Telegram Web Link
ብልፅግና ፓርቲ ‘የሚዲያ ሠራዊት’ አቋቁሞ በሚቃወሙት እና በሚተቹት ላይ ስም ማጥፋት ዘመቻ እንደሚያካሂድ ተገለጸ‼️

በገዢው ብልፅግና ፓርቲ ‘የሚዲያ ሠራዊት’ የሚል መጠሪያ ያላቸው የፓርቲው አባላት፤ መንግሥትን በሚተቹ እና በሚቃወሙ ግለሰቦች ላይ በፌስቡክ በተደረጉ የሐሰተኛ መረጃ እንዲሁም ‘የጥላቻ ንግግር’ ተብለው ሊቆጠሩ የሚችሉ ጽሑፎች እና ምስሎች ሥርጭት ላይ እንደተሳተፉ ቢቢሲ ባደረገው ምርመራ ማረጋገጡን አስታወቀ።

#የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ሲኖዶስ ዋና ፀሐፊ አቡነ ጴጥሮስ ከአዲስ አበባ ወደ አሜሪካ መጓዛቸውን ተከትሎ በወቅቱ የተሰራጩ መረጃዎችን ቢቢሲ በማሳያነት አቅርቧል።

በቤተክርስቲያኗ እና በገዢው ፓርቲ መካከል የተፈጠረውን ቅራኔ ተከትሎ “ሰበር መረጃ፤ አቡነ ጴጥሮስ ከሀገር ኮበለሉ”፣ “አሜሪካዊው አቡነ ጴጥሮስ ከሀገር ኮብልለዋል!” እና “ከአሜሪካዊ አቡነ ጴጥሮስ ኩብለላ ጀርባ ያሉ እውነታዎች!” የሚል መግቢያ ያላቸው መረጃዎች በወቅቱ ተሰራጭተው እንደነበር አውስቷል።

“ለምንድነው ላይክ፣ ሼር የማታደርጉት?” የሚል ጥያቄ ለተሳታፊዎቹ እንደሚያቀርብ፤ የሚዲያ ሠራዊት አባላት ላክይ፣ ኮሜንት እና ሼር ማድረጋቸውን የሚያሳይ “ስክሪን ሻት” እንዲልኩ እንደሚጠየቁ ቢቢሲ በግሩፑ የተደረጉ የመልዕክት ልውውጦችን ዋቢ በማድረግ አስታውቋል።

መንግስትን የሚቃወሙ ጽሁፎችን ባጋሩ የፌስቡክ ገጾች ላይ ‘የሚዲያ ሠራዊቱ’ አባላት ተዘጋጅቶ የተሰጣቸውን ጽሁፎች ኮሜንት እንደሚያደርጉ አረጋግጫለሁ ብሏል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
🛒ታላቅ ቅናሺ ከሸገር ገበያ📣

✔️m13 Samsung 📱
✔️4ram
✔️64Gb

        ዋጋ 13200

እዚህ ላይ ያናግሩን 👇👇
                  @ethio_sellerr

አዲስአበባ ያሉበት እናደርሳለን 🛵🚵
ክፍለሀገር በፖስታ ይደርሷታል።📩📮
የቻይና ከተሞች እየሰመጡ ነው❗️

ከቻይና ዋና ዋና ከተሞች ግማሽ ያህሉ ላይ የመስመጥ አደጋ መጋረጡ ተሰምቷል።  በበሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች በተለይ የባህር ከፍታ ሲጨምር ለጎርፍ አደጋ እየተጋለጡ ነው ሲል በአገር አቀፍ ደረጃ የወጣው የሳተላይት መረጃ  አመልክቷል። በሳይንስ ጆርናል የታተመው ይኸው ጥናት 45 በመቶው የቻይና የከተማ መሬት በአመት ከ3 ሚሊ ሜትር በላይ በፍጥነት እየሰመጠ ነው ያለ ሲሆን 16 በመቶው ደግሞ በዓመት ከ10 ሚሊ ሜትር በላይ መስመጡን ገልጿል።  በከተሞቹ የሚገኙ በርካታ ሰማይ ጠቀስ ህንፃዎች  ምክንያት መሆናቸውን ሮይተርስ በዘገባው አመልክቷል።

@ethio_mereja_news
ተቀጥተዋል😁

በቤጂንግ ግማሽ ማራቶን ከስፖርት ጨዋነት ባፈነገጠ መልኩ ቻይናዊውን አትሌት ሆን ብለው እንዲያሸንፍ አድርገዋል የተባሉ የኬንያ እና የኢትዮጵያ አትሌቶች ያገኙት ሜዳሊያና የገንዘብ ሽልማት ተነጥቀዋል።

ባልተገባ መንገድ ውድድሩን እንዲያሸንፍ የተደረገው ቻይናዊ አትሌትም ሽልማቱን ተነጥቋል።

ኬንያውያኑ አትሌቶች ዊሊ ምናንጋት እና ሮበርት ኬተር እንዲሁም ኢትዮጵያዊው ደጀኔ ሃይሉ ቢቂላ ማሸነፊያው መስመር ላይ ሆን ብለው ቻይናዊው እንዲያሸንፍ ፍጥነታቸውን ሲገቱ እንደነበር መታየታቸው ተገልጿል፡፡

ባለፈው እሁድ በተካሄደው የግማሽ ማራቶን ሩጫ ውድድር ላይ የተፈፀመውን ያልተገባ ድርጊት የተመለከተው የውድድሩ አዘጋጅ ኮሚቴ ጉዳዩን እየመረመረ መቆየቱን ገልጿል፡፡

ኬንያዊው ምናንጋት መጀመሪያ ላይ የእስያ ጨዋታዎች ሻምፒዮናን እንዲያሸንፍ ያደረገው ጓደኛው በመሆኑ ነው ቢልም፤ ነገር ግን በኋላ ላይ ለማሯሯጥ እንደተቀጠረ ተናግሯል።

ይህንንም ተከትሎ የቤጂንግ ግማሽ ማራቶን ውድድር አዘጋጁ የአሸናፊውን ሂ ጄ እና የሦስቱን አትሌቶች ሜዳሊያና የገንዘብ ሽልማት መንጠቁን ሳውዝ ቻይና ሞርኒንግ ፖስት ዘግቧል፡፡

Via:- FBC

@ethio_mereja_news
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
Who's here? 
We've asked for a free link to a paid channel, for our subs.
x2-x3 Signals here

👉 CLICK HERE TO JOIN 👈
👉 CLICK HERE TO JOIN 👈
👉 CLICK HERE TO JOIN 👈

❗️JOIN FAST! FIRST 1000 SUBS WILL BE ACCEPTED
#Update

የ " ቲክቶክ " እገዳ በኪርጊስታን ተግባራዊ ሆነ።

ኪርጊስታን " ቲክቶክ " በመላ ሀገሪቱ  እንዲታገድ ውሳኔ ማስለፏ ይታወሳል በዚሁ ውሳኔ መሰረት የቴሌኮም አገልግሎት የሚሰጡ ድርጅቶች ትዕዛዙን ወደ መፈጸም #እርምጃ ገብተዋል።

በሀገሪቱ " ቲክቶክ " መስራት እንዳቆመም ተነግሯል።

ሰዎች መተግበሪያውን ሲከፍቱን የሚያገኙት መልዕክት " Unable to load, please try again." የሚል ነው።

ውሳኔው በሀገሪቱ ብሔራዊ ደህንነት መ/ቤት የተላለፈ ነው።

የኪርጊስታን ዲጂታል ሚኒስቴር ቲክቶክን የሚያስተዳድረው ' ባይት ዳንስ ' ኩባንያ ፥ " #የልጆችን
- አእምሯዊ፣
- አካላዊ፣
- መንፈሳዊ እና #ሥነምግባራዊ እድገትን ለመጠበቅ በህግ የተዘረዘሩ ህጋዊ መስፈርቶችን ማክበር አልቻለም " ብሏል።

በዚህም ምክንያት " ቲክቶክ " በሀገሪቱ እንዳይሰራ ተደርጓል።

ውሳኔው የተቃወሙ አካላት ይህ ተገቢ እንዳልሆነ በመግለጽ ገደቡ እንዲነሳ ጠይቀዋል። ከገደብ ይልቅ ቁጥጥር ይደረግበት ብለዋል።

ከዚህ ቀደም የኪርጊስታን የባህል፣ ወጣቶችና ስፖርት ሚኒስቴር ፥ " ቲክቶክ " የተሰኘው መተግበሪያ ለልጆች አእምሯዊ እድገት እና አጠቃላይ ደህንነት ጠንቅ እየሆነ ነው " ማለቱ ይታወሳል።

መተግበሪያው #ህጻናት እጅግ ጎጂ ሊሆኑ የሚችሉ ይዘቶችን እንዳያገኙ ለመከላከል በቂ #መቆጣጠሪያ እንደሌለው ነበር የገለጸው።

በተጨማሪም ለተጠቃሚዎቹ ትክክለኛ የዕድሜ ማረጋገጫ እርምጃዎች እንደለለው እና ተጠቃሚዎችን በአጫጭር የቪዲዮ ክሊፖች ወደ ምናባዊ ግዛት በመሳብ #ሱስ የሚያስይዝ ይዘት እንዳለው አስረድቶ ነበር።

ሚኒስቴሩ " ቲክቶክ " በወጣቱ ትውልድ ደህንነት ላይ አሉታዊ ተጽእኖ እንዳለው በአጠቃላይም ለትውልዱ ጠንቅ እየሆነ እንደመጣ አሳውቆ ነበር።

በሌላ በኩል ፤ አሜሪካ ውስጥ ከመረጃ ደህንነት ጋር በተያያዘ መተግበሪያው እንዲታገድ ከፍተኛ ግፊት እየተደረገ ሲሆን  " ቲክቶክ " ከቻይናው ኩባንያ ካልተፋታ / አሜሪካ የምትቆጣጠረው አይነት ካልሆነ በመላ ሀገሪቱ መታገድ ዕጣ ፋንታ ሊገጥመው ይችላል ተብሏል።

via tikvahethiopia

@merkato_media
This is 100% REAL!  

Ethiopians this service is for you 🔥

We offer you a unique opportunity to open VIP Offshore bank accounts in US Dollars and Euros in Panama.

Enjoy the security of one of the best banking jurisdictions worldwide and get approved by one of the TOP 3 best banks in Panama City!

🍀 Receive your Visa/Mastercard in 2 weeks via FedEx or DHL in Ethiopia or anywhere in Africa.

Book your free call with our experts Today! 📞

Join our Official Channel NOW! ⤵️⤵️⤵️

👉 https://www.tg-me.com/myafricanwealthofficial
👉 https://www.tg-me.com/myafricanwealthofficial
እስራኤል በኢራን ላይ የአጸፋ ጥቃት ሰነዘረች

እስራኤል ከኢራን ለተቃጣባት የሚሳኤልና ድሮን ጥቃቶች የአጸፋ እርምጃ መውሰዷ ተገለጸ።

እስራኤል ኢስፋሃን በተባለ የማዕከላዊ አራን አካባቢ ባሉ ወታደራዊ ካምፖች ላይ በድሮኖች ጥቃት መሰንዘሯ ነው የተጠቀሰው።

ይህን ተከትሎ ኢራን የጸረ-ሚሳኤል መከላከያ ማስወንጨፏንና የተተኮሱባትን ሦስት ድሮኖች መታ መጣሏን አስታውቃለች።

ኢስፋሃን የኢራን አየር ኃይል እና የኒዩክሌር ጣቢያ የሚገኝ ከተማዋ ሲሆን በአካባቢው የተሰማው ፍንዳታ ኢራን ያስወነጨፈቻቸው የጸረ ሚሳኤል መከላከያ መሆኑን አገሪቱ ባወጣችው መረጃ ገልጻለች።

የእስራኤልን ጥቃት ተከትሎ የአየር በረራዎች ተስተጓጉለው እንደነበርና በአሁኑ ሰዓት በረራ መጀመሩን እንዲሁም አካባቢው ወደ ሰላማዊ እንቅስቃሴ መመለሱን የአልጃዚራ ዘገባ አመላክቷል።

በፈረንጆቹ ሚያዝያ 1 ቀን እስራኤል ሶሪያ በሚገኘው የኢራን ቆንስላ ጽሕፈት ቤት ላይ ባደረሰችው ጥቃት 13 ዜጎቿ መገደላቸውን ተከትሎ በእስራኤል ላይ ባሳለፍነው ቅዳሜ 300 ሚሳኤልና የድሮን ጥቃት ማድረሷ ይታወሳል። ለኢራን ጥቃት እስራኤል አጸፋዊ እርምጃ እንደምትወስድ ዝታ እንደነበርም የሚታወስ ነው።የሁለቱ አገራት የሰሞኑ ግጭትን ተከትሎ አገራት ዜጎቻቸውን ወደ እስራኤል እንዳይጓዙ እያስጠነቀቁ ነው።

ከስውር ጦርነት አልፎ ወደ ይፋዊና ቀጥተኛ ግጭት ውስጥ የገባው የሁለቱ አገራት የሰሞነኛ ፍጥጫ በቋፍ ላይ የነበረ የአካባቢውን ሰላምና ጸጥታ ወደለየለት ጦርነት እንዳይከተው ተሰግቷል።

 
የቡድን-7 አገራት ውጭ ጉዳይ ሚንስትሮች፣ በኢትዮጵያ የሰፈነው ውጥረትና ኢትዮጵያ ከሱማሌላንድ ጋር የተፈራረመችው የባሕር በር መግቢያ ስምምነት እንደሚያሳስባቸው ትናንት ባወጡት መግለጫ አስታውቀዋል።

አገራቱ፣ ኢትዮጵያ እና ሱማሊያ "ኹሉንም የንግግር መስመሮች" ክፍት በማድረግ ውጥረቶችን እንዲያደርግቡ ጠይቀዋል። በኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች፣ የኢኮኖሚ ቀውስና የምግብ ዋስትና ማሽቆልቆል አሳሳቢ እንደኾኑም አገራቱ ገልጸዋል።

የቡድኑ አባል አገራት፣ የመንግሥት የሰብዓዊ መብቶች ጥበቃ ዘላቂ እንዲኾን፣ ሲቪሎችን ከጥቃት እንዲጠበቁ፣ ውጥረቶች በፖለቲካዊ ንግግር እንዲፈቱ፣ እርቅ፣ የሽግግር ፍትህና ተጠያቂነት እንዲሰፍን ጥሪ አድርገዋል።

በተያያዘ ዜና

የቡድን-7 አገራት፣ ሱማሊያና ኢትዮጵያ በባሕር በር መግቢያ ዙሪያ የገቡበትን ውጥረት ለመፍታት "ኹሉንም የንግግር መስመሮች ክፍት እንዲያደርጉ" ላቀረቡት ጥሪ፣ የሱማሊያ መንግሥት ትናንት እኩለ ሌሊት ላይ ባወጣው መግለጫ አሉታዊ ምላሽ ሰጥቷል።

የሶማሊያ መንግሥት፣ ኢትዮጵያ ከሰሜናዊቷ ግዛቴ ሶማሊላንድ ጋር የደረሰችበትን የባሕር በር መግቢያ የመግባቢያ ስምምነት እስካልሰረዘችና የሱማሊያን አንድነት፣ ሉዓላዊነትና በውስጥ ጉዳይ ጣልቃ ያለመግባት መርህ ሙሉ በሙሉ እስካላረጋገጠች ድረስ፣ ንግግር ማድረግ የሚሳካ ነገር አይደለም ብሏል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ኢዜማ፣ የመንግሥት አመራሮች፣ ካድሬዎችና የሜዲያ ተቀጣሪዎች "ሐሰተኛ መረጃ" እና "የጥላቻ ንግግር ሊባሉ የሚችሉ" ንግግሮችን በፌስቡክ ላይ በማሠራጨትና ስም በማጥፋት ዘመቻ ስለመጠመዳቸው ቢቢሲ ባደረገው ምርመራ መረጋገጡ፣ "ፍጹም ተቀባይነት የሌለው" እና ሥልጣን ከያዘ መንግሥት የማይጠበቅ ድርጊት መኾኑን ትናንት ምሽት ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።

ኢዜማ፣ ይህ "አምባገነናዊነት" እና ራስን "በአሸዋ መሠረት" ላይ የማቆም አካሄድ የዲሞክራሲ እንቅፋት በመኾኑ በጥብቅ አወግዘዋለሁ ብሏል። ፓርቲው፣ መንግሥት ከመሰል ድርጊቱ እንዲቆጠብና ለእስካኹኑ ድርጊቱ ሕዝቡን ይቅርታ እንዲጠይቅ አሳስቧል።

ፓርቲው፣ የመንግሥት መገናኛ ብዙኀን መንግሥትንና ፓርቲን በማይለዩ ሃላፊዎች በመያዛቸው ሕዝቡ በመንግሥት ላይ እምነት እንዲያጣና ማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎችን የመጀመሪያ የመረጃ ምንጭ አድርጎ እንዲቆጥር ተደርጓል ብሏል።

@sheger_press
@sheger_press
እናንተ ደጋግ ኢትዮጵያውያን እባካችሁ‼️

ድምፅ ሁኗት 🙏😭

ቪድዮውን ማየት ያልቻላቹ የመልክተኛው የቲክቶክ ገፅ ላይ አለላቹ

ሼር አድርጉት እባካችሁ 🥹

እናት እና አባቷ ለስራ በሌሊት ሲወጡ ጠብቀው 3 ጎረምሶች በራቸውን በርግደው ገቡ። እቺ የ 17 ዓመት ልጅና ታናሿ የ4 ዓመት ልጆች ቤት ውስጥ ብቻቸውን ነበሩ።

ጎረምሶቹም እቺን ልጅ ሊደፍሯት አባቷ ተኝቶበት የነበረው ፍራሽ ላይ ገፍትረው ጣሏት። አፏን በጨርቅ አፍነው ይታገሏት ጀመር። በዚህ ውስጥ ሆና እንኳን የታናሽ እህቷ ጉዳይ አስጨንቅዋት ወደ እህቷ ሊሄድ የሚታገለውን ጎረምሳ በእጅም በምልክትም መማፀን ጀመረች።

ጎረምሳዎቹም ስታስቸግራቸው ራስን የሚያስት መዳኒት አፍንጫዋ ላይ ነፉባት። ራሷንም ሳተች። ሶስቱም ጎረምሶች እስኪበቃቸው ከደፈርሯት በኃላ ጥለዋት ወጡ።

ስትነቃ ራሷን ያገኘችው ሆስፒታል ተኝታ ነው! ጉዳዩ ለሕግ አካላት ተነገረ። ሕጉም ምንም ማስረጃ የለም አርፈሽ ኑሪ ብለው ሸኟት። በስንት መከራ ከህመሟ እና ከስብሯቷ አገግማ entrance ስላልመጣላት የሜካፕ ኮርስ መውሰድ ትጀምራለች።

ይሄንን ያዩ ደፋሪዎች እንዴት እኛ ደፍረንሽ ከቤት ወጣሽ አርፈሽ ቤት ተቀመጪ የሚል ማስፈራሪያ ይደርሳት ጀመር።

ጭራሽ 2መቶ ብር እና እንገልሻለን የሚል ደብዳቤ ይላክላት ጀመር። ሁኔታው ያስፈራቸው ቤተሰቦች አሁንም ደብዳቤውን ይዘው ወደህግ ይሄዳሉ። የሕግ አካላትም አታካብዱ ይሄ እኮ ቀላል ነው be2መቶ ብሩ ቡና አፍሉበት በሚል ስላቅ ይመልሷቸዋል።

ካስፈራሯት ከቀናት በኃላ የሆነች ሴትዮ መጥታ ሰው የምትጠይቃት አስመስላ አዘናግታ ከደፋሪዎቹ ጋር አፍነው ወሰዷት። ስትነቃ መኪና ውስጥ እራሷን አገኘችው። ደፋርዎቹም መንቃቷን ሲያዩ ድጋሜ መድሃኒቱን ነፍተውባት ራሷን ከሳተች በኃላ እንደፈለጉ ተጫውተውባት እንዳስፈለጋቸው አድርገው ጫካ ውስጥ ጥለዋት ሄዱ!

ቤተሰቦቿም እሷን በማሳከም ያላቸውን ጨርሰው ሸራ ወጥረው መኖር ከጀመሩ ሰነባብተዋል። ደፋርዎቹም ማንም ስለማይጠይቃቸው የፈለጉት ቤት እየገቡ የፈለጉዋትን ሴት መድፈራቸውን ቀጥለዋል ። የሕግ አካላቱም በተጎጂዎች ቁስል እየተሳለቁ የወንጀሉ ተባባሪ ሆነዋል ።

ነግ በኔ ነው! ለዚች ሴት ፍትህ እንጠይቅ እንደሷ ድምፃቸው ላልተሰማ ተሰብረው ቤት ለቀሩት ሴቶች ፍትህ እንጠይቅ ሕግ የለም አትበሉ ሚዲያ የያዘው ጉዳይ ሕግ አለው ለማለት ይሰራል ጫና እናድርግ ፍትህ እንበል ፍትህ እንሻለን

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
Forwarded from Bura - collection
m14 Samsung 📱
✔️6ram
✔️128 GB

📌ዋጋ=16500

@ethio_sellerr   
@Birukepromo
           ላይ  ያናግሩን።
በስልክ ቁጥራችን 0946159797 ይደዉሉልን ።

አዲስአበባ ያሉበት እናደርሳለን 🛵🚵
ክፍለሀገር በፖስታ ይደርሷታል።📩📮

ተጨማሪ እቃዎችን ለመሸመት የቴሌግራም ገፃችንን ይቀላቀሉ👇👇
https://www.tg-me.com/bura_collection
በአዲስ አበባ ከተማ በተገነቡ ማዕከላት ከመደበኛው ገበያ የጤፍ ዋጋ ላይ የ3 ሺ ብር ቅናሽ እንዳለው ተገለፀ

በአዲስ አበባ ከተማ ተገንብተው አምራችን ከሸማቾች የሚያገናኙ ሶስት ማዕከላት ሙሉ በሙሉ ስራ መጀመራቸውን የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ አስታውቋል።

ቢሮው አሁን ላይ በዋነኛነት የገበያ ማዕከላት ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ እንደሚገኝ ለብስራት ሬድዮና ቴሌቭዥን የተናገሩት የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ የኮምኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰውነት አየለ ከ3.3 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ ተደርጎባቸው እንደተገነቡ ተናግረዋል።

ከተማ አስተዳደሩ በእነዚህ ማዕከላት አምራቾችን ሙሉ በሙሉ አስገብቶ ለሸማቾች ከማሳ የተሰበሰቡ ምርቶችን በቅናሽ ዋጋ እያቀረበ ነው ብለዋል።እነዚህ ማዕከላት በሸማቹ እና በአምራቹ መሀል የነበረውን ህገ ወጥ ደላላን መስበር የቻለ ነው።

ከዋጋም አኳያ ከእሁድ ገበያ አንፃር የተሻሉ መሆናቸውን ገልፀዋል።ምርቶች በበቂ ሁኔታ በገበያ ማዕከላት ቢገቡም ህብረተሰቡ ስለ ማዕከላቱ በቂ ግንዛቤ ስሌለው የሚበላሹ  ምርቶች አሉ በተለይ ደግሞ  የአትክልት እና ፍራፍሬ ምርቶች ብልሽት እንደሚገጥማቸው ተናግረዋል።

ሸማቹ ወደ እነዚህ ማዕከላት በመምጣት ሁሉንም ምርቶች በአንድ እንዲሁም በቅናሽ ዋጋ ማግኘት እንደሚችል ገልፀዋል።ከመደበኛ ገበያዎች የጤፍ ዋጋ በእነዚህ ማዕከላት ውስጥ የ3ሺ ብር ቅናሽ እንዳለው አንስተዋል። እንዲሁም አትክልት እና ፍራፍሬ ምርቶችም ከእሁድ ገበያው ቅናሽ እንዳለውም አቶ ሰውነት አየለ ጨምረው ለብስራት ሬድዮና ቴሌቭዥን ተናግረዋል።

ማዕከላቱ በኮልፌ ፣በአቃቂ እና በለሚ ኩራ ክፍለ ከተሞች ይገኛሉ ተብሏል።

ዳጉ_ጆርናል
ሶሻል ሚዲያ ይሺጡ ይግዙ

✔️የቴሌግራም ግሩፕ እና ቻናል
✔️የዩትዩብ ቻናል
✔️የፌስቡክ ፔጅ
✔️የቲክቶክ ገፅ

መግዛት እና መሸጥ የምትፈልጉ አናግሩን ሁሉም እኛ ጋር አለ።
    @ethio_sellerr
@birukpromo ላይ አናግሩን

በስልክ ቁጥራችን 0946159797 ይደዉሉንን::
ኢራን አፋጣኝ የበቀል እርምጃ ለመውሰድ እቅድ የላትም ሲሉ አንድ የኢራን ባለስልጣን ተናገሩ

አንድ የኢራን ከፍተኛ ባለስልጣን ለሮይተርስ የዜና ወኪል እንደተናገሩት "ኢራን በእስራኤል ላይ አፋጣኝ የበቀል እርምጃ ለመውሰድ እቅድ የላትም" ሲሉ እስራኤል በኢራን ኢስፋሃን ከተማ ላይ ጥቃት መሰንዘሯ ተከትሎ ተናግረዋል፡፡

ሁለት የአሜሪካ ባለስልጣናት ጥቃቱ ከእስራኤል የመጣ መሆኑን ለመገናኛ ብዙሃን ቢናገሩም እስራኤል ኃላፊነቱን ለመዉሰድ ወዲያዉ መግለጫ አላወጣችም ነበር።አንድ ኢራናዊ ተንታኝ ለኢራን መንግስት ቲቪ እንደተናገሩት "በኢስፋሃን በአየር መከላከያ የተተኮሱ ሚኒ ሰው አልባ አውሮፕላኖች ወደ ኢራን ውስጥ ሰርጎ ገቦች ገብተዋል" በማለት እስራኤል ጥቃቱን ፈጽማለች የሚለውን ዘገባ አሳንሰዉ ተናግረዋል፡፡

በሌላ በኩል እስራኤል በኢራን ላይ የበቀል ጥቃት መፈጸሙን ተከትሎ ዩናይትድ ስቴትስ በእስራኤል ለሚገኙ የኤምባሲ ሰራተኞቿ እና ቤተሰቦቻቸው “ከከፍተኛ ጥንቃቄ የተነሳ” የጉዞ ገድብ ጥላለች።ኤምባሲው ሰራተኞቹ ከታላቋ ቴል አቪቭ ክልል ውጭ  ወደ ሄርዝሊያ ፣ ኔታንያ እና ዩሁዳን ጨምሮ ወደ እየሩሳሌም እና ቢየር ሼቫ አካባቢዎች እንዳይጓዙ አስጠንቅቋል፡፡
ራያ‼️

ከአላማጣ እና አካባቢው 29 ሺህ ህዝብ መፈናቀሉ ተገለጸ

ተፈናቃዮቹ በቆቦ፣ወልዲያ እና ሰቆጣ ከተሞች መጠለላቸው ተገልጿል
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ባወጣው ሪፖርት 29 ሺህ ዜጎች ከራያ እና አላማጣ አካባቢዎች መፈናቀላቸውን አስታውቋል፡፡

እንደ ድርጅቱ ሪፖርት ከሆነ ከሰሞኑ በትግራይ እና አማራ ክልል አዋሳኝ ቦታዎች ላይ ባገረሸው ግጭት ምክንያት ዜጎች ከመኖሪያ ቤታቸው ተፈናቅለዋል ብሏል፡፡
ተፈናቃዮቹ በቆቦ፣ወልዲያ እና ሰቆጣ ከተማ በሚገኙ መጠለያዎች ላይ እንደተጠለሉም ድርጅቱ አስታውቋል፡፡

በአካባቢው ባለው አለመረጋጋት ምክንያት ተጨማሪ ዜጎች ሊፈናቀሉ እንደሚችሉ የገለጸው ድርጅቱ ለተፈናቃዮች ውሃ፣ ምግብ እና ሌሎች ህይወት ማቆያ ድጋፍ በማድረግ ላይ መሆኑንም ገልጿል፡፡

አሁን ላይ ከለጋሽ ተቋማት እና ሀገራት የሚገኘው ድጋፍ እየተሟጠጠ በመሆኑ በአካባቢው ያለው ማህበረሰብ የሚችለውን ድጋፍ እያደረገ እንደሆነም ተገልጿል፡፡

ለተፈናቃዮቹ መጠለያ፣ የሕክምና አገልግሎት እና ሌሎች መሰረታዊ ድጋፎችን ማድረግ ይገባል ያለው ድርጅቱ የኢትዮጵያ አደጋ መከላከል እና ዝግጁነት ኮሚሽን ሰራተኞች ወደ ስፍራው ተሰማርተዋልም ተብሏል፡፡

ተፈናቃዮቹ ከአንድ ሳምንት በፊት በሚኖሩባቸው አካባቢዎች የህወሃት ታጣቂዎች ወደ ራያ እና አላማጣ አካባቢዎች መምጣታቸውን ተከትሎ ቤታቸውን ጥለው ለመሰደድ እንደተገደዱ ተገልጿል፡፡
ከተፈናቀሉት 29 ሺህ ዜጎች ውስጥ 70 በመቶዎቹ ህጻናት እና ሴቶች ሲሆኑ ቀሪዎቹ አዛውንቶች እና ታዳጊዎች ናቸው ተብሏል፡፡

በአላማጣ ከተማ የፌደራል የጸጥታ ሀይሎች መግባታቸውን ተከትሎ ተቋርጦ የነበረው ከቆቦ-አላማጣ ትራንስፖርት ዳግም መከፈቱ ተገልጿል፡፡

@sheger_press
@sheger_press
የመውጫ ፈተና‼️

ትምህርት ሚኒስቴር ሚያዝያ 9/2016 ዓ.ም ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በፃፈው ደብዳቤ፤ የመውጫ ፈተና ከሰኔ 14 እስከ 21/2016 ዓ.ም ድረስ እንደሚሰጥ አሳውቋል።(tikvah)

@sheger_press
ሹመት‼️

የቀድሞ የመከላከያ ሚንስትር ቀንዓ ያደታ የጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አህመድ ምክትል የደህንነት አማካሪ ሆነው ተሾሙ።

ዋዜማ በደረሳት መረጃ መሰረት ቀንዓ ያደታ በሚንስትር ዴዔታ ማዕረግ ከመሾማቸው አስቀድሞ በተለያዩ የፌደራልና የክልል የፀጥታ ተቋማት ውስጥ አገልግለዋል።

በኦሮሚያ የፀጥታ ዘርፍ ኀላፊ እንዲሁም የፌደራሉ ፖሊስ ምክትል ኮምሽነር ሆነው ሰርተዋል። በትግራዩ ጦርነት ሲጀመር የመከላከያ ሚንስትር የነበሩት ቀንዓ በመሀል በአብርሃ በላይ መተካታቸው ይታወሳል።

የጠቅላይ ሚንስትሩ የደህንነት አማካሪ ሚንስትር በነበሩት አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ተይዞ የነበረው የዋና አማካሪነት ቦታ እስካሁን አልተተካም።

[ዋዜማ]

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
እንድታውቁት‼️

ዛሬ መንገድ ይዘጋል።

ዛረረ ሚያዚያ 13 ቀን 2016 ዓ/ም በአዲስ አበባ መነሻና መድረሻውን መስቀል አደባባይ ያደረገ ሩጫ ይካሄዳል።

ሩጫው የ2016 " የኢትዮጵያ ታምርት " የጎዳና ላይ የ10 ኪሎ ሜትር የሩጫ ውድድር ነው።

የአዲስ አበባን ዋና ዋና መንገዶችን የሚያካልል እንደሆነም ታውቋል።

መነሻው መስቀል አደባባይ ከዛም በለገሃር ፣ ሜክሲኮ አደባባይ ፣ ቡልጋሪያ ማዞሪያ ፣ ቄራ ፣ ጎተራ ማሳለጫ ፣ አጎና ሲኒማ ፣ ጥላሁን አደባባይ አድርጎ መዳረሻውን መስቀል አደባባይ ያደርጋል።

ይህን ተከትሎ ሩጫው ተጀምሮ እስኪያልቅ የሚዘጉ መንገዶች እንዳሉ የአዲስ አበባ ፖሊስ አሳውቋል።

በዚህ መሰረት ፦

- ከመገናኛ ወደ መስቀል የሚወስደው መንገድ ኡራኤል አደባባይ
- ⁠ከኦሎምፒያ አደባባይ ወደ መስቀል
- ከመስቀል ፍላዎር አደባባይ ወደ አጎና መስቀለኛ
- ከጎርጎሪዎስ አደባባይ ወደ ጎተራ
- ከጎተራ ሼል ወደ ጎተራ
- ከማሞ ማቋረጫ ወደ ጎተራ
- ከጎፋ ገብርኤል ወደ ጎፋ ማዞሪያ
- ከአልማዝዬ ሜዳ ወደ ቄራ በረት
- ከመካኒሳ አቦ አደባባይ ወደ ሳር ቤት አደባባይ
- ከካርል አደባባይ ወደ ሳር ቤት አደባባይ
- ከልደታ ፀበል ወደ ኤዩ መብራት
- ከቡልጋሪያ ማዞሪያ ወደኤዩ መብራት
- ከኦርቢስ መታጠፊያ/ጮራጋዝ/ መስቀለኛ ወደ ሲጋራ ፋብርካ
- ከጠማማ ፎቅ ወደ ጥይት ፋብርካ
- ከላንድ ማርክ ሆስፒታል ወደ ገነት መብራት
- ከከፍተኛ ፍ/ቤት /ባልቻ ሆስፒታል/ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ
- ከአረቄ ፋብርካ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ
- ከሠንጋ ተራ 40/60 መስቀለኛ ወደ ሠንጋ ተራ መብራት
- ከበድሉ ህንፃ ወደ ቴሌ ባር
- ከብሔራዊ ቲያትር መብራት ወደ ለገሃር መብራት
- ከሀራምቤ መብራት ወደ ሳንጆሴፍ መብራት
- ⁠ከብ/ቤተመንግስት ወደ መስቀል አደባባይ
- ⁠ከኢንተርኮንትኔታል ሆቴል ወደ ባምቢስ የሚወስዱ መንገዶች ከማለዳው 11:00 ሰዓት ጀምሮ ሩጫው እስኪጠናቀቅ ድረስ ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናሉ።

#AddisAbabaPolice
2024/10/03 00:16:40
Back to Top
HTML Embed Code: