Telegram Web Link
Hamster‼️

ኢትዮጵያን ጨምሮ በተለያዩ የዓለም ሀገራት ላይ እየተዘዋወረ ያለው “ሃምስተር ኮምባት” ምንድነው ?

“ሃምስተር ኮምባት” (Hamster Kombat) ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በበርካቶች ዘንድ እየተዘወተረ የመጣ በቴሌግም ላይ የተመሰረተ ጨዋታ ሲሆን፤ ተጫዋቾቹ በየቀኑ ስክሪናቸውን በጣታቸው መታ መታ (ታፕ ታፕ) ሲያደርጉ ክሪፕቶ ሳንቲሞችን የሚያገኙበት ነው።
“ሃምስተር ኮምባት” (Hamster Kombat) ኢትዮጵያን ጨምሮ በተለያዩ የዓለም ሀገራት ላይ በበርካቶች እየተዘወተረ የመጣ ጨዋታም ሆኗል።

በቴሌግራም ላይ የተመሰረተው ሃምስተር ኮምባት በአለም አቀፍ ደረጃ 200 ሚሊዮን ተጫዋቾችን በማፍራት ከፍተኛ ተወዳጅነትን አግኝቷል።

ሃመስትር ኮምባት በቴልግራም ላይ የተመሰረተ ጨዋታ ሲሆን፤ ኤር ድሮፕ ሊሆኑ የሚችሉ ሳንቲሞችን (ኮይን) ተጫዋቾችን የሚሸልም የቴሌግራም ጨዋታ ነው። እንዲሁም ሰዎች በቴሌግራም ለይ ጓኞቻውን እየጋበዙ በርከት ያለ የክሪፕቶ ሳንቲሞችን ለመሰብሰብ በጋራ የሚጫወቱት ጨዋታ እንደሆነም ይነገራል።

ሃመስትር ኮምባት በቴልግራም ላይ የተመሰረተ ጨዋታ ሲሆን፤ ኤር ድሮፕ ሊሆኑ የሚችሉ ሳንቲሞችን (ኮይን) ተጫዋቾችን የሚሸልም የቴሌግራም ጨዋታ ነው። እንዲሁም ሰዎች በቴሌግራም ለይ ጓኞቻውን እየጋበዙ በርከት ያለ የክሪፕቶ ሳንቲሞችን ለመሰብሰብ በጋራ የሚጫወቱት ጨዋታ እንደሆነም ይነገራል።

ምናልባት ጨዋታ ብቻ ስለሆነ ዋናው ጥቅሙ ምንድነው? የሚል ጥያቄ ሊያስከትል ይችላል፤ ምንም እንኳን በአሁኑ ጊዜ ጨዋታ ቢሆንም፣ በሃመስተር ኮምባት የሰበሰብናቸው ሳንቲች (ኮይኖች) ኤርድሮፕ የመሆን ዝግጅት እንዳለ ነው የሚነገረው።

ይህ ማለትም በዚህ ጨዋታ ሳንቲሞችን (ኮይን) የሰበሰቡ ተጫዋቾች በቲ.ጂ.ኢ (ቶከን ጄኔሬሽን ኢቨንት) ወቅት ለኤር ድሮፕ ብቁ የመሆን እንደል አላቸው። ሳንቲሞቹ አስተዳዳሪዎች ያዋጣል ብለው ያመኑትን ማንኛውንም ተመን በመጠቀም ወደ ቶከን ይቀየራሉ፤ ስለዚህ “ሃምስተር ኮምባት” (Hamster Kombat) መጫወት ከጉዳቱ ጥቅሙ ያመዝናል ነው የተባለው።

ሃምስተር ኮምባት ህጋዊ ወይስ ማጭበርበሪያ ዘዴ ነው?

“ሃምስተር ኮምባት” (Hamster Kombat) በክሪፕቶ ገንዘብ ተፈጥሮ ምክንያት ህጋዊ ወይም ማጭበርበሪያ ዘዴ ነው ብሎ ለመደምደም የሚያስችል ምንም መንገድ የለም። ነገር ግን ሃምስተር ኮምባት ጠቃሚ ነገር ሊሆን እንደሚችል የሚጠቁሙ ምልክቶች አሉ የተባለ ሲሆን፤ ከእነዚህም አንዱ ማሳያዎ እንደ “BingX” ካሉ ልውውጦች ጋር ስትራቴጂካዊ አጋርነት መፍጠሩ ነው።

ይህ ማለት ወደፊት በ”BingX” ልውውጥ ላይ የሃምተርን ተመዝግቦ ልናይ እንችላል፤ ነገርግን አሁን ማድረግ ያለብን ማመን እና ጨዋታውን መጫወት ብቻ ነው። ተለዋዋጭ በሆነው እና ተገማች ባልሆነው በክሪፕቶ ዓለም ውስጥ ማድረግ የምንችለው እንድ ነገር ወይ አምኖ መጫወት አሊያም መተው ብቻ ነው።

መረጃው የ አል አይን ኒውስ ነው

መጀመር የምፈልጉ ደሞ በዚ Link መጀመር ትችላላቹ👇👇
https://www.tg-me.com/hamsTer_kombat_bot/start?startapp=kentId5355126428
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በአንዳንድ አገልግሎቶቹ ላይ ከሀምሌ 19 ቀን 2016 ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረግ የአገልግሎት ክፍያ ማሻሻያ ማድረጌን እወቁልኝ ብሏል።

ዝርዝሩ ከላይ ተቀምጧል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ፍትሕ ሚንስቴር ሕወሃት በልዩ ኹኔታ እንዲመዘገብ ለምርጫ ቦርድ ጥያቄ ማቅረቡን ከምርጫ ቦርድ መስማቱን ጠቅሶ ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዘግቧል።

ምርጫ ቦርድ፣ ሕወሓት በሰሜኑ ጦርነት ወቅት በአመጻ ተግባር ላይ ተሳትፏል በማለት ሕጋዊ ሰውነትቱን የሰረዘው በጥር 2013 ዓ፣ም ነበር።

ፍትሕ ሚንስቴር ሕወሓት “በልዩ ኹኔታ እንደ ፖለቲካ ፓርቲ ለመመዝገብ እንዲችል ቦርዱ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግ ከኹለት ቀናት በፊት በደብዳቤ መጠየቁን ዘገባው አመልክቷል።

ቦርድ የሚንስቴሩን ጥያቄ በሥራ ላይ ካሉ ሕጎች አንጻር መርምሮ ውሳኔ እንደሚሰጥ ተናግሯል ተብሏል።

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በቅርቡ ያሻሻለው የምርጫና ፖለቲካ ፓርቲዎችን አዋጅ፣ በአመጽ ተግባር በመሠማራታቸው ሕጋዊ ሰውነታቸው የተሰረዘባቸው የፖለቲካ ፓርቲዎች ወደ ሰላማዊ እንቅስቃሴ ለመመለሳቸው ማረጋገጫ ከሰጡ በድጋሚ እንዲመዘገቡ የሚፈቅድ አዋጅ ማጽደቁ ይታወሳል።

@sheger_press
@sheger_press
#አስተያየት የፍትህ ሚኒስትሩ ትናንት በንብረት ማስመለስ ህጉ ዙሪያ የሰጡት ማብራሪያ ከመልስ ይልቅ ብዙ ጥያቄዎችን የሚያጭር ሆኖ አግኝቼዋለሁ

(በቢንያም እሸቱ የተፃፈ)/

ከሁሉ በላይ ግርም ያለኝ የወንጀል ህግን መሰረታዊ መርሆ በተለይም ህግ ወደ ሗላ ተመልሶ እንደማይሰራ የሚደነግገውን (The principle of legality, specifically its non-retrospective 'or non-retroactive' aspect, that laws should not apply to actions that occurred before the law was enacted) የሚጣረዝ ህግን ተቀባይነት ያለው አሰራር ለማስመሰል የተጠቀሙት አገላለጽ ነው።

እንደ ፍትህ ሚኒስትሩ ማብራሪያ የንብረት ማስመለስ ረቂቅ አዋጅ ከያዛቸው 57 አንቀጾች ውስጥ 52 የሚሆኑት ከጸደቀበት ቀን ወደፊት ብቻ የሚፈጸሙ ሲሆን4 ወይም 5 የሚሆኑት አንቀጾች ብቻ ወደኋላ ሄደው ተፈፃሚ ይሆናሉ።

በሶስት አህጉራት (በኢትዮጵያ፣ በእንግሊዝና በአሜሪካ) በተማርኳቸው [የህግ] ትምህርቶች የአንቀፆች ይዘት እንጂ ብዛት ቁመነገር እንደሌለው ተገንዝቤያለሁ ።
Elias Meseret

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
Forwarded from Sheger Press️️
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
አያት አክሲዮን ማሕበር

የአክሲዮን እና ቤት ሽያጭ

አያት ዞን ሁለት ; ሦስት እና ሲኤምሲ አፓርተማዎችን ለሽያጭ አቅርበናል። እንዲሁም "8" እህት ኩባንያዎችን ያካተተዉ እና 51.38% አመታዊ ትርፍ ያከፋፈለዉ አያት "አክሲዮን"በመሸጥ ላይ ነዉ።

አያት የተሰማራባቸው የስራ ዘርፎች

በሪል ስቴት ግንባታና ልማት

በሆቴል እና ቱሪዝም(ራስ& ሮሃ ሆቴል)

በማርብል ማምረቻ ኢንዱስትሪ፣

በጠጠር ማምረቻ ኢንዱስትሪ

በብሎኬት ማምረቻ ኢንዱስትሪ

በእንጨትና ብረታብረት ምርቶች

በትምህርት ኢንቨስትመንት

በፋይናንሻል ኢንቨስትመንት

የትርፍ አከፋፈል ሂደቱ ከ2011 ጀምሮ

በ2011 - 26%

በ2012 - 27%

በ2013 - 31%

በ2014 - 44%

በ2015 - 51.38%

በ2015 የ1,000,000 አክሲዮን የነበራቸዉ 513,000 ብር አትርፈዋል።

የ500,000 የነበራቸዉ ደግሞ....250,000 ብር አትርፈዋል።

ለበለጠ መረጃ... 09-12-62-24-04
ምርጫ ቦርድ፣ ለፖለቲካ ፓርቲዎች ለሚሰጠው የገንዘብ ድጎማ ድልድል ከ10 ሺህ እስከ 900 ሺህ ሴት እና አካል ጉዳተኛ አባል አለን ያሉ 11 ፓርቲዎች እስከ ትናንት ድረስ ማስረጃ ሊያቀርቡለት እንዳልቻሉ አስታውቋል።

ቦርዱ ለፖለቲካ ፓርቲዎች የገንዘብ ድጎማ ድልድል ለማድረግ በመስፈርትነት የሚጠቀመው፣ ፓርቲዎች ያላቸውን የሴት እና አካል ጉዳተኛ አባላት ብዛት ነው።

በተያዘው ዓመት ከ10 ሺህ እስከ 900 ሺህ ሴት እና አካል ጉዳተኛ አባላት አሉን ብለው ለቦርዱ ሪፖርት ካደረጉት ፓርቲዎች መካከል፣ ብልጽግና ፓርቲ፣ አብን፣ ኦብነግ እና ዓረና ትግራይ ይገኙበታል።

ቦርዱ፣ ፓርቲዎቹ በቀጣዮቹ ሰባት ቀናት ማስረጃ ካላቀረቡ ሕጋዊ ርምጃ እወስዳለኹ በማለት አስጠንቅቋል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ዶክተር ቴዎድሮስ አድሃኖም የክብር ዶክትሬት ተሰጣቸው

የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ቴዎድሮስ አድሃኖም በቆጵሮስ ኒኮሲያ ከሚገኘው የህክምና ዩኒቨርሲቲ የክብር ዶክትሬት ተሰጣቸው። ዋና ዳይሬክተሩ ለሽልማቱ አድናቆታቸውን ገልጸው "የጤና ባለሙያዎች በቅንነት የሚያገለግሉ ከሆነ በአለም ላይ ትልቅ ለውጥ ከማምጣት የሚያግዳቸው ነገር የለም" ብለዋል።

@ethio_mereja_news
ለልማታዊ መዋጮ በሚል መምህራን ሳይመክሩበት ከደመወዛቸው እየተቆረጠባቸው ነው ተባለ‼️

የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር መምህራን ሳይመክሩበት እና ሳይጠየቁ ለልማታዊ መዋጮ እየተባለ ከደመወዛቸው እየተቆረጠባቸው ነው ሲል ቅሬታውን ገልጿል።

ይህ እየተፈጸመ ያለው በተለያዩ ክልሎች ያሉ መምህራን ላይ እንደሆነ የማህበሩ ምክትል ፕሬዚዳንት ሽመልስ አበበ ለአራዳ ተናግረዋል።

ለመንገድ ግንባታ አዋጡ ፣ ለልማት እየተባለ ከመምህራን ደመወዝ የሚቆረጠው መዋጮ እንደማንኛውም የህብረተሰብ ክፍል ተጠይቀው እና አምነውበት ሊሆን እንደሚገባም ነው የተናገሩት።

በክልሎች የሚገኙ መምህራን ከጊዜ ወደ ጊዜ ችግራቸው እየተበራከተ መጥቷል ያሉት አቶ ሽመልስ ማግኘት ያለባቸውን የአቅም ማሳደጊያ፣ የደረጃ እድገት እና መሰል ጥቅማ ጥቅሞቻቸውንም እየተከለከሉ መሆኑን ገልጸዋል።

በተጨማሪም አሁን ባለው የደመወዝ መጠን የኑሮ ውድነትን መቋቋም ያቃታቸው መምህራን ይባስ ብሎ የሶስት እና የአራት ወር ደመወዛቸው ያልተከፈላቸው የደቡብ፣ የአፋር እና የአማራ ክልል መምህራን እንዳሉም አስረድተዋል።

ችግሩን ለመቅረፍ ክልሎችን ብናናግርም ተገቢውን ምላሽ እየሰጡን አይደለም ብለዋል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
አነጋጋሪው የትራምፕ እና የባይደን ክርክር

የአሁኑ እና የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ባይደን እና ዶናልድ የትራምፕ ትናንት ምሽት በመጭው ህዳር ለሚደረገው ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ክርክር አድርገዋል።

የዲሞክራቲክ ፓርቲው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን እና የሪፐብሊካን ፓርቲው ፕሬዚዳንታዊ እጩ ዶናልድ ትራምፕ ትናንት ሐሙስ ምሽት በአትላንታ ባደረጉት የ2024 ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ክርክር ስደት እና ኢኮኖሚን ጨምሮ ሌሎች በርካታ ጉዳዮች ተነስተዋል።

አሜሪካውያን በቀጥታ የቴሌቪዥን ስርጭት በተመለከቱት በዚህ የመጀመሪያ ክርክር ፤የ78 ዓመቱ ዶናልድ ትራምፕ የ81 የዕድሜ ካላቸው ጆ ባይደን የዕድሜ ልዩነታቸው ብዙ ባይሆንም፤ የበለጠ ንቁ ሆነው ታይተዋል።

በክርክሩ ፕሬዝዳንት ባይደን ሃሳባቸውን ለመግለጽ ተቸግረው እና የጀመሩትን አርፈተ ነገር እንኳ መጨረስ አቅቷቸው መታየቱ ብዙዎችን አነጋግሯል።ለ90 ደቂቃ በዘለቀው ክርክር ባይደን ቃላቶች እየጠፏቸው ሃሳባቸውን መግለጽ ሲያቅታቸው ተስተውሏል ከዚህ አንፃር በክርክሩ ትራምፕ ባይደንን በልጠው ታይተዋል።

ጆ ባይደን በተጫናቸው እርጅና ሳቢያ አሜሪካን በፕሬዚዳንትነት ለተጨማሪ አራት ዓመታት መምራት ስለመቻላቸው በርካታ አሜሪካውያን ሲጠራጠሩ የቆዩ ሲሆን፤ የትናንት ምሽቱ የምርጫ ክርክር የአሜሪካውያኑን ስጋት ከፍ አድርጎታል።(ዶቼ ቬሌ)

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ያለፍቃዳችን ከደመወዛችን 1000 ብር ተቆረጠብን‼️

#ጋምቤላ ዙሪያ ወረዳ የሚሰሩ የመንግስት ሰራተኞች ህጋዊ ባልሆነ መንገድ 1000 ብር እና ከዚያ በላይ ተቆርጦብናል ሲሉ በርካታ ሰዎች ጥቆማ አድርሰውኛል። 

ለምንድነው ብለን ብንጠይቅ ለትግራይ ክልል መልሶ ማቋቋምና በአማራ ክልል ውጊያ ውስጥ ለሚገኘው የመከላከያ ሰራዊት ድጋፍ የሚውል ነው ሲሉ ምላሽ ሰጥተውናል ብለዋል።

ለምን የእኛ ፍቃደኝነት ሳትጠይቁን ስንላቸው ከፈለጋችሁ እናስወጣችኋለን፣ይሄ እኮ የመንግስት ብር ነው ከኪሳችሁ የሚወጣ አይደለም የሚል መልስ ሰጥተውናል ብለዋል። ከዚህ በተጨማሪ የወር ደመወዝ የሚከፈለን 15-20 ቀን ዘግይቶ ነው ብለዋል።

በህጉ መሰረት የአንድ የመንግሥት ሰራተኛ ደመወዝ ተቀናሽ የሚሆነው ወይም ሊቆረጥ የሚችለው በፍርድ ቤት ትዕዛዝ እና በሰራተኛው ፍቃድ ብቻ እንደሆነ ያስረዳል።

@ethio_mereja_news
መራጮች ላይ ጫና አሳድረዋል

ኢሰመኮ ዕሁድ'ለት ድጋሚ ምርጫ በተካሄደባቸው ክልሎች የቀበሌና የወረዳ አመራሮች እንዲኹም የገዥው ብልጽግና ፓርቲ አባላት በምርጫ ጣቢያዎች ውስጥ መራጮች ላይ ጫና በሚያሳድር ኹኔታ ድምጽ ሰጪዎችን በመመዝገብና በማነጋገር ድርጊቶች ላይ ተሠማርተው መታዘቡን አስታውቋል።

ኢሰመኮ፣ በአብዛኛዎቹ ምርጫ ጣቢያዎች ውስጥ ወይም ከምርጫ ጣቢያዎች በ500 ሜትር አቅራቢያ የደንብ ልብስ የለበሱ የጸጥታ አካላት ሲንቀሳቀሱ መመልከቱን ገልጧል።

በሶማሌ ክልል በጅግጅጋ እንዲኹም በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በመስቃን እና ማረቆ ምርጫ ክልሎች በግለሰቦች መኖሪያ ቤቶችና በኃይማኖት ተቋም ትምህርት ቤት ውስጥ አምስት የምርጫ ጣቢያዎች ተቋቁመው እንደነበርም ኢሰመኮ ገልጧል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን “የመንግሥት ኃይሎች”  ‘ሰላማዊ ሰዎችን’ እንደገደሉ ነዋሪዎችን ዋቢ አድርጎ ቢቢሲ አማርኛ ዘግቧል።

ጥቃቱ ሰኔ 19/ 2016 ዓ/ም መፈፀሙ የተነገረ ሲሆን፤ ቢያንስ 15 ንጹሃን ሰዎች መገደላቸው ተነግሯል።

በሰሜን ሸዋ ዞን ጣርማ በር ወረዳ ከደብረ ሲና ከተማ ወጣ ብላ በምትገኝ ሾላ ሜዳ በተባለች አነስተኛ የገጠር ከተማ ሰኔ 19 በመንግሥት ኃይሎች ደርሷል በተባለ ጥቃት ቢያንስ 15 ሰዎች መገደላቸውን እና አራት የሚሆኑ ሰዎች መቁሰላቸውን ነዋሪዎቹ ነግረውኛል ብሏል።

በከተማዋ ‘አጋም በር መገንጠያ’ በተባለ ሰፈር ጥቃቱ በዕለቱ 11፡30 አካባቢ እንደተፈጸመ አንድ ከጥቃቱ የተረፉ እማኝ፤ በጥቃቱ በአብዛኛው ማዳበሪያ ለመውሰድ ከተለያዩ ቀበሌዎች የመጡ አርሶ አደሮች እንደተገደሉ ለጣቢያው ገልጸዋል።

ከመንግስት አካላት መረጃ ለማግኘት ያደረኩት ሙከራ አልተሳካም ሲል ከመንግስት በኩል መካተት የነበረበት ምላሽ እንዳልተካተተ ዘገባው ጨምሯል።

በአማራ ክልል በሰኔ ወር መጀመሪያ ቀናት በምዕራብ ጎጃም እና ምስራቅ ጎጃም ዞኖች “በመንግሥት ኃይሎች” ተፈጽሟል በተባለ ጥቃት ከ20 በላይ ሰዎች መገደላቸው ይታወሳል።

@ethio_mereja_news
አማራ ክልል በመንግስት የፀጥታ ኃይሎችና በፋኖ ኃይሎች መካከል አመት በሞላው ግጭት ሳቢያ:-
ከ12 እስከ 13 ቢሊዮን ብር የሚገመት ንብረት ወድሟል።
ንጹሃን ተገድለዋል።
ከ3 ነጥብ 6 ሚሊዮን በላይ ህጻናት ከትምህርት ገበታ ዉጭ ሆነዋል።
የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ክፉኛ ተጎድቷል።
የግልና የመንግስት ተቋማት ከቦታ ቦታ መንቀሳቀስ ባለምቻላቸው ምክንያት የአገልግሎት አሰጣጥ ከፉኛ ተዛብቷል።
ነፍሰጡር እናቶች በአግባቡ የአምቡላንስና የወላድ አገልግሎት አያገኙም።
እናቶችና ህጻናት ከጦርነት ተሳትፎ ዉጭ የሆኑ የክልሉ ዜጎች ለከፋ የስነ ልቦና ጫና ተዳርገዋል።
እገታ ተስፋፍቷል።
ዜጎች ያለከልካይ በጠራራ ጸሃይ ይዘረፋሉ፤ ይገደላሉ።
ታላላቅ ፕሮጀከቶች ተስተጓጉለዋል።
ሕዝቡ ለሁለት ወገን ግብርና ቀረጥ ይከፍላል እና ሌሎች መሰል ጉዳዮች ግጭቱ ካመጣቸው መዘዞች በጥቂቱ ናቸው ሲል የእርቅና ድርድር አመቻች ካውንስል ዛሬ በሰጠው መግለጫ አስረድቷል።

(wasu mehammed)

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
በሀይል ሊመጣ የሚችል ድል እንደሌለ በትግራይ፣ በኦሮሚያ እና በአማራ ክልሎች በተካሄዱ እና አሁንም እየተካሄዱ ባሉ ግጭቶች አይተናል፣ በዚህ መልኩ የሚመጣ ድል ቢኖርም ዘላቂነቱ አጠራጣሪ ነው።

ስለዚህ ይህ ካውንስል አሁን ላይ ያወጣውን መግለጫ ሁሉም አካላት በበጎ በማየት እና ጦርነቱን በሰላም ለመቋጨት ቁርጠኝነት በማሳየት ህዝቡን እንዲያሳርፉት ሁላችንም ድምፅ መሆን ይገባናል።

መሳርያ ይዞ የሚዋጉት አካላት ላይ እየደረሰ ያለውን ጉዳት ሳይጨምር ባለፉት ጥቂት ቀናት ብቻ ታጣቂዎች የሚፈፅሙትን የደፈጣ ጥቃት ተከትሎ በወታደሮች በተፈፀሙ ጥቃቶች የሞቱ ዜጎች ቁጥር ከመቶ በላይ ሆኗል።

#Peace

EliasMeseret
@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ዩኒቨርሲቲዎች የቀጣይ ዓመት የምግብ በጀት ካልተስተካከለላቸው ተማሪዎችን መቀበል እንደማይችሉ አስታወቁ

ማረሚያ ቤቶችም ታራሚዎችን መመገብ እንደከበዳቸው ተነግሯል

በተለያዩ የአገሪቱ ከተሞች በመንግሥት ተገንብተው ተማሪዎችን በራሳቸው ወጪ እያስተናገዱ ያሉ ዩኒቨርሲቲዎች፣ እንዲሁም የፌደራል ማረሚያ ቤቶች በቀጣይ ዓመት የሚመደበው የምግብ በጀት ካልተስተካከለ ምግብ ማቅረብ አዳጋች እንደሚሆንባቸው አስታወቁ፡፡ዩኒቨርሰቲዎች ተማሪ ለመቀበል የማይችሉበት ደረጃ እንደሚደርሱ ተናግረዋል፡፡

መንግሥት በየዓመቱ መጨረሻ ለመጪው በጀት ዓመት ለተቋማት የሚደለድለውን ዓመታዊ በጀት ተከትሎ፣ በርካታ ዩኒቨርሲቲዎች ጥያቄ ሲያቀርቡበት የኖረውና ለአንድ ተማሪ የሚመደብ የአንድ ቀን ወጪ 22 ብር እስካሁን መልስ ማግኘት አልቻለም፡፡ በተመሳሳይ በማረሚያ ቤቶች ለታራሚዎች የሚቀርበው ገንዘብ በቂና ጥራት ያለው ምግብ ለማቅረብ መቸገራቸውን ገልጸዋል፡፡
(Reporter)

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ዝናቡ ስለሚያይል ጥንቃቄ ይደረግ

- የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት

በዘንድሮው ክረምት ከመደበኛ በላይ ዝናብ ሊያጋጥም ስለሚችል አደጋ እንዳይከሰት ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አሳሰበ።

በኢንስቲትዩቱ የሚቲዎሮሎጂ ትንበያና ቅድሚያ ማስጠንቀቂያ ምርምር ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አሳምነው ተሾመ (ዶ/ር) ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንዳስታወቁት፤ ከባድ የክረምት ዝናብ በሚፈጥረው “ላሊና” ምክንያት በቀጣይ ጊዜያት ከመደበኛ በላይ የሆነ የዝናብ መጠንና ሥርጭት ሊፈጠር ይችላል።

ከባድ የዝናብ ስርጭቱ ሊያስከትል የሚችለውን ጎርፍና መሰል ጉዳት ለመከላከል ተቋማት የቅድመ ዝግጅት ተግባራትን አጠናክረው መሥራት ይጠበቅባቸዋል ሲሉ አስረድተዋል።(EPA)

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
የመቀሌ ከተማ ፖሊስ ጽሕፈት ቤት ባለፉት 11 ወራት ውስጥ በከተማው 12 ሴቶች ተገድለው በድምሩ ከ4 ሺህ በላይ ወንጀሎች ተፈጽመዋል አለ።

ከሰሞኑን የዘጠኝ ወር ሪፖርት ተብሎ በተለያዩ ሚዲያዎች ሲሰራጭ የነበረው መረጃ የ11 ወራት ሪፖርት መሆኑን የከተማው ፖሊስ ጽህፈት ቤት አስታውቋል።

በ2016 ባለፉት 11 ወራት 4 ሺህ 340 ወንጀሎች የተመዘገቡ ሲሆን ወንጀሎቹ 7 ዓይነት ናቸው።
12 ሴቶች ሲገደሉ፣
80 የአስገድዶ መደፈር፣
1 ሺህ 953 የስርቆት፣
583 የድብደባ፣
178 የግድያ ሙከራ እንዲሁም
10 የጠለፋ ወንጀሎች መሆናቸውን የመቀሌ ከተማ ፖሊስ ገልጿል።

ወንጀሎችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ከ170 በላይ የማህበረሰብ አቀፍ የፖሊስ ሃይሎችን የማጠናከር ስራ እየተሰራ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን የህብረተሰቡ ተሳትፎ በእጅጉ ያስፈልጋል ተብሏል።

በቅርቡ በክልሉ ዋና ከተማ እና ሌሎችም አካባቢዎች በሴቶች ላይ የሚደርሰውን ግድያ እና አፈና ለማውገዝ ሰላማዊ ሰልፎች እንደተካሄዱ መዘገባችን አይዘነጋም።(wasu)

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
"የኢትዮጵያ ከሱማሌላንድ ጋር የገባችውን ስምምነት ካቋረጠች የሆብዮ ወደብ እንድትጠቀም እፈቅዳለሁ" የሞቃዲሾ አስተዳደር

በኢትዮጵያ እና በሶማሊያ መካከል የተፈጠረውን አለመግባባት ለመፍታት በቱርክ አስታራቂነት ሁለቱን ሀገራት በአንካራ የድርድር ጠረጴዛ ላይ መቀመጣቸው ተሰምቷል።

በኢትዮጵያ እና በሞቃዲሾ አስተዳደር መካከል በሚካሄደው ውይይት የጋራ ስምምነት ላይ ለመድረስ ሲሆን የውይይቱ አጀንዳ የኢትዮጵያና የሶማሌላንድ ስምምነት እና በቀጠናው ያለውን ዲፕሎማሲያዊ ቀውስ ያካትታል ተብሏል።

ዛሬ በአንካራ እየተካሄደ ይገኛል በተባለው ዉይይት የሶማሊያ ባለስልጣናት ኢትዮጵያ ከሶማሌ ላንድ ጋር የገባችውን ስምምነት ካቋረጠች ኢትዮጵያ በ ጋልሙዱግ ግዛት የሚገኘውን የሆብዮ ወደብ እንድትጠቀም አቅደዋል ነዉ የተባለዉ።

በሁለቱም ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች አማካኝነት በጠረጴዛ የተቀመጡት ሀገራቱ ኢትዮጵያ ከሞቃዲሾ አስተዳደር ጋር ስምምነት ላይ ከደረሰች እና ወደ የሆብዮ ወደብ ካቀናች በቀጣናው ያላትን ተፅዕኖ የበለጠ እንደምታሳድግ ይጠበቃል።
Capital

@ethio_mereja_news
በአማራ ክልል “ድጋሚ ግብር ካልከፈላችሁ ማዳበሪያ አታገኙም” የተባሉ አርሶ አደሮች የዘር ጊዜ ሊያልፍባቸው ነው😭

ግጭት ባለባቸው የአማራ ክልል አካባቢዎች ለሁለት ወገን ግብር እንዲከፍሉ የተገደዱ አርሶ አደሮች “ግብር ካልከፈላችሁ ማዳበሪያ አታገኙም” መባላቸውን ለዋዜማ ተናግረዋል።

በአማራ ክልል ግጭት ባለባቸው አካባቢዎች አርሶ አደሮች የግብርና ማዳበሪያ ለማግኘት ግብር መክፈል እንደግዴታ በመቀመጡና ግብር እንክፈል ሲሉ የሚሰበስብ አካል በመጥፋቱ የአዝመራው ወቅት ሊያልፋቸው መሆኑንም ያስረዳሉ።

አርሶ አደሮቹ በተለይ የፋኖ ታጣቂዎች በሚንቀሳቀሱባቸው አካባቢዎች ታጣቂዎቹ አስቀድመው ግብር እየሰበሰቡ መቆየታቸውን ገልፀው፣ ድጋሚ ለመንግስት ግብር ከፍለው ማዳበሪያ ለማግኘት የጠየቁ አርሶ አደሮች ግብር የሚሰበስብ አካል አለማግኘታቸውን ነግረውናል።

“አርሶ አደሩ ማዳበሪያ እንዲቀርብለት በድጋሚ ግብር ለመክፈል ቢስማማም…..ማን ሰብስቦ ማን ያድረስው? ” ሲሉ ዋዜማ ያነጋገረቻቸው አርሶ አደሮች በዘር ወቅት ችግር ላይ መውደቃቸውን ገልጠዋል፡፡
በአንዳንድ ታጣቂዎች በተቆጣጠሯቸው አካባቢዎች አርሶ አደሩ ቀድሞ የማዳበሪያ መግዣ ገንዘብ ሰብስቦ ከላከ በኋላ አቅርቦት በትንሹ ተጀምሮ ነበር።

በመንግሥት በኩል ማዳበሪያ ሳይቀርብላቸው የዘር ወቅት የደረሰባቸው አርሶ አደሮች አቅርቦት ካላቸው አጎራባች አካባቢዎች ከነጋዴ በውድ ዋጋ እየገዙ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በመንግስት በኩል 4ሺህ ሁለት መቶ ብር የሚሸጠውን ማዳበሪያ ከግለሰብ ነጋዴዎች በስምንት ሺህ ስምንት መቶ ብር ለመግዛት እንደተገደዱ አርሶ አደሮቹ ይናገራሉ።
በዘንድሮው አመት የአማራ ክልል ስምንት ሚሊየን ኩንታል ማዳበሪያ ቢገዛም ወደ ክልሉ የደረሰው አራት ሚሊየን ስምንት መቶ ሺህ ኩንታል ብቻ ነው። ከዚህም ወስጥ የተወሰነው በግለሰብ ነጋዴ እጅ መግባቱ ለአርሶ አደሩ ችግሩን አወሳስቦበታል።

ዋዜማ የአርሶ አደሮቹን ጥያቄ ይዛ የክልሉን ግብርና ቢሮ ጠይቃለች፡፡
የቀረቡት ችግሮች ክልሉ ካለበት ሁኔታ አንጻር በተለያዩ ክፍተቶች የተፈጠሩ መሆናቸውን የክልሉ ግብርና ቢሮ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አምሳሉ ጎባው ለዋዜማ ገልጸዋል፡፡ የፋኖ ታጣቂዎች ወጣ ገባ በሚሉባቸውና በተቆጣጠሯቸው አካባቢዎች አርሶ አደሩ ገጥሞኛል ላለው ግብርን እንደ መያዣ አድርጎ ማዳበሪያ አለማቅረብ “እንደዚያ ሊገጥም ይችላል” ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡

ለዚሁ ችግር “አመራር ሁሉ አንድ አይደለም” በማለት የየአካባቢውን አመራር ተጠያቂ ያደረጉት ቃል አቀባዩ፣ አርሶ አደሩ ግብር ካልከፈልክ ማዳበሪያ አታገኝም መባሉ ስተት ነው ብለዋል፡፡

ቢሮው “ግብረናንን ተንተርሶ ግብር፣ የስፖርት፣ የቀይ መስቀል” የሚባሉ ክፍያዎችን ማዳበሪያን እንደ መያዣ አድርጎ መሰብሰብ አይቻልም የሚል መመሪያ መስጠቱን ገልጠዋል፡፡ ችግሩ የተከሰተባቸው አካባቢዎች የሚገኙ አርሶ አደሮች ችግሩን ለግብርና ቢሮ ሪፖርት ማድረግ እንደሚችሉም ጠቁመዋል፡፡
ከአቅርቦት እጥረት ጋር በተያያዘ የቀረበውን ቅሬታ “እንኳንም ክልሉ በቀውስ ውስጥ ሆኖ በማንኛውም ሁኔታ ይከሰታል” በማለት አርሶ አደሮች ያነሱት እጥረት አምነዋል፡፡

ቃል አቀባዩ ማዳበሪያ በነጋዴ እጅ ስለመግባቱ በሰጡት ምላሽ “በወሬ ደረጃ ይባላል” በማለት ለቀረበው ቅሬታ የጸጥታ አካሉን ተጠያቂ አድርገዋል፡፡ ስለ ሁኔታው ሲስረዱም “ግብርና እጃችን ላይ ያለው እስኪብርቶና ወረቀት ነው፣ ሕግ የምናስከበርበት አቅም የለንም” ብለዋል፡፡ ግብርና ቢሮ ዋና ሚናው አቀርቦት መሆኑን የጠቆሙት ቃል አቀባዩ ቢሮው ያቀረበው ማዳበሪያ “አቅርቦቱን ሕገ ወጥ ሲወስደው ፖሊስ የት አለ?” ሲሉም ጠይቀዋል፡፡ [ዋዜማ]

@ethio_mereja_news
ቱርክ፣ ኢትዮጵያንና ሱማሊያን በባሕር በር ውዝግባቸው ዙሪያ ዛሬ አንካራ ውስጥ እንዳደራደረች ከባለሥልጣናት ምንጮች መስማቱን ጠቅሶ ሮይተርስ ዘግቧል።

ኾኖም ኹለት ለድርድሩ ቅርብ የኾኑ ምንጮች የድርድሩ ግብ ምን እንደኾነ ግልጽ እንዳልኾነና ከድርድሩ ኹነኛ ውጤት የመገኘቱ እድሉ ዝቅተኛ መኾኑን መናገራቸውን ዘገባው አመልክቷል።

የኢትዮጵያ፣ ሱማሊያና ቱርክ ባለሥልጣናት በቱርክ-መራሹ ድርድር ዙሪያ አስተያየት ከመስጠት እንደተቆጠቡ ዜና ምንጩ ገልጧል። የሶማሊላንድ ራስ ገዝ መንግሥት ቃል አቀባይ ግን፣ ሶማሊላንድ በቱርክ አደራዳሪነት በሚካሄደው ድርድር ውስጥ ተሳታፊ እንዳልኾነች ተናግረዋል ተብሏል።

የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር፣ ከሱማሊያ ጋር በቱርክ አመቻቺነት ዛሬ ይደረጋል ስለተባለው ንግግር ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ሰዓት ድረስ ያለው ነገር የለም። 

@ethio_mereja_news
2024/09/30 17:17:11
Back to Top
HTML Embed Code: