለት ለዜጎች ማዘን እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡  ለራስ ብቻ ከማግበስበስ ዕሳቤ በመውጣት ምርታማ ሠራተኛን ለማፍራት፣ አሁን  ተመጣጣኝ የደመወዝ ጭማሪ ማድረግ ብዙ ነው የሚያሰኝ አለመሆኑን ገልጸዋል፡፡

በዚህ ጉዳይ ላይ ሪፖርተር ያነጋገራቸው የአሠሪዎች ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት አቶ ዳዊት ሞገስ በበኩላቸው፣ ለዋጋ መጨመር አንዱ ምክንያት የደመወዝ ጭማሪ ነው ይላሉ፡፡ ደመወዝ ከመጨመሩ በፊት የምርት ማደግ መፍትሔ መሆኑን የተናገሩት ፕሬዚዳንቱ፣ ለሠራተኛ 300 ፐርሰንት እንዲጨመር ከተፈለገ ምርታማነቱ በዚያው ልክ ማደግ አለበት ብለዋል፡፡ ለሠራተኛ ደመወዝ መጨመር እሰየው የሚያስብል ቢሆንም፣ ምርታማነት ዝቅተኛ ከሆነባቸው አገሮች መካከል አንዷ በሆነችው ኢትዮጵያ ከመንግሥት ጋር እኩል 300 ፐርሰንት ደመወዝ ጭማሪ አድርጉ ማለት ይከብዳል ብለዋል፡፡

በጉዳዩ ላይ በአሠሪዎች ዘንድ የታሰበ ነገር ባይኖርም ሠራተኛው ሥራ ጥሎ እንዳይሄድ ምን እናደርግ የሚል ውይይት መጀመሩን ጠቅሰው፣ ደመወዝ ቢጨምር የባሱ ችግሮች ሊፈጠሩ ስለሚችሉ መጠንቀቅ ያስፈልጋል  ሲሉ ተናግረዋል፡፡

‹‹በቀጣይ ሠራተኞች ደመወዝ ይሻሻል ብለው መጠየቃቸው አይቀርም፡፡ ያለውን ነባራዊ ሁኔታ ግምት ውስጥ በማስገባትና ጥናት በማድረግ ጥንቃቄ ተደርጎበት ሊሠራ የሚገባ ጉዳይ ነው፤›› ሲሉ አክለዋል፡፡

ሰው በችግር ውስጥ ሆኖ መኖርና መሥራት የለበትም ያሉት ፕሬዚዳንቱ ነገር ግን አንዳንድ የግሉ ዘርፍ አባላት በዋጋ ንረት፣ በዶላር እጥረትና በመሰል ማነቆዎች እየተንገዳገዱ ናቸው ብለዋል፡፡ በመሆኑም በዚህ ችግር ላይ ደመወዝ ጨምሩ ማለት ሊከብድ ቢችልም፣  ምናልባት የመንግሥት የደመወዝ አጨማመር ታይቶ ሊታሰብበት የሚገባ ጉዳይ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

የኢሠማኮ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አያሌው፣ አሠሪዎች ደመወዝ እንጨምር ካሉ ሁለትና ሦስት ሠራተኛ ይሠራው የነበረውን ለአንድ ሠራተኛ በማሸከም፣ ሠራተኛ ወደ መቀነስ ሊገቡ እንደሚችሉ ተናግረዋል፡፡ አቶ ዳዊት ግን፣ ‹‹የመንግሥትን አጨማመር ተመልክተን የምንሄድበት ይሆናል፤›› ብለው፣ ዋናውና መወሰድ ያለበት በየተቋማቱ ባሉ የቢሮክራሲ ማነቆዎች የጉዳይ መጓተት ባለበት ሁኔታ፣ ሥራ በታቀደው ጊዜ ማስኬድ በማይቻልበት ደመወዝ ጨምሩ ማለት አስቸጋሪ ነው ብለዋል፡፡ መንግሥት አምራቹን መደገፍ በሚገባው ልክ አቅጣጫ በመስጠት ድጋፍ ሊያደርግ እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል፡፡
(ሪፖርተር)

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
መቀሌ

" የህዝብ ደህንነት ለመጠበቅ ሲባል ላለልተወሰነ ጊዜ የድጋፍም ይሁን የተቋውሞ ሰልፍ ማድረግ ተከልክሏል " - ሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ

የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር፣ ምክትል ፕሬዜዳንት ሌ/ጀነራል ታደሰ ወረደ ዛሬ ከሰዓት መግለጫ ሰጥተዋል።

በዚህም ፤ " ፓለቲካዊ አለመግባባት ወደ ማንኛውም የፀጥታ አደጋ እንዲሸጋገር አንፈቅድም " ሲሉ አጠንቅቀዋል።

" የህዝብ ደህንነት ለመጠበቅ ሲባል ላለልተወሰነ ጊዜ የድጋፍም ይሁን የተቋውሞ ሰልፍ ማድረግ ተከልክሏል " ያሉት ጀነራል ታደሰ ወረደ " ፓለቲካዊ ልዩነት በሰላማዊ መንገድ ብቻ መፈታት አለበት " ሲሉ ተናግረዋል።

ከዚህ ቀደም ጊዜያዊ አስተዳደሩ ፤ በቀላል እና ከባባድ ወንጀሎች ተሳትፈዋል ያላቸውን ግለሰቦች በቁጥጥር ስር የማዋል ኦፕሬሽን መጀመሩ ይታወሳል።

ሌ/ጄነራል ታደሰ ወረዳ በዛሬ መግለጫቸው ላይ በህግ ቁጥጥር ስር የዋሉት ግለሰቦችና ብዛታቸውን ባይገልጹም " የህግ የበላይነት ለማስከበር የተጀመረው እርምጃ ተጠናክሮ ይቀጥላል " ሲሉ አሳውወዋል።

የዘንድሮ የአሸንዳ በዓል አከባበርና የህወሓት ጉባኤ ከመካሄድ ጋር ተያይዞ የፀጥታ ችግር እንዳይፈጠር ተገቢ እና ጥብቅ የፀጥታ ስራ ይሰራል ሲሉም ተናግረዋል።

በህወሓት አመራሮች መካከል ያለው ልዩነት እየሰፋ እና እየከረረ መሄዱ በርካቶችን ያሳሰበ ጉዳይ ሆኗል።

ሁኔታው የፀጥታ ስጋት ደቅኗል የሚሉ አልጠፉም።

ሌ/ጄነራል ታደሰ ግን ፓለቲካዊ ልዩነት በሰላማዊ መንገድ ብቻ መፈታት እንዳለበት ፤ ማንኛውም ልዩነት ወደ ፀጥታ አደጋ እንዲሸጋገር የጸጥታ አካሉ እንደማይፈቅድ አጠንቅቀዋል።
(Tikvahethiopia)

@ethio_mereja_news
የኢትዮጵያ እና የሶማሊያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ሁለተኛ ዙር ውይይት ነገ በአንካራ ሊካሄድ ነው

በኢትዮጵያ እና ሶማሊያ መካከል የተፈጠረውን ውጥረት ለመፍታት በቱርክ የተጀመረው ሽምግልና ሁለተኛ ዙር ንግግር ከታቀደለት ጊዜ አስቀድሞ ሊካሄድ ነው። በቱርክ ዋና ከተማ አንካራ በሚካሄደው እና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ታዬ አጽቀሥላሴ እንዲሁም የሶማሊያ አቻቸው አህመድ ሙዓሊም ፊቅ የሚሳተፉበት ውይይት፤ ነገ ሰኞ እንደሚካሄድ ጉዳዩን በቅርብ የሚከታተሉ አንድ የዲፕሎማቲክ የመረጃ ምንጭ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል።

@ethio_mereja_news
#TPLF : " ህወሓትን ለማፍረስ አልሞ በሚካሄደው ጉባኤ አንሳተፍም " ያሉት ምክትል ሊቀመንበሩ አቶ ጌታቸው ረዳ የሚገኙባቸው 14 የማእከላዊ ኮሚቴ አባላት " ጉባኤውን ተከትሎ ለሚመጣው ነገር እኛ የለንበትም " ብለዋል።

ጉባኤው " በጥቂት ቡድኖች ማን አለበኝነት " የተዘጋጀ ፦
- የጉባኤው ከፍተኛ ስልጣን ያለው የማእከላዊ ኮሚቴ አመራር ያልወሰነው
- የድርጅቱ የማእከላዊ የቁጥጥር ኮሚሽን ውድቅ ያደረገው
- ከኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ መግባባት ያልተደረሰበትና
- ትግራይ ከጫፍ አስከ ጫፍ ያልተወከለበት፤ ነጻ ያልወጡ አካባቢዎች ባሉበት ነው ብለዋል።

" ጉባኤው የጠባብ ቡድን ጥቅም ለማስከበር ብቻ ያለመ ነው ፤ እኛ ደግሞ በዚህ ላይ አንሳተፍም " ሲሉ ገልጸዋል።

" ህወሓትን እና የትግራይ ህዝብ ወደ ከፋ አደጋ የሚያጋልጥ ያልተረጋጋ ጉባኤ ማካሄድ የጠባብ ቡድኑ ጥቅምን ከማረጋገጥ ያለፈ እርባና የለውም " ሲሉም ገልጸዋል።

14ቱ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት " ህወሓትን እና የትግራይ ህዝብ ወደ ሌላ የተወሳሰበ ቀውስ በሚከት በጠባብ ቡድን የተዘጋጀው ጉባኤ አንሳተም " ብለው " ጉባኤውን ተከትሎ ለሚፈጠረው ማንኛውም ነገር ተጠያቂው ይኸው ቡድን መሆኑ እናስታውቃለን " ብለዋል።

አቶ ጌታቸው ረዳ ያሉበት 14 የማእከላዊ ኮሚቴ አባላት " ጠባብ ቡድን " እያሉ የገለጻቸውን ጥቂት ቡድኖች በስም አልገለጿቸውም።

#Tikvah

@ethio_mereja_news
2024/09/30 09:37:38
Back to Top
HTML Embed Code: