Telegram Web Link
ግጭት ባለባቸው የአማራ ክልል አካባቢዎች ለኹለት ወገን ግብር እንዲከፍሉ የተገደዱ አርሶ አደሮች “ግብር ካልከፈላችሁ ማዳበሪያ አታገኙም” እንደተባሉ ለዋዜማ ተናግረዋል።

ኾኖም ድጋሚ ለመንግሥት ግብር ከፍለው ማዳበሪያ ለማግኘት የጠየቁ አርሶ አደሮች፣ ግብሩን የሚሰበስብ አካል እንዳላገኙ ገልጸዋል።

አንዳንድ አርሶ አደሮች መንግሥት 4 ሺህ 200 ብር የሚሸጠውን ማዳበሪያ ከአጎራባች አካባቢዎች በ8 ሺህ 800 ብር  ከነጋዴ በውድ ዋጋ እየገዙ መኾኑን ጠቁመዋል።

የክልሉ ግብርና ቢሮ ስለ አርሶ አደሮቹ ቅሬታ ተጠይቆ፣ እንደዚያ ዓይነት ኹኔታ ሊያጋጥም እንደሚችል ጠቅሶ፣ ግብር ካልከፈላችሁ ማዳበሪያ አታገኙም ማለት ግን ስህተት እንደኾነና በጉዳዩ ላይ መመሪያ አስተላልፎ እንደነበር ለዋዜማ ገልጧል።

ማዳበሪያ በነጋዴዎች እጅ መግባቱን በተመለከተ፣ ለችግሩ ተጠያቂው የክልሉ ጸጥታ ኃይል እንደኾነ ቢሮው ተናግሯል።
(Wazema)

@ethio_mereja_news
የተሽከርካሪ ሰሌዳ እና የአሽከርካሪ መንጃ ፍቃድ ሊቀየር መሆኑ ተሰምቷል።

✔️አዲሱ ታርጋ የክልል ስምና ኮድ አይኖረውም።

✔️በቀለምና በስቲከር ብቻ ይለያል ተብሏል።

✔️መንጃ ፍቃድ ABC በማለት ደረጃ ይኖረዋል።

✔️ የህዝብ፣አውቶ፣ደረቅ የሚሉ የድሮ ደረጃዎች በአዲሱ ይተካሉ ተብሏል።(wasu)

@ethio_mereja_news
TapSwap‼️

ታፕስዋፖች በቅርቡ ትልቅ ዜና ጠብቁ ብለዋል ያም ዜና አዲሱን ሌላኛውን ዋጋ ይፋ የሚያደርጉበት ኤክስቼንጅ መሆኑን ነው የገለፁት ።

አሁን ላይ በቴሌግራም ከተጀመሩ ኤርድሮፖች Hamster ፣ TapSwap ፣ Yes coin እና pixel Verse በቶን ብሎክቼይን ዋጋቸው ይፋ እንደሚደረግ የገለፁ ሲሆን ከቶን ብሎክቼይን ውጪ በሌላ ብሎክቼይን ወይም ኤክስቼንጅ ዋጋቸው ይፋ እንደሚደረግ ግን አንዳቸውም አልገለፁም ነበር

ያልጀመራቹ አሁንም ጊዜ አላቹ ባጭር ጊዜ ውስጥ ከ10 M በላይ መስራት ትችላላቹ።

በዚ ሊንክ ጀምሩ👇👇
https://www.tg-me.com/tapswap_mirror_2_bot?start=r_769729488
https://www.tg-me.com/tapswap_mirror_2_bot?start=r_769729488


ዝርዝር መረጃ ከፈለጋቹ ይህንን ቻናል ተቀላቀሉ👇👇
http://www.tg-me.com/sheger_crypto
http://www.tg-me.com/sheger_crypto
ኢትዮጵያ ስለ አንካራው ውይይት ማብራሪያ ሰጥታለች

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በአንካራው ውይይት ጉዳይ የፕሬስ መግለጫ አውጥቷል።

በመግለጫው በቱርኪዬ ሪፐብሊክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሀካን ፊዳን ጋባዥነት የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ እና የሶማሊያ የውጭ ጉዳይና ዓለምአቀፍ ትብብር ሚኒስትር አህመድ ሞአሊም ፊቂ ትላንት ሰኔ 24 ቀን 2016 ዓ.ም በአንካራ ተገናኝተው መወያየታቸውን አረጋግጧል።

" በቱርኪዬ መንግስት አመቻቺነት የተካሄደው የሁለቱ ሚኒስትሮች ውይይት በሁለቱ አገራት መካከል ላሉ አለመግባባቶች መፍትሄ ሊያመጡ በሚችሉ ጉዳዮች ላይ ግልፅና ወዳጅነት የተሞላበት የሀሳብ ልውውጥ የተደረገበት ነበር " ብሏል።

ሁለቱ ሚኒስትሮች ያሉ አለመግባባቶችን በሰላማዊ መንገድ እልባት ለመስጠት ቁርጠኝነታቸውን መግለጻቸውን አመልክቷል።

የቱርኪዬ መንግስት ውይይቱን ለማመቻቸት ስለተጫወተው ገንቢ ሚናም ምስጋና እንደቀረበ ገልጿል።

ሁለቱ ሚኒስትሮች መልካም ጉርብትናን እና ቀጠናዊ መረጋጋትን ከግምት በማስገባት መፍትሄዎችን ለማመላከት ያለሙ ምክክሮችን ለመቀጠልም እንደተስማሙ አረጋግጧል።

ሁለቱም ሚኒስትሮች የቱርኪዬ ፕሬዚዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ምከከሩን አገራቸው ለማስተናገድ የወሰዱትን ተነሳሽነት በማድነቅ ሁለተኛ ዙር ውይይታቸውን ነሐሴ 27 ቀን 2016 ዓ.ም በአንካራ ለመቀጠል እንደተስማሙ የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አሳውቋል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
በድሬዳዋ በአሸዋ የገበያ ማዕከል በተነሳ የእሳት አደጋ ንብረት ወደመ

በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር አሸዋ ገበያ ሰልባጅ ተራ ሰፈር በተነሳ የእሳት አደጋ ከፍተኛ የሆነ ንብረት ወድሟል።

ከአካባቢው ምንጮች ባገኘነው መረጃ መሰረት የእሳት አደጋው በሰው ሕይወት ላይ ጉዳት አላደረሰም።

ከስፍራው ተቀርጸው በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ እየተዘዋወሩ ከሚገኙ ተንቀሳቃሽ ምስሎች እንደተመለከትነው አደጋው በንብረት ላይ ከፍተኛ ውድመት አስከትሏል።

አሁን ላይ አደጋውን ሙሉ ለሙሉ መቆጣጠር ተችሏል።

(ሔለን ታደሰ -አዲስ ዋልታ)

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
"የግል ትምህርት ቤት ማን አስተምሩ አላችሁ?"

በግል ትምህርት ቤቶች የሚማሩ የማትሪክ ተፈታኞች በግል ላፕቶፕ ስለምትፈተኑ ላፕቶፕ አዘጋጁ ተብለዋል።

ታድያ ቤተሰቦችን"ላፕቶፕ ቀርቶ ወርሀዊ ክፍያ አቅቶናል" ሲሉ ትምህርት ሚኒስቴር እየሰጣቸው ያለው መልስ "በመንግስት ትምህርት ቤት ለሚማሩት ላፕቶፕ ለማዳረስ እየሰራን ነው፣ የእናንተ ግን አይመለከተንም። የግል ትምህርት ቤት ማን አስተምሩ አላችሁ?" እንደሆነ ከቤተሰቦች በተደጋጋሚ የሚደርሱኝ ጥቆማዎች ያሳያሉ።

በዚህም ምክንያት ላፕቶፕ ለመግዛት ንብረት የሸጠ እንዳለ እንዲሁ ሰምቻለሁ።

ብዙ ኢትዮጵያዊ የግል ትምህርት ቤት ልጆቹን የሚያስተምረው ተርፎት ሳይሆን እሱ ካገኘው የተሻለ ትምህርት ካገኘ በሚል ተቸግሮ ነው።

በዚህ መልኩ የተፈተነ ተቆጥሮ "ይህን ያህል ተማሪ በኦንላይን አስፈተንን" የሚል ሪፖርት ማቅረቡ ፈይዳ ይኖረው ይሆን?
(EliasMeseret)

@sheger_press
ሂውማን ራይትስ ዎች፣ በኤርትራ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ መብት ልዩ ራፖርተር ሞሃመድ አብድልሰላም ባቢከር የቆይታ ጊዜ እንዲራዘም ጠይቋል።

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ መብት ምክር ቤቱ በጉዳዩ ላይ ውሳኔ የሚሰጠው በቀጣዩ ሳምንት ነው። ሩሲያ፣ ኢራን እና የተወሰኑ የምክር ቤቱ አባል አገራት የልዩ ራፖርተሩ የቆይታ ጊዜ እንዳይራዘም እንደሚፈልጉ ድርጅቱ ገልጧል።

የልዩ ራፖርተሩ መቀጠል አኹንም እጅግ አስፈላጊ መኾኑን የጠቀሰው ድርጅቱ፣ የምክር ቤቱ አባል አገራት የኤርትራን የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ሲቪል ማኅበረሰቦች ጥሪ እንዲሰሙና ከጎናቸው እንዲቆሙ ጠይቋል።

ልዩ ራፖርተሩ በቅርቡ ለምክር ቤቱ ባቀረቡት ሪፖርት፣ የኤርትራ መንግሥት አስከፊ የሰብዓዊ መብት አያያዙን ለማሻሻል የወሰደው ርምጃ እንደሌለ ገልጠው ነበር።

@sheger_press
@sheger_press
የአማራ ክልል ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባዔ አማረ ሰጤ፣ የፌደሬሽን ምክር ቤት በአማራ እና ትግራይ ክልሎች የይገባኛል ጥያቄ በሚነሳባቸው አካባቢዎች ላለፉት አራት ዓመታት ለምን የፌደራል ድጎማ ሳይመድብላቸው እንደቀረ ማብራሪያ እንዲሰጥ መጠየቃቸውን ሸገር ሬዲዮ ዘግቧል።

የክልሉ ምክትል አፈ ጉባዔ፣ የማንነትና የአስተዳደር ወሰን በሚነሳባቸው የተወሰኑ አካባቢዎች የመብራት፣ የባንክ፣ የሞባይል ኔትዎርክና ሌሎች አገልግሎቶች እንደተቋረጡ መግለጣቸውን ዘገባው አመልክቷል።

የፌደሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባዔ አገኘው ተሻገር ለጥያቄው በሰጡት ምላሽ፣ የወልቃይት ጠገዴ እና ሌሎች የማንነት ጥያቄዎች የሚነሳባቸውን አካባቢዎች የበጀት ጥያቄ በፌደራል በጀት ቀመር መኾኑ ቀርቶ ገንዘብ ሚንስቴር በበጀት አስተዳደር እንዲያስተናግደው ምክር ቤቱ ለሚንስቴሩ ደብዳቤ እንደጻፈና ጉዳዩን ተከታትሎ ማስፈጸም የክልል መንግሥት ኃላፊነት እንደኾነ መናገራቸውን ዘገባው ጠቅሷል።

@ethio_mereja_news
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ትናንት ከኢምግሬሽን ጋር የተያያዙ ኹለት ረቂቅ አዋጆችን አጽድቋል።

ምክር ቤቱ፣ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎትን እንደገና ለማቋቋም የተዘጋጀውን ረቂቅ አዋጅ በአራት ድምጸ ተዓቅቦ ማጽደቁን ገልጧል።

ረቂቅ አዋጁ የተዘጋጀው፣ ጠንካራ የቅድመ ጉዞ መረጃዎችን በማዘጋጀትና ከአገራት ጋር ውጤታማ የመረጃ ልውውጥ በማድረግ ወንጀለኞችን ለመያዝ የሚያስችል ሥርዓት ለመዘርጋት ነው ተብሏል።

ምክር ቤቱ፣ ኢትዮጵያዊያን ከአገር እንዳይወጡ የማገድ ሥልጣን ለኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የበላይ ኃላፊ የሰጠውን ሌላኛውን ረቂቅ አዋጅም አጽድቆታል።

@ethio_mereja_news
በአማራ ክልል ሥር የተቋቋሙት የጠለምት እና ማይጸብሪ አስተዳደሮች ሙሉ በሙሉ እንደፈረሱና ቢሮዎቻቸው እንደታሸጉ ቢቢሲ አማርኛ የአካባቢውን ምንጮች ጠቅሶ ዘግቧል።

በጦርነቱ ከአካባቢዎቹ የተፈናቀሉ ነዋሪዎች ወደ ቀያቸው በመመለስ ላይ እንደኾኑም ዘገባው ገልጧል።

ሰሞኑን የፈረሱት ጊዜያዊ አስተዳደሮች፣ የምሥራቅ ጠለምት ወረዳ፣ የምዕራብ ጠለምት ወረዳ እንዲኹም የማይጸብሪ ከተማ ተብለው በሰሜን ጎንደር ዞን ሥር የተዋቀሩ አስተዳደሮች ናቸው።

መዋቅሮቹ የፈረሱት፣ ከአማራ ክልል መንግሥትና ከፌደራሉ መንግሥት ተወካዮች ጋር ውይይት ከተደረገ በኋላ መኾኑንና የፖሊስና ሚሊሻ አባላትም ከቅዳሜ ጀምሮ እንዲወጡ እንደተደረገ መስማቱን ዘገባው አመልክቷል።

@ethio_mereja_news
"ጥላቻ፣ ጦርነት፣ ጠብ፣ ክርክር፣ ሞኝ መሆኑን፡ እያወቅን እዚያ ላይ እንንከባለላለን። የሰው ልጅ ህልውናውን ለመጠበቅ ሰላምን መምረጥና መከተል ይኖርበታል። የሰላምን እጦት ያመጣነው ራሳችን ነን። ማንም አምጥቶ አልጫነብንም።ሰላም ከሌለ መንፈሳዊም ሆነ ዓለማዊ ተቋማት ምንም መሰራት እንደማይችሉ አውቀን ለሰላም በአንድነት መቆምና ሰላምን መከተል ይኖርብናል።

ለዚህም ሁላችንም ከቀደመው እየተማርን መጪውን ሰላማዊ ለማድረግ መጣር ይኖርብናል።

የሔድንበት መንገድ ጎድቶናል።ስለሆነም ወደ ሰላም፡ እንመለስ ብለን መወሰን አለብን።ለዚህም ሁላችንም ወደ አእምሮችን ተመልሰን ሰላምን እንከተላት።"

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ
ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወክጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት

"የሃይማኖት ተቋሞቻችን ለዘላቂ ሰላማችን"በሚል ርእስ በሸራተን አዲስ ዛሬ በተካሔደው መድረክ ላይ ካስተላለፉት መልዕክት የተወሰደ።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ሹመት‼️

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፥ አቶ ካሳሁን ጎፌን የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር አድርገው ሾሙ።

ወ/ሮ ሽዊት ሻንካን ደግሞ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር አድርገው ሾመዋቸዋል።

የባህልና ስፖርት ሚኒስትር የነበሩት አቶ ቀጀላ መርዳሳ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የወጣቶች እና ስፖርት አማካሪ ሚኒስትር ሆነው ከዛሬ ሰኔ 26 /2016 ዓ/ም ጀምሮ እንደ ተሾሙ ታውቋል፡፡

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
አዳማ‼️

በአዳማ ከተማ በተቀሰቀሰ ተቃውሞ ቢያንስ 7 ሰዎች ተገደሉ

ብጥብጡ የተነሳው በኮሪደር ልማት በተነሳ ተቃውሞ ነው

(ዋዜማ ሬዲዮ)

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
TapSwap‼️

ታፕስዋፕ ትልቅ ፕሮጀክት ነው በቅርብ ቀን List መሆኑ የተረጋገጠ ነው።

ያልጀመራቹ አሁንም ጊዜ አላቹ ባጭር ጊዜ ውስጥ ከ10 M በላይ መስራት ትችላላቹ።

በዚ ሊንክ ጀምሩ👇👇
https://www.tg-me.com/tapswap_mirror_2_bot?start=r_769729488
https://www.tg-me.com/tapswap_mirror_2_bot?start=r_769729488
4 ሕጻናት በደራሽ ውኃ ተወሰዱ!

በምሥራቅ ጉራጌ ዞን ቡኢ ከተማ ከለኪንዶ ወንዝ አራት ሴት ሕጻናት በደራሽ ውኃ መወሰዳቸውን የከተማ አሥተዳደሩ ፖሊስ ጽሕፈት ቤት አስታወቀ፡፡

በውኃ የተወሰዱት ሕጻናት ዕድሜያቸው ከ13 እስከ 15 እንደሚገመት የቡኢ ከተማ አሥተዳደር ፖሊስ ጽ/ቤት አዛዥ ዋና ኢንስፔክተር መለሰ ተሰማ አስታውቀዋል፡፡

ሕጻናቱ ወደ ከለኪንዶ ወንዝ ለጸበል ብለው በሄዱበት ዛሬ ጠዋት በደራሽ ውኃ መወሰዳቸውንም አረጋግጠዋል፡፡

የሁለቱ ሕጻናት አስክሬን መገኘቱን እና የቀሪዎቹን ለማግኘትም ፍለጋው ተጠናክሮ ቀጥሏል ማለታቸውን የቡኢ ከተማ አሥተዳደር ኮሙኒኬሽን ጽሕፈት ቤት መረጃ አመላክቷል፡፡

ወቅቱ ክረምት ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ሕብረተሰቡ ልጆቹን እንዲቆጣጠር እና ጥንቃቄ እንዲያደርግም አሳስበዋል፡፡(Via FBC)

@ethio_mereja_news
አዳማ‼️

በአዳማ ከተማ ከቤት ፈረሳ ጋር በተያያዘ በተፈጠረ ግጭት ነፍሰ ጡርን ጨምሮ 7 ሰዎች መገደላቸው ተሰማ

👉🏼 ቁጥራቸው በዉል ያልታወቁ ሰዎችም ቆስለዋል ተብሏል


በኦሮሚያ ክልል በአዳማ ከተማ አሮሬቲ እና ቶርበን ኦቦ በተባሉ ቀበሌዎች ዛሬ በተቀሰቀሰ ተቃውሞ ላይ የመንግሥት ጸጥታ ኃይሎች በተኮሱት ጥይት አንዲት ነፍሰ ጡርን ጨምሮ 7 ሰዎች እንደተገደሉና ቁጥራቸው ያልታወቁ ሌሎች ሰዎች እንደቆሰሉ ዳጉ ጆርናል ከዋዜማ ዘገባ ተመልክቷል።

ተቃውሞው የተቀሰቀሰው፣ የከተማዋ አስተዳደር 1 ሺሕ 500 ገደማ መኖሪያ ቤቶችን ሕገወጥ ናቸው በማለት ማፍረስ ሲጀምር መኾኑን ነዋሪዎቹ ተናግረዋል። ነዋሪዎቹ፣ መሬቶቹን ከአካባቢው አርሶ አደሮች ገዝተው ከ2005 ዓ፤ም ጀምሮ ለከተማዋ አስተዳደር ግብር ሲከፍሉ መቆየታቸው ገልጸዋል።

ነዋሪዎቹ ቀደም ሲል ለጠቅላይ ሚንስትር ጽሕፈት ቤት ባቀረቡት አቤቱታ መሠረት፣ ጉዳዩ በይደር እንዲታይ ተወስኖላቸው እንደነበርም ዋዜማ ተረድታለች። ዋዜማ በክስተቱ ዙሪያ የከተማዋን አስተዳደር ለማነጋገር ያደረገችው ተደጋጋሚ ጥረት አልተሳካም ስትል ዘግባለች።

@ethio_mereja_news
#HoPR

ዛሬ የህዝብ ተወካዮች ም/ ቤት 36ኛ መደበኛ ስብሰባ እየተካሄደ ይገኛል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) በምክር ቤቱ ተገኝተዋል።

በስብሰባው የ2016 በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት እና በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከምክር ቤቱ አባላት ለሚነሱ ጥያቄዎች ማብራሪያ እና ምላሽ ይሰጣሉ፡፡

በአሁን ሰዓት የምክር ቤት አባላት ጥያቄ እያቀረቡ ናቸው።
የተከበሩ ወ/ሮ ራህመት ለጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ያቀረቡት ጥያቄ

-የፕሪቶሪያዉ የሰላም ስምምነት አፈጻጸም በምን ደረጃ ላይ ይገኛል?

- በአፋር፣ አማራ እና ትግራይ ክልሎች ያሉ የመልሶ ማቋቋም ሂደቶች ምን ላይ ናቸዉ ለቀጣይስ ምን ታስቧል?

የተከበሩ አቶ አቤኔዘር በቀለ ለጠ/ሚኒስትር ዐቢይ ያቀረቡት ጥያቄ

የኑሮ ዉድነቱ ከፍቷል...የመንግስት ሰራተኛዉ መኖር አቅቶታል ፣ መኖር የቅድሚያ ቅድሚያ ሊሰጠዉ የሚገባ ነዉ፥ የኑሮ ዉድነቱን ማረጋጋት አልተቻለም። ስለሆነም እንደመንግስት በቀጣይ አመታት የህዝብን ጥያቄ ለመፍታት ምን ታቅዷል?

@ethio_mereja_news
የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ አባል፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል አቶ አበባው ደሳለው👇

"ከአገራዊ ምክክር በፊት "እምነት መገንባት" ይቀድማል፤መንግስት በህዝብ ዘንድ አመኔታ አልፈጠረም ብለን እናስባለን፤ ለዚህም ማሳያው የሰብዓዊ መብት አያያዝ ነው ሲሉ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) እና የፓርላማ አባሉ ተናግረዋል። በጅምላ የንጹሀን ግድያን ጨምሮ ዘረፋ፣ ውድመት፣ እገታ እና ሌሎችም ወንጀሎችና የመብት ጥሰቶች በአማራ ክልል ተንሰራፍቷል ብለዋል።

በፖለቲካ አመለካከት ልዩነት ሳቢያ ፖለቲከኞች እና ጋዜጠኞች፤ እንዲሁም ዜጎች በማንነት እየተለዩ እየታሰሩ ነው በማለትም የባልደረባቸውን ክርስቲያን ታደለ ጉዳይ በማንሳት የመንግስትን ሀብት ከምዝበራ የመጠበቅ ሀላፊነትን ወስዶ ሲሰራ የቆየን ሰው ለአንድ ዓመት ገደማ በእስር እየማቀቀ ነው ብለዋል።

ከብልጽግና መንግስት ጋር አብረው እየሠሩ የሚገኙ ሰዎችም ስህተት አለ በማለታቸው ታስረዋል፤ ሀብታሙ በላይነህ የተባለው የአብን እና የፌዴሬሽን ምክር ቤት አባልም ለአራት ወራት የት እንዳለ የማይታወቅ በመሆኑ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ምላሽ እንዲሰጡ እንማጸናለን ብለዋል"።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
2024/09/30 23:40:26
Back to Top
HTML Embed Code: