Telegram Web Link
ወንጀለኛው ጌትነት ከማረሚያ ቤት አምልጦ ነበር:-የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር‼️
የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር  በታዳጊዋ ሄቨን አሰቃቂ ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን አሁንም በድጋሜ ይገልጿል::

ከተማ አስተዳደሩ *ሀምሌ 25 / 2015 ዓ.ም* በባሕር ዳር ከተማ ዳግማዊ ሚኒሊክ ክፍለ ከተማ በ7 አመቷ ታዳጊ ህጻን ሄቨን ላይ በተፈጸመው አሰቃቂ ድርጊትና ህልፈተ ህይወት በእጅጉ ማዘኑን ገልፆ የነበረ መሆኑ ይታወሳል።

በህጻናት ላይ የሚፈጸምን ማንኛውም ጥቃት መከላከል በዋነኛነት የመንግስት ሃላፊነት ሲሆን በሌላ በኩል የሁሉም አካል ተመሳሳይ ድርሻ ያለው መሆኑን የገለፀው ከተማ አስተዳደሩ እንደዚህ አይነት አስነዋሪና አሳፋሪ ድርጊት በከተማችን በመፈፀሙ በእጅጉ ዛሬም በድጋሜ አዝነናል ።

የባሕር ዳር ከተማ ህዝብ ሰው ወዳድ፣ ሁሉን አክባሪ፣ ባህሉን፣ ወጉንና ታሪኩን ጠባቂ አስተዋይ ጨዋ ህዝብ ነው ። በዚህ እሴትና ባህል በተገነባ ማህበረሰብ ውስጥ የተፈፀመው ድርጊት በፍፁም ነውረኛና የከተማውን ህዝብ የማይገልፅ ሁሉም ሰው ሊያወግዘው የሚገባ ዘግናኝ ተግባር ነው ።

ሁሉም እንደሚያስታዉስዉ ወንጀሉ እንደተፈፀመ  የከተማ አስተዳደሩ የሚመለታቸው ተቋማት በዋነኝነትም  ከፖሊስ ፣ ከጤና ተቋም ፣ ከፍትህ እንዲሁም ከተበዳይ ወገኖች ጋር በመቀናጀት ጉዳዩ በህግ እንዲያዝ በማድረግ ልዩ ትኩረትና ክትትል በማድረግ ድርጊቱን የፈጸመው ግለሰብ ተይዞ በ20/06/2016 ዓ.ም በከፍተኛ ፍርድ ቤት የ25 አመት ጽኑ እስራት ተፈርዶበት ባህርዳር ማረሚያ ቤት እንዲገባ ተደርጓል። 

በዚህ አጋጣሚ ከተማ አስተዳደሩ የፍርድ ቤቱን የዳኝነት ነፃነት የሚያከብር ቢሆንም ከተፈፀመው ዘግናኝ ድርጊትና የማህበረሰቡን ሞራልና ክብር ዝቅ ያደረገ ወጀል በፈፀመው ወንጀለኛ ላይ የተሰጠው ፍርድ አስተማሪነት የሚያንሰው መሆኑን አስተዳደሩ በፅኑ ያምናል ።

ከተማ አስተዳደሩ ጉዳዩን በጥብቅ ለመከታተል ባለው ፅኑ አቋም ክልሉን ባጋጠመው ቀውስ ወንጀለኛው ከማረሚያ ቤት አምልጦ የወጣ መሆኑን እንዳወቀ  በልዩ ሁኔታ የፀጥታ ሀይሉ ክትትል እንዲያደርግ አመራር ተሰጦ ወንጀለኛው ተይዞ ድጋሜ ወደ ማረሚያ ቤት እንዲገባ ተደርጓል።

ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ በአሁኑ ወቅት ወንጀለኛው ይግባኝ የጠየቀ እንደሆነ እና ጉዳዩ ለጥቅምት 20/2017 ዓ.ም ፍ/ቤቱ ቀጠሮ የሰጠ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ ያውቃል። የፍርድ ቤቱን ነጻነት በጠበቀ መልኩ ከህግ አኳያ የይግባኙን ሁኔታ በተመለከተ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን በትኩረት የምንከታተለው እና ፍትህ እንዲረጋገጥ በፅናት የምንታገል እንደሆነ ለማረጋገጥ እንወዳለን።

ከተማ አስተዳደሩ በልጃችን ህፃን ሄቨን  ለደረሰው ግፍ ፍትህ ሲጠይቅ ፣ ለጉዳዩ ለሰጠው ትኩረት እና እያደረገ ላለው ትግል ለመላው የህብረተሰብ  ክፍል   ምስጋና እያቀረብን በቀጣይም ለፍትህ መረጋገጥ ለምናደርገው ትግል ህ/ሰቡ ከጎናችን እንዳይለይ ጥሪያችን እያቀረብን በቀጣይም የህፃናት ጉዳይ የሁላችንም ጉዳይ ስለሆነ በትብብር መስራት ይጠበቅብናል።

@sheger_press
@sheger_press
ጥቆማ‼️

ክሪፕቶና ኤርድሮፕን በተመለከተ የተለያዩ መረጃዎችን በስፋት የምንዳስስበትን ሁለተኛው ቻናላችንን join ብታደርጉ ትጠቀማላችሁ።


- Crypto trading
- Airdrop list
- Daily combo
- Updates and listing date

አሁንኑ ይቀላቀሉ👇👇
https://www.tg-me.com/+fzeZ2gn56UE3NTI0
https://www.tg-me.com/+fzeZ2gn56UE3NTI0
🇪🇹ለሀገር ውክልና የተመረጠው አትሌት በተፈፀመበት ድብደባ የአይን ብርሃኑን አጣ!!

👉በድብደባ አንድ አይኑን ያጣው አትሌት አደጋው እንዴት ደረሰበት?

የ17 አመቱ አትሌት ሰው መሆን ታሪኩ፤ ፔሩ ለሚካሄደው የዓለም ከ20 አመት በታች ለሀገር ውክልና ተመርጦ ፌደረሽኑ ባዘጋጀላቸው ሆቴል በዝግጅት ላይነበር ። በዚህ ሁኔታ እያለ ባለፈው እሁድ የከሰዓት በኋላ ፕሮግራም ለመስራት ወደ ጫካ ወጣ ብሎ ልምምዱን ጨርሶ ያቀዘቅዛል ። በዚህ ሁኔታ አንድ ሰው ወደ አትሌቱ ይቀርብና ፓሊስ ነኝ በማለት ፤
' እዚህ አካባቢ ቁማር የሚጫወቱ ታውቃለህ ' በማለት ይጠይቃል ። አላውቅም ብሎ እንደመለሰ ወዲያው በፍጥነት አንገቱን ሲይዘው አትሌቱም እራሱን ለመከላከል ጥረት ያፈርጋል ።

ሌሎች ሁለት ሰዎች በድነገት በመምጣ በሁለት በድንጋይ ጭንቅላቱን በመምታ አልወድቅ ሲል በሽጉጥ አይኑን ተኩሰው ከመቱት በኋላ በኪሱ ያለውን ሞባይል በመውስድ እንደተሰወሩ ጓደኛቹ ለኢትዮ ራነርስ ገልፀዋል። ጉዳቱም ከፍተኛ ነው።

አትሌቱ በዳግማዊ ሚኒልክ ሆስፒታል ህክምና እየተከታተለ ሲሆን የፌደረሽን ሰዎች እየመጡም እየጠየቁት እንደሆነ ለህክምና የሚወጣውን የወጭ ደረሰኝ ያዙ ማንኛውንም ወጪ እንሸፍናለን በማለት በቃል እንደነገሯቸውም ጓደኞቹ ለኢትይ ራነርስ ገልፀዋል።

ልጁ ለሀገር ውክልና ተመርጦ ባለበት ሁኔታ ነውና አደጋው የደረሰበት ሙሉ ሀላፊነት ፌደረሽኑ ይወስዳል ብለን እንገምታለን።

ምን አልባት በፓሪስ በመጣው ውጤት የተበሳጩ ሌቦች ሊሆኑ ስለሚችሉ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴም ህክምናው ላይ እጁን ያስገባል የሚል ግምት አለን።

Via Ethio runners

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ከሕወሓት ጠቅላላ ጉባዔ ራሳቸውን ያገለሉ የፓርቲው ማዕከላዊ ኮሚቴና የቁጥጥር ኮሚሽን አባላትና ሌሎች አካላት ትናንት መቀሌ ውስጥ "ሕወሓትን ለማዳን" ያለመ ምክክር አድርገዋል።

ምክክሩ፣ ግጭት ሊቀሰቅሱ የሚችሉ የውስጥና የውጭ ሴራዎችን በጽኑ እንደሚያወግዝ ገልጦ፣ በመደናገር በፓርቲው ጉባዔ በመሳተፍ ላይ የሚገኙ የፓርቲው አባላት ከሕዝቡ ጎን እንዲቆሙ ጠይቋል።

የማዕከላዊ ኮሚቴና የቁጥጥር ኮሚሽን አባላቱ ምክክሩን ያደረጉት፣ ምርጫ ቦርድ ዕውቅና የነፈገው ጉባዔ በፓርቲው ስም ማናቸውንም እንቅስቃሴ እንዳያደርጉ ባገዳቸው ማግስት ነው።

@sheger_press
ገንዘብ ሚንስቴር ያለ ውጭ ምንዛሬ ክፍያ ዕቃዎች ወደ ሀገር ውስጥ እንዲገቡ ፈቅዷል‼️

የነዳጅ አውቶሞቢሎች እና ከፀጥታና ከደህንነት ዕቃዎች ውጪ ወደ አገር እንዳይገቡ በሕግ ክልከላ ከተደረገባቸው ዕቃዎች ያለ ውጭ ምንዛሬ ክፍያ (በፍራንኮ ቫሉታ) ወደ አገር እንዲገቡ መፈቀዱን የገንዘብ ሚኒስቴር አሳውቋል።

ውሳኔው የተላለፈው መንግሥት በቅርቡ ተግባራዊ ያደረገው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው፤  የገቢ ንግዱን በይበልጥ እንዲያሳልጥ መሆኑን የገንዘብ ሚኒስቴር ለጉምሩክ ኮሚሽን በጻፈው ደብዳቤ አስታውቋል።

ሚኒስቴሩ ከተከለከሉት ሁለቱ በስተቀር ያለ ውጭ ምንዛሬ ክፍያ (በፍራንኮ ቫሉታ) ዕቃዎች ወደ ሀገር ውስጥ እንዲገቡ  በመንግስት የወሰነ መሆኑን በመጥቀስ ተግባራዊ እንዲደረግ አሳስቧል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ሁሉም ነገር አሳዛኝ ነዉ

በአማራ ክልል በመንግስት እና በፋኖ ሀይሎች መካከል እየተደረገ ያለዉ ዉጊያ ሰሞኑን ተባብሶ ቀጥሎል ፡፡

የአማራ ክልል የመረጃ ምንጮች እንደሚሉት ከሆነ በሰሞኑ ከፍተኛ ዉጊያ ከሁለቱም የአንድ ሀገር ወጣቶች ከፍተኛ ሰበአዊ እልቂት እንዳስተናገዱ ነዉ ፡፡

በጎጃም በጎንደር እና ሰሜን ሸዋ ባገረሸዉ ዉጊያ በአንድ በኩል ከፍተኛ ቁጥር ያላቸዉ የመንግስት ሀይሎች ሲገደሉ እንዲሁም ለታጣቂዎቹ እጃቸዉን ሲሰጡ መከላከያ ወሰደ በተባለ አፀፋዊ ርምጃ በተመሳሳይ የፋኖ ሀይሎችም ተመሳሳይ እጣ ፈንታ ደርሶቸዋል፡፡

አንድ ስማቸዉ እንዳይጠቀስ ያሉ በጎጃም የሚኖሩ ገበሬ ስለ ሰሞኑ ሁነት ሲገልፁ' 'በኛ አካባቢ ለ ስድስት ሰአት የፈጀ ደም አፋሳሺ የጨበጣ ዉጊያ ድረስ የተደረገ ጦርነት ተካሂዶ ተኩሱ በረደ ብለን ከቤታችን ስንወጣ ማሳችን ሙሉ ለሙሉ በሬሳ ተጥለቅልቆ ነዉ የጠበቀን የመንግስትም ይሁን የፋኖ ወታደሮች ወድቆል ሲሉ ገልፀዋል'

ሰላም ለሀገራችን ሰላም ለኢትዬጲያ

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ህወሓት ምርጫ አካሂዷል

ዶ/ር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ሊቀመንበር ሆነው በድጋሚ ተመረጡ።

-አቶ አማኑኤል አሰፋ አቶ ጌታቸው ረዳን በመተካት የፓርቲው ምክትል ሊቀመንበር ሆነው ተመርጠዋል።

ህወሓት ሁለቱን የፓርቲውን ከፍተኛ አመራሮች ምርጫ ያደረገው ላለፉት ስድስት ቀናት በመቐለ ከተማ ሲያደርገው የነበረውን አወዛጋቢ ጠቅላላ ጉባኤ በዛሬው ዕለት ሲያጠናቅቅ ነው። በዛሬው የጉባኤ ውሎ፤ ዘጠኝ አባላት ያሉበት የህወሓት ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት ምርጫም ተከናውኗል።

ፓርቲው ከስድስት ዓመት በፊት ባከናወነው ጉባኤ ከመረጣቸው የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት ውስጥ በአሁኑ ምርጫ የተካተቱት ዶ/ር ደብረጽዮን፣ ወ/ሮ ፈትለወርቅ ገብረእግዚያብሔር እና ዶ/ር አብርሃም ተከስተ ብቻ ናቸው። ከጠቅላላ ጉባኤው ራሳቸውን ያገለሉት አቶ ጌታቸው ረዳ እና አቶ ጌታቸው አሰፋን ጨምሮ 6 የፖሊት ቢሮ አባላት በአዲስ ተመራጮች ተተክተዋል።

(ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)

@ethio_mereja_news
‘’ዛላንበሳ ጨምሮ በኤርትራ ሰራዊት በተያዙ የኢሮብ አካባቢዎች ነዋሪዎች ከፍተኛ ጉዳት እየደረሰባቸው ነው’’ ሲል የህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም የመቀሌ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት አስታወቀ‼️
በዛላንበሳን ጨምሮ በኤርትራ ሰራዊት እጅ በሆኑ የኢሮብ አካባቢዎች አገልግሎት መስጠት እንዳልቻለ ጽሕፈት ቤቱ አስረድቷል፡፡

‘’የፌደራል መንግስት እና በሃወሃት መካከል ተደርጎ በነበረው ጦርነት ምክንያት በኤርትራ ሰራዊት እጅ የገቡ አካባቢዎች ባለመለቀቃቸው የአካባቢው ተወላጆች ላይ ችግር እየደረሳባቸው’’ እንዳለ የጽሕፈት ቤቱ ሃላፊ ፀሃዬ እንባዬ ተናገረዋል፡፡

በኢሮብ የነበረው የባንክ፣ የስልክ  እና መሰል አገልግሎት በጦርነቱ ወቅት ከተቋረጠ ወዲህ ዳግም አልተመለሰም ተብሏል፡፡

በዚህም ምክንያት ‘’በኤርትራ ሰራዊት እጅ ባሉ እና ከኢሮብ አካባቢ ወደ አዲግራት እንዲሁም ጎረቤት ከተሞች 100 ኪ.ሜ ለማይሞላ መንገድ 600 ብር እየከፈሉ’’ እንደሆነ ኃላፊው ተናግረዋል፡፡

በተያዙ አካባቢዎች ያሉ ትምህርት ቤቶች እና የጤና ተቋማት እስካሁን ከአገልግሎት ውጭ ናቸው፡፡
ሸገር

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
እንዲህም ሆኗል‼️
የጭካኔ ጥግ😭😭 ነው‼️

እናት 4ህፃናት ልጆቿን እንጀራ ለማጉረስ ሁሌም ለሊት 12:00ሰዓት ከቤት ወጥታ ካገኘች የቀን ስራዋን ሰራርታ ማታ 12:00ሰዓት ትመለሳለች!!

ግንበኛው አባት ደግሞ አረፋፍዶ ጠዋት 2:00ሰዓት ከቤት ይወጣና ስራውን ሰርቶ እንደጨረሰ እሱም ወደ ልጆቹ ይመለሳል!!

በአንደኛው ክፉ ቀን እናት እንደተለመደው በለሊት መውጣቷን ተከትሎ አባት የ14ዓመቷ የ6ተኛ ክፍል ተማሪ የመጀመሪያ ሴት ልጁን

"አባዬ እባክህ ተወኝ"

እያለችው አስችሎት በተኛችበት በጭካኔ ደፈራት!

ህፃኗ ልጅ መናገር እየፈራች ስቃይዋን እንደምንም ችላ ብትኖር በድጋሚ የእናት መውጫ ሰዓት ጠብቆ አንገላቶ ደፈራት!!

በጣም ፈሪ፣ምንም አይነት የወንድ ጓደኛ የሌላት ሴት ከወራት በኋላ በአካባቢና ጎረቤት ውትወታ ሰትመረመር ምንም የማታውቀው የ14ዓመት ህፃን

የ3ወር እርጉዝ ነሽ" ተባለች!አማራጭ ስላልነበራት ሁሉንም ለፖሊስ ተናገረች!!

አረመኔው አባት እስር ቤት ገብቶ ፍርድ ቤት ቆሞ 18ዓመት ቢፈረድበትም

ህፃኗ ከአባቷ ያረገዘችውን ጨቅላ ወልዳ ጡት ማጥባት ስላልቻለች የአንድ አመት ልጅ ያላት እናቷ እያገዘቻት በደሳሳ ጎጆአቸው ውስጥ በስቃይ እየኖሩ ይገኛል!

አባትም በእስር ቤት እየተቀለበ
ሙያ እየተማረ በህይወት እየኖረ ይገኛል!!

Via Henok Fikadu

* ፍትህ ለሄቨንና
* ለእህቶቻችን🙏

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
በኮንሶ ዞን “የታጠቁ ኃይሎች” ባደረሱት ጥቃት፤ የፖሊስ አባላትን ጨምሮ 11 ሰዎች ተገደሉ‼️

ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፣ በኮንሶ ዞን፣ ሰገን ከተማ ባለፈው ቅዳሜ እና ከትላንት በስቲያ እሁድ በደረሰ ጥቃት፤ ስድስት ነዋሪዎች እና አምስት የፖሊስ አባላት ተገድለዋል።
ጥቃቱን ያደረሱት “የታጠቁ ጽንፈኛ ኃይሎች ናቸው” ሲሉ ዋና አስተዳዳሪው ወንጅለዋል።

በደራሼ ወረዳ ከምትገኝ ሀይቤና ከተባለች ቀበሌ እንደመጡ የተነገረላቸው የታጠቁ ኃይሎቹ፤ ወደ ሰገን ከተማ “በድንገት” የገቡት ቅዳሜ ነሐሴ 11፤ 2016 አመሻሽ ላይ መሆኑን አቶ ኡርማሌ ገልጸዋል።

ታጣቂዎቹ ወደ ከተማይቱ ከገቡ በኋላ “ከባድ ተኩስ” መክፈታቸውን የገለጹት የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ፤ በመጀመሪያ ኢላማ ያደረጉት “የወረዳው የአስተዳደር እና የጸጥታ ተቋማት ላይ” እንደነበር አስረድተዋል።

“ቀጥታ ተኩሱን የከፈቱት ወደ አስተዳደር እና ወደ ፖሊስ ጽህፈት ቤት፤ ፖሊስ ጣቢያው ላይ ነው። ከቅዳሜ ለሊት 6 ሰዓት እስከ 10 ሰዓት ሲታኮሱ ቆዩ። ከዚያ በኋላ በመሃል ረገብ አለ። ማለዳ ላይ 12 ሰዓት አካባቢ [በድጋሚ] ጀመሩ” ሲሉ አቶ አርማሉ በዕለቱ የነበረውን ሁኔታ አብራርተዋል።

ታጣቂዎቹን “በደንብ የተደራጁ” ሲሉ የገለጿቸው የሰገን ዙሪያ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ፤ በተኩስ ልውውጡ አምስት የፖሊስ አባላትን መግደላቸውን ተናግረዋል።
ከዚህ በተጨማሪ በርካታ ቤቶችንም ጭምር አቃጥለዋል።

(ayu)

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በኤፍራታና ግድም ወረዳ በሁለት ቀበሌዎች በመሬት መንሸራት ምክንያት በ 156 የግለሰብ ቤቶች ላይ ጉዳት አደረሰ‼️

በሰ/ሸዋ ዞን ኤፍራታና ግድም ወረዳ በበርግቢ ቀበሌ እና በመንተኬ ሸረፋ ቀበሌ የመሬት መንሸራተት ተከስቷል።

በመሬት መንሸራተቱ ምክንያት በዕለቱ በሰው ህይወት ላይ ያደረሰው ጉዳት ባይኖርም በአንድ መቶ ሃምሳ ስድስት የግለሰብ የመኖርያ ቤትን ጨምሮ፣ ማሳ ላይ እና ቋሚ ተክሎች ላይ ጉዳት አድርሷል።

በዚህም መሠረት በርግቢ ቀበሌ በነሃሴ 07/2016 ዓ.ም ባስከተለው ከባድ ዝናብ የ24 ግለሰቦች ቤት የመፈራረስ እና ከነበረበት ቦታ ዝቅ የማለት(የመስጠም) አደጋ የደረሰባቸውና ቤቶቹ ከጥቅም ውጭ የሆኑ ሲሆን በዚሁ ቀበሌ በነሃሴ 12/2016 ዓ.ም በ12 አርሶ አደሮች ማሳ ላይ የመሬት መንሸራተቱ ተከስቷል።

ከዚህ በተጨማሪም በነሃሴ 12/2016 ዓ.ም በመንተኬ ሸረፋ በሶስት ጎጦች ላይ በ132 ግለሰቦች የመኖሪያ ቤት ላይ እና የቋሚ ተክሎች ላይ ጉዳት ያደረሰ ሲሆን ለጊዜው የመሬት መንሸራተት የተከሰተባቸው ቤቶች እና ተክሎች ለጊዜው ሙሉ በሙሉ የጠፉ ባይሆንም የክረምቱ የዝናብ መጠን በዚሁ የሚቀጥል ከሆነ ከጥቅም ውጭ መሆናቸው አይቀርም ሲሉ የዘገበው የወረዳው ኮሙኒኬሽን ቢሮ ነው

@ethio_mereja_news
በጉራጌ ዞን  ሁለት ህፃናት በጅብ ተበልተዉ ህይወታቸዉ አለፈ

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በጉራጌ ዞን እንደጋኝ ወረዳ እድሜያቸዉ የ8 እና  የ9 ዓመት የሆኑ ሁለት  ታዳጊ ህፃናት በጅብ ተበልተዉ ህይወታቸዉ ማለፉን የዞኑ ፖሊስ ገልጿል።

በጉራጌ ዞን እንደጋኝ ወረዳ በወሌቾ ቀበሌ አንዦኔ ተብሎ በሚጠራ መንደር ድርሻዬ ኑረዲን የተባለ የ8 ዓመት ታዳጊ ነሐሴ 11 ቀን 2016 ዓ.ም ከቀኑ 7:00 ሠዓት ገደማ በጅብ መበላቱን  ፖሊስ አስታዉቋል።

በተጨማሪም ነሐሴ 13 ቀን 2016 ዓ.ም ከቀኑ 8:30 ሠዓት  በወረዳው ሸውራ ቀበሌ ልዩ ስሙ ጎምሻ ተብሎ በሚጠራ መንደር መድሐኒት ፀጋዬ የተባለች የ9ዓመት ታዳጊ በጅብ ተበልታለች።

ታዳጊዋ ከሌሎች ጓደኞቿ ወንዝ ውሀ ልትቀዳ በሄደችበት በቀን አድፍጦ ይጠባበቅ በነበረ የተራበ ጅብ ተበልታ ህይወቷ ሊያልፍ መቻሉን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን የሚዲያ ክፍል ኃላፊ ምክትል ኮማንደር ታጁ ነጋሽ ለብስራት ሬዲዮና ቴሌቪዥን ተናግረዋል።

ተመሳሳይ በሆነ መልኩ ሊደርስ በሚችል የጅብ ጥቃት የህፃናት ህይወት እንዳያልፍ ህብረተሰቡ ለህፃናት  ተገቢዉ ጥንቃቄና ጥበቃ ማድረግ  አለበት ሲሉ ኮማንደሩ አሳስበዋል።

በሳምራዊት ስዩም

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ተረጋገጠ‼️

ሴናተር ቦብ ሜነንዴዝ አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ ጫና እንድታደርግ ከግብጽ ጉቦ መቀበላቸው ተረጋገጠ‼️

የሀገሪቱ ፍትህ ተቋማት ባደረጉት ምርመራ ቦብ ሜነንዴዝ ከግብጽ እና ኳታር ኩባንያዎች ጋር ጥቅም ትስስር በመፍጠር ያልተገባ ገንዘብ እንደተከፈላቸው ማረጋገጣቸው ተዘግቧል።

ትራምፕ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት በነበሩት ወቅት ኢትዮጵያ፣ ግብጽ እና ሱዳን መሪዎች በታላቁ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ የሶስትዮሽ ውይይት በማድረግ ላይ በነበሩት ወቅት እኚህ ሴናተር ኢትዮጵያ binding agreement እንድትፈሮም ጫና ሲያደርጉ እንደነበር እና በወቅቱ ኢትዮጵያም አልፈርምም በማለቷ ድርድሩ ያለ ስምምነት መጠናቀቁ ይታወሳል።

በዚህም ባለፉት 40 ዓመታት በአሜሪካ ፖለቲካ ውስጥ ተጽዕኖ ፈጣሪ የነበሩት ሜነንዴዝ ጉቦ በመቀበል ፍትህ እንዲዛባ በማድረግና በሌሎች ወንጀሎች ጥፋተኛ ሆነዋል።
ይህን ተከትሎም የሀገሪቱ ፍርድ ቤት በጉምቱው ፖለቲከኛው ላይ የእስር እና ሌሎች ቅጣት ውሳኔዎችን ለማስተላለፍ ለመጪው ጥቅምት ወር ቀጠሮ ይዟል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
2024/09/30 09:36:47
Back to Top
HTML Embed Code: