Telegram Web Link
በደቡብ ጎንደር ዞን የሦስት ወረዳዎች ነዋሪዎች በጎርፍ መከበባቸው ተገለፀ‼️

በደቡብ ጎንደር ዞን ሦስት ወረዳዎች፣ ከባድ ዝናም መጣሉን ተከትሎ በሺሕዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በጎርፍ መከበባቸውን የገለጹ ነዋሪዎች እና የአካባቢው ባለሥልጣናት፣ ከ15ሺሕ በላይ ነዋሪዎች አስቸኳይ የነፍስ አድን ሥራ እንደሚያስፈልጋቸው አመልክተዋል፡፡

የፎገራ እና የሊቦ ከምከም ወረዳ አደጋ መከላከል እና ምግብ ዋስትና ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት ባለሞያዎች፣ ትናንት ረቡዕ ለአሜሪካ ድምፅ ሲናገሩ፣ በሁለቱ ወረዳዎች በተለይ ከ12 በላይ የሚኾኑ ቀበሌዎች በጎርፍ መከበባቸውን አስታውቀዋል፡፡

በቀበሌዎች ያሉ ስድስት ትምህርት ቤቶች እና ሁለት የእምነት ተቋማት፣ በጎርፉ ጉዳት እንደደረሰባቸው የተናገሩት ባለሞያዎቹ፣ “በ3ነጥብ7 ሄክታር መሬት ላይ የነበረ ማሳ ወድሟል፤ በርካታ የቤት እንስሳትም በጎርፍ ተወስደዋል፤” ብለዋል፡፡

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
Become an AI Engineer for the Ethiopian FinTech Sector!

The Kifiya AI Mastery Training Program offers an intensive, project-based learning approach to make you job-ready for the Ethiopian FinTech sector and beyond!

In 3 months we will prepare you for top-notch job offers with hands-on projects, and you’ll gain practical skills for real-world applications. This program is fully funded and FREE!

This training is offered by Kifiya Financial Technology and powered by 10 Academy.

Application Open Until 16 AUG, 2024

Our curriculum covers key technology areas:
- Generative AI Engineering
- Machine Learning Engineering
- Data Engineering

Women, people with disabilities ( long-term physical, mental, intellectual, or sensory impairments), refugees, returnees, and IDPs are highly encouraged to apply.

Apply Today: apply.10academy.org

Learn more about the program at https://10academy.org/kifiya/learn-more
Forwarded from Sheger Press️️
Become an AI Engineer for the Ethiopian FinTech Sector!

The Kifiya AI Mastery Training Program offers an intensive, project-based learning approach to make you job-ready for the Ethiopian FinTech sector and beyond!

In 3 months we will prepare you for top-notch job offers with hands-on projects, and you’ll gain practical skills for real-world applications. This program is fully funded and FREE!

This training is offered by Kifiya Financial Technology and powered by 10 Academy.

Application Open Until 16 AUG, 2024

Our curriculum covers key technology areas:
- Generative AI Engineering
- Machine Learning Engineering
- Data Engineering

Women, people with disabilities ( long-term physical, mental, intellectual, or sensory impairments), refugees, returnees, and IDPs are highly encouraged to apply.

Apply Today: apply.10academy.org

Learn more about the program at https://10academy.org/kifiya/learn-more
ሰሞኑን የዶላር ዋጋ መጨመሩን ተከትሎ ገበያው ለያዥ ለገናዥ እያስቸገረ ነው‼️

አዲስ አበባ ውስጥ ባሉ የገበያ ስፍራዎች ከዶላር ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት የሌላቸው ምርቶች ድንገት ዋጋቸው ሲንር ተስተውሏል፡፡

መንግስትም #የዶላር_ጭማሪውን ተገን በማድረግ ዋጋ መጨመር አይቻልም፤ የሚጨምሩት ላይ እርምጃ እየወሰድሁኝ ነው ቢልም በነጋዴዎች ዘንድ ይህ እርምጃ ዋና አከፋፋዮቹን ሳይሆን ቸርቻሪው ነጋዴ ላይ ነው የበረታው ሲሉ እየተቹት ነው፡፡

በችርቻሮ ንግድ ላይ የተሰማሩ #ነጋዴዎች እንዳሉን ከሆነ ምርት አከፋፋይ ነጋዴዎች የዋጋ ጭማሪ አድርገዋል፤ መንግስት እነሱ ላይ እያደረገው ያለው ቁጥጥር የላላ ነው ሲሉ ተናግረዋል፡፡

ቸርቻሪ ነጋዴው ላይ ግን ቁጥጥሩ እጅግ የበረታ ነው ብለዋል፡፡

ታዲያ መንግስት አሁን እየሰራ ያለው አከፋፋዮችን ከመቆጣጠር ይልቅ ቸርቻሪ ነጋዴው ላይ ነው እየበረታ ያለው ገበያው እንዲረጋጋ ከተፈለገ ቅድሚያ #አከፋፋዮች እና አምራቾችን መከታተልና መቆጣጠር የዋጋ ንረት ችግሩን ይፈታል ብለዋል፡፡
# ሸገር ኤፍ ኤም

@ethio_mereja_news
የደመወዝ ማሻሻይ ይፋ ተደርጓል ?

እስካሁን የመንግሥት ሠራተኞች የደመወዝ ማሻሻያ / ጭማሪ ዝርዝር መረጃ ይፋ አልተደረገም።

በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ በቴሌግራም ፣ በፌስቡክ እየተዘዋወረ ያለው " የፌዴራል መንግሥት ሲቪል ሰርቫንት ደመወዝ ማሻሻያ " የሚለው መረጃ ምንም ምንጩ የማይታወቅ ነው።

የተሰራጨው የደመወዝ ማሻሻያ ሰንጠረዥ ፤ የፅሁፍ ስህተቶች ጎልተው የሚታዩበት፣ የአጻጻፉ ግድፈት ያለበት፣ የድምር ጭምር ግልጽ እና ቀላል ስህተት ያለበት ነው።

ሲቀጥል ማን ይፋ እንዳደረገው አይታወቀም።

ማህተም አላፈረበትም ፤ መረጃውን ያወጣው መ/ቤትም አይታወቅውም።

እስካሁን በይፋ ለህዝብ የተሰራጨ የደመወዝ ጭማሪ ዝርዝር መረጃ የለም።

መንግሥት በቅርቡ የደመወዝ ጭማሪ እንደሚደረግ ማሳወቁ ይታወሳል።

@ethio_mereja_news
የተሰጣችሁን ቀድሞ የመውጣት ተልኮ ካልተገበራችሁ ትቀጣላችሁ ተብለናል ሲል አትሌት ዮሚፍ ቀጀልቻ ተናገረ

በፓሪስ ኦሊምፒክ 10 ሺ ሜትር የወንዶች ፍጻሜ የተሳተፈው ዮሚፍ ቀጀልቻ በተሰጠን ታክቲክ ምክንያት ሀገራችን የወርቅ ክብሯን ተነጥቃለች ብሏል።

አትሌቱ በውድድሩ ጥሩ የቡድን ስራ ነበረን ግን ቀድመን መውጣታችን እኛንም ሀገራችንንም ዋጋ አስከፍሏል ፣ ቢሆንም የብር ሜዳሊያ አሳክተናል ሲል ተናግሯል።

ቀድማችሁ ወጥታችሁ ሩጡ ይህን ካላደረካችሁ ግን ትቀጣላችሁ የሚል ማስጠንቀቂያ ለኛም ለአሰልጣኞችም ተሰጥቶን ነበር ያደረግነውም እሱን ነው ብሏል።

በዚህ ምክንያት አቅማችንን ቀድመን ጨርሰን አጨራረስ ላይ ተበልጠናል ፣ ከ5 ሺ በኋላ ብንወጣ ኖሮ ሁላችንም የትኛውንም አትሌት በታትኖ የመውጣት ጥሩ ብቃት ላይ ነበርን ብሏል።

በቀነኒሳ በቀለ ተይዞ የነበረውን የኦሊምፒክ ሪከርድ የሰበረውና የወርቅ ሜዳሊያውን ያሸነፈው ዩጋንዳዊው ጆሹዋ ቸፕታጋይ የኛን የቡድን ስራና ታክቲክ በመረዳት ለድሉ ተጠቅሞበታል ብሏል ዮሚፍ።

አትሌቱ በርቀቱ የወርቅ ሜዳሊያ ባለማምጣታችን የሀገሬን ህዝብ ይቅርታ እጠይቃለሁ ሲል ከኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ጋር ባደረገው ቆይታ ተናግሯል።

የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ እና አመራሮች በተወዳዳሪ አትሌቶች ፣ በቀድሞ አንጋፋ እና ስመጥር አትሌቶች እንዲሁም በስፖርቱ አዋቂዎች የሚነሳበት ነቀፌታ ቀጥሏል።

Via ሁሴን ግዛው

@ethio_mereja_news
የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ #በሕግ መጠየቅ አለበት!

“የፓሪስ ኦሎምፒክ የኢትዮጵያን አንገት ያስደፋ ነው፤ የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ #በሕግ መጠየቅ አለበት”

- ሻለቃ አትሌት ሐይሌ ገ/ሥላሴ

@sheger_press
@sheger_press
Fake News‼️

ትናንት በማህበራዊ ሚዲያዎች ሲዘዋወር የነበረው የደመወዝ ጭማሪ መረጃ " ሐሰተኛ መረጃ ነው " ሲል የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. መንግስት ኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት ማምሻውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠው ቃል አረጋግጧል። (Tikvah)

ሀሰት መሆኑ ትናንት መዘገባችን የሚታወስ ነው።

@sheger_press
@sheger_press
ኢትዮ መረጃ - NEWS
የደመወዝ ማሻሻይ ይፋ ተደርጓል ? እስካሁን የመንግሥት ሠራተኞች የደመወዝ ማሻሻያ / ጭማሪ ዝርዝር መረጃ ይፋ አልተደረገም። በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ በቴሌግራም ፣ በፌስቡክ እየተዘዋወረ ያለው " የፌዴራል መንግሥት ሲቪል ሰርቫንት ደመወዝ ማሻሻያ " የሚለው መረጃ ምንም ምንጩ የማይታወቅ ነው። የተሰራጨው የደመወዝ ማሻሻያ ሰንጠረዥ ፤ የፅሁፍ ስህተቶች ጎልተው የሚታዩበት፣ የአጻጻፉ ግድፈት…
ለትዝብት‼️

ደሞዝን በሚመለከት ትናንት መዘገባችን የሚታወስ ነው።

አንዳንዶቻቹ አንድ መስመር በማንበብ ብቻ እንዴት ሀሰተኛ መረጃ ትለቃላቹ ከሚሉ መረጃዎች በተጨማሪ ስትሳደቡ ለመመልከት ችለናል።

በድጋሚ ተመልከቱት መረጃው የሚለው ግን ሀሰተኛ መረጃ መሆኑ ነው የሚጠቅሰው።

ሳታረጋግጡ ክፉ አታውሩ አንድ መስመር በማንበብ ብቻ መረጃ አታንብቡ።

@sheger_press
የዋጋ ንረቱ ሰራተኛውን አልፎት ሄዷል! ለዚህም የደመወዝ ማሻሽያው መዘግየት የለበትም " - ኢሠማኮ

@sheger_press
ሹመት‼️

ጠቅላይ ሚንስትሩ የተለያዩ ሹመቶችን ሰጡ።

1. ለወ/ሪት ሀና ተልህኩ ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ በኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ዋና ዳይሬክተር

2. አቶ ተስፋዬ ይገዙ  በመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ

3. ዶ/ር ብሩክ ታዬ በኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ዋና ስራ አስፈፃሚ

4. ለአቶ አብዱርሃማን ኢድ ጣሂር በገቢዎች ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ

5. ኮማንደር ፍቅሩ አለማየሁ የአዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር

6. ለአቶ አብዱልሃኪም ሙሉ በንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ

7. አቶ አብዱርሃማን አብደላ በመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ

8. ለአቶ ፍቃዱ ተሰማ በሚኒስትር ማዕረግ በዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል

9. ወ/ሮ መስከረም ደበበ በገቢዎች ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ

10. ዶ/ር ቢቂላ ሁሪሳ በሚኒስትር ማዕረግ በዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል በመሆን ተሹመዋል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ከ2 ሺህ በላይ አስመጪና ሻጮች የሚሳተፉበት ኢግዚቢሽን ሊካሄድ ነው ተባለ

ባሮክ ኤቨንት ኦርጋናይዘር የ2017 ዓ.ም የአዲስ ዓመት በዓልን ምክንያት በማድረግ አስመጪዎች እና አምራቾች ከሸማች የሕብረተሰብ ክፍል ጋር የሚገበያይበትን ባዛር እና ኤክስፖን አስመልክቶ በዛሬው ዕለት በሚሊነየም አዳራሽ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰቷል።

የአዲስ ዓመት ባዛር እና ኤክስፖ ከነሃሴ 20 እስከ ጳግሜ 5 ቀን 2016 ዓ.ም በሚሊኒየም አዳራሽ እንደሚያካሂድ ተገልፆል ፡፡

በዝግጅቱ ላይ ከ2 ሺህ በላይ አስመጪና ሻጮች እንደሚሳተፉ የተጠቆመ ሲሆን፤ በቀን ከ7 ሺህ እስከ 10 ሺህ ሸማቾች ይገኛሉ ተብሎ ይታሰባል ተብሏል፡፡

በተጨማሪ በየቀኑ በሀገራችን የሚገኙ ከ35 በላይ ባህላዊ እና ዘመናዊ የሙዚቃ ባለሙያዎች የሙዚቃ ስራዎቻቸውን እንደሚያቀርቡም ተመላክቷል።

የዝግጅቱ የመግቢያዉ ዋጋ ከ100-150 ብር እንደሆነ ተነግሯል ።

አቤል እስጢፋኖስ (ኢትዬ ኤፍ ኤም)
“ የኦሎምፒክ ኮሚቴው ኢትዮጵያ በፓሪስ አሸበረቀች መባሉ ስላቅ ነው “ ሻለቃ ኃይሌ ገብረ ስላሴ‼️

ኢትዮጵያ በፓሪስ ኦሎምፒክ “ ያጌጠችበት ነው “ መባሉን ሻለቃ ኃይሌ ገ/ስላሴ “ ስላቅ “ ነው ሲል ገልፆታል።

“ ተሽቆጥቁጠናል መባሉ ይሄ ስላቅ ነው ፣ ስለ ውድድሩ የሚወራ ከሆነ እስከ አሁን ሜዳሊያ አልተገኘም አንገት የሚያስደፋ ውጤት ነው “
ኃይሌ ገብረ ስላሴ

ኃይሌ በዚህ ውስጥ ግን አትሌት በሪሁ አረጋዊ ፣ ፅጌ ድጉማ እና በተለይም ምስጋናው ዋቁማ ያሳዩትን ጥረት ሊደነቅ እንደሚገባ ገልፆል።

ኃይሌ ለተፈጠረው ነገር ከሀላፊነት መነሳት በቂ አለመሆኑን ሲናገር “ መጠየቅ አለባቸው “
ሲልም አሳስቧል።

የጉዳዩን አሳሳቢነት በቆይታው ያነሳው ኃይሌ በቀጣይ “ ወደ ክስ መሄዱ አይቀርም ፣ የህግ ተጠያቂነት መኖር አለበት “ ሲል ተደምጧል።

ወደ ስፍራው ያቀኑ ሰዎች በቁጥር በርካታ  መሆናቸውን የጠቆመው ኃይሌ “ የምፈራው ከዚህ በኋላ ያለውን ነው ፣ ምን ያህል ሰው ተመልሶ ይመጣል ? “ ሲል በጥያቄ ምላሽ ሰጥቷል።
ከመነሀሪያ 99.1 የራድዮ ጣቢያ የተወሰደ

@ethio_mereja_news
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
Join the Kifiya AI Mastery Training Program!

Apply by August 16, 2024👉 apply.10academy.org

Learn more about the training program at https://10academy.org/kifiya/learn-more
Forwarded from Sheger Press️️
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
Join the Kifiya AI Mastery Training Program!

Apply by August 16, 2024👉 apply.10academy.org

Learn more about the training program at https://10academy.org/kifiya/learn-more
አቶ ጌታቸው ረዳ ህወሓት በሚያካሂደው ቀጣይ ጉባኤ እንደማይሳተፉ አስታወቁ፣

#የትግራይ ክልል ግዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት እና የህወሓት ምክትል ሊቀመንበር አቶ ጌታቸው ረዳ ፓርቲያቸው በሚያካሂደው ጉባኤ እንደማይሳተፉ ትላንት ነሃሴ 2 ቀን 2016 ዓ.ም ለፓርቲው ሊቀመንበር በጻፉት ደብዳቤ አስታወቁ።

የፓርቲው ማዕከላዊ ኮሚቴ ውሳኔ ያላስተላለፈበት እና የማያውቀው የምዝገባ እንቅስቃሴ እየተደረገ ነው ሲሉ በመግለጽ በጉባኤው የዲሞክራሲያዊ አካሄድ እና ህጋዊነት ዙሪያ የጋራ መግባባት ላይ ባልተደረሰበት ሁኔታ አልሳተፍም ማለታቸውን በትግራይ ቴሌቪዥን ይፋ በተደረገው ደብዳቤያቸው ተመላክቷል።

አቶ #ጌታቸው ረዳ ለፓርቲው ሊቀመንበር #ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል በጻፉት ደብዳቤ ሊያካሄድ የታሰበው ጉባኤ ፓርቲውን እና የክልሉን ህዝብ አደጋ ላይ የሚከት ነው ሲሉም አስታውቀዋል።

ፓርቲው ህጋዊ እውቅና እንዲያገኝ ለብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተጻፈው ደብዳቤም ይሁን በህወሓት ስም የሚደረጉ የጉባኤ እንቅስቃሴዎች ፓርቲውን የማይወክሉ እና የአንድ ቡድን ህገወጥ እንቅስቃሴ በመሆናቸው እንደማልቀበለው ላሳውቅ እወዳለሁ ብለዋል።

ምንጭ ፣ አዲስ ስታንዳርድ

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ግንደወይን የ14 ሰዎች ህይወት አለፈ

ከግንደወይን ከተማ ወደ ባህርዳር ሲጓዝ የነበረ የህዝብ ማመላለሻ መኪና መንገድ ስቶ ወንዝ ዉስጥ በመግባቱ የ14 ሰዎች ህይወት አለፈ።

ከሟቾቹ መካከል የሁለቱ አስከሬን የተገኘ ሲሆን መኪናዉን ጨምሮ የሌሎች ሰዎች አስከሬን እስካሁኑ ሰዓት ድረስ አልተገኘም።

ከምስራቅ ጎጃም ዞን ግንደወይን ከተማ ነሀሴ 2/2016 ዓ,ም መነሻዉን አድርጎ ወደ ባህርዳር  ሲጓዝ የነበረ  ኮድ 3. 21757 አማ አነስተኛ የህዝብ ተሽከርካሪ መኪና በሁለት እጁ እነሴ ወረዳ አብያ የሚባል ወንዝ ላይ ከረፋዱ 4.00 ሰዓት አካባቢ መንገድ ስቶ በመግባቱ ሾፌሩን ጨምሮ የ14 ግለሰቦች ህይወት ሲያልፍ በሁለት ሰዎች ላይ ከባድ ጉዳት ደርሷል።

አደጋ ከደረሰበት ወንዝ ዉስጥ የሁለቱን  ሰዎች አስከሬን ማግኘት የተቻለ ሲሆን የ12ቱን ሰዎች አስከሬንና መኪናዉን እስካሁን ማግኘት አለመቻሉን የጎንቻ ሲሶ እነሴ ወረዳ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አድርሷል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ህውሀት‼️

ህወሃት እንደ አዲስ ፓርቲ አልመዘገብም፣የቀድሞ ህጋዊ ሰውነቴ ይመለስልኝ በሚል ለምርጫ ቦርድ ያቀረበው ጥያቄ ምርጫ ቦርድ በልዩ ሁኔታ ተቀብሎታል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
2024/09/30 17:19:13
Back to Top
HTML Embed Code: