🕊
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ
አምላክ፡፡ አሜን፡፡ †
[ † ግንቦት ፳፪ [ 22 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት † ]
🕊 † ቅዱስ እንድራኒቆስ † 🕊
ቅዱስ ወብጹእ እንድራኒቆስ ሐዋርያ ትውልዱ ነገዱ ከቤተ እሥራኤል ሲሆን ከ፸፪ [72] ቱ አርድእት አንዱ ነው:: ጌታችን በመዋዕለ ስብከቱ ፻፳ [120] ቤተሰቦቹን ሲመርጥ እርሱን ከአርድእት ጋር ደምሮ አስተምሮታል::
ሰብዐው አርድእት በጌታችን ተልከው አጋንንት ሲገዙላቸው ከእነርሱ አንዱ ቅዱስ እንድራኒቆስ ነበር:: ይሕ የተፈጸመ ገና መድኃኔ ዓለም ከመሰቀሉ በፊት ነው:: [ሉቃ.፲፥፩-፳] (10:1-20)
ቅዱሱ ከጌታችን ዕርገት በኋላ ከሐዋርያት ጋር ለ፲ [10] ቀናት በሱባኤ ሰንብቶ የመንፈስ ቅዱስን ሐብት ተቀብሏል:: እንደ ባልንጀሮቹም ወደ ዓለም ወጥቶ የወንጌል የምሥራችን ሰብኳል:: በተለይ ከቅዱስ ዻውሎስ ጋር ለበርካታ ዓመታት አምላኩን አገልግሏል:: ቅዱስ ዻውሎስም በቆረንቶስ እያለ ቅዱስ እንድራኒቆስ በሮም ያስተምር ነበር:: ለዛም ነው በሮሜ መልዕክቱ ፲፮፥፯ [16:7] ላይ "እንድራኒቆስን ሰላም በሉ" ያለው::
ቅዱስ ዻውሎስ በሰማዕትነት ካረፈ በኋላ ከቅዱስ ዮልዮስ ጋር ሆነው የአህዛብን ልቡና በወንጌል አብርተዋል:: እጅግ ብዙ መከራ ደርሶባቸዋል:: ከእግዚአብሔር በተሰጣቸው ትዕግስት ድል ነሥተዋል:: በዚሕም በርካታ የጣኦት ቤቶችን አፍርሰው አብያተ ክርስታያናትን አንጸዋል:: በአሕዛብም ፊት ድንቅ ድንቅ ተአምራትን አሳይተዋል::
ቅዱስ እንድራኒቆስ ብዙ መከራን ቢቀበልም አንገቱን ይቆረጥ ዘንድ የጌታ ፈቃዱ አልነበረምና ጥቂት ታሞ በዚሕች ቀን አርፏል:: ባልንጀራው [ሐዋርያው] ቅዱስ ዮልዮስ በክብር ገንዞ ቀብሮታል::
† 🕊 ቅዱስ ያዕቆብ 🕊 †
ዳግመኛ በዚሕ ቀን ጻድቅና ተአማኒ [ታማኝ] የተባለ የምሥራቅ ሰው ቅዱስ ያዕቆብ መታሠቢያ ይደረግለታል::
ቅዱስ ያዕቆብ ቁስጥንጥንያ አካባቢ በርሃ ውስጥ ይኖር የነበረ አባት ነው:: ከቅድሰና ሕይወቱ ባሻገር በደፋርነቱ [ ጥብዐቱ ] ይታወቃል:: በ፫፻፵ [ 340 ] ዎቹ ዓ/ም ታናሹ ቆስጠንጢኖስ አርዮሳዊ በሆነ ጊዜ ይሔ አባት በይፋ ገስጾታል:: በዚህም ምክንያት መከራ ተቀብሏል: ታስሯል: ተገርፏል:: እግዚአብሔርም መናፍቁን ንጉሥ ለጦርነት በወጣበት ቀስፎታል::
የአባቶቻችን አምላክ ልዑለ ባሕርይ ክርስቶስ ጸጋ ክብራቸውን ያድለን::
[ † ግንቦት ፳፪ [ 22 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅዱስ እንድራኒቆስ ሐዋርያ [ከ፸፪ [72] ቱ አርድእት]
፪. ቅዱስ ያዕቆብ ምሥራቃዊ [ለክርስቶስ የታመነ]
[ † ወርኃዊ በዓላት ]
፩፡ ቅዱስ ዑራኤል ሊቀ መላእክት
፪፡ ቅዱስ ደቅስዮስ
፫፡ ቅዱስ ዮልዮስ ሰማዕት
፬፡ ቅዱስ ሉቃስ ወንጌላዊ
፭፡ አባ እንጦንስ አበ መነኮሳት
፮፡ አባ ጳውሊ የዋህ
" ስለ እናንተ ብዙ ለደከመች ለማርያ ሰላምታ አቅርቡልኝ:: በሐዋርያት መካከል ስመ ጥሩዎች ለሆኑ: ደግሞም ክርስቶስን በማመን ለቀደሙኝ: አብረውኝም ለታሰሩ ለዘመዶቼ ለአንድራኒቆንና ለዮልያን [እንድራኒቆስና ዮልዮስ] ሰላምታ አቅርቡልኝ:: " + [ሮሜ.፲፮፥፮] (16:6)
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ
አምላክ፡፡ አሜን፡፡ †
[ † ግንቦት ፳፪ [ 22 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት † ]
🕊 † ቅዱስ እንድራኒቆስ † 🕊
ቅዱስ ወብጹእ እንድራኒቆስ ሐዋርያ ትውልዱ ነገዱ ከቤተ እሥራኤል ሲሆን ከ፸፪ [72] ቱ አርድእት አንዱ ነው:: ጌታችን በመዋዕለ ስብከቱ ፻፳ [120] ቤተሰቦቹን ሲመርጥ እርሱን ከአርድእት ጋር ደምሮ አስተምሮታል::
ሰብዐው አርድእት በጌታችን ተልከው አጋንንት ሲገዙላቸው ከእነርሱ አንዱ ቅዱስ እንድራኒቆስ ነበር:: ይሕ የተፈጸመ ገና መድኃኔ ዓለም ከመሰቀሉ በፊት ነው:: [ሉቃ.፲፥፩-፳] (10:1-20)
ቅዱሱ ከጌታችን ዕርገት በኋላ ከሐዋርያት ጋር ለ፲ [10] ቀናት በሱባኤ ሰንብቶ የመንፈስ ቅዱስን ሐብት ተቀብሏል:: እንደ ባልንጀሮቹም ወደ ዓለም ወጥቶ የወንጌል የምሥራችን ሰብኳል:: በተለይ ከቅዱስ ዻውሎስ ጋር ለበርካታ ዓመታት አምላኩን አገልግሏል:: ቅዱስ ዻውሎስም በቆረንቶስ እያለ ቅዱስ እንድራኒቆስ በሮም ያስተምር ነበር:: ለዛም ነው በሮሜ መልዕክቱ ፲፮፥፯ [16:7] ላይ "እንድራኒቆስን ሰላም በሉ" ያለው::
ቅዱስ ዻውሎስ በሰማዕትነት ካረፈ በኋላ ከቅዱስ ዮልዮስ ጋር ሆነው የአህዛብን ልቡና በወንጌል አብርተዋል:: እጅግ ብዙ መከራ ደርሶባቸዋል:: ከእግዚአብሔር በተሰጣቸው ትዕግስት ድል ነሥተዋል:: በዚሕም በርካታ የጣኦት ቤቶችን አፍርሰው አብያተ ክርስታያናትን አንጸዋል:: በአሕዛብም ፊት ድንቅ ድንቅ ተአምራትን አሳይተዋል::
ቅዱስ እንድራኒቆስ ብዙ መከራን ቢቀበልም አንገቱን ይቆረጥ ዘንድ የጌታ ፈቃዱ አልነበረምና ጥቂት ታሞ በዚሕች ቀን አርፏል:: ባልንጀራው [ሐዋርያው] ቅዱስ ዮልዮስ በክብር ገንዞ ቀብሮታል::
† 🕊 ቅዱስ ያዕቆብ 🕊 †
ዳግመኛ በዚሕ ቀን ጻድቅና ተአማኒ [ታማኝ] የተባለ የምሥራቅ ሰው ቅዱስ ያዕቆብ መታሠቢያ ይደረግለታል::
ቅዱስ ያዕቆብ ቁስጥንጥንያ አካባቢ በርሃ ውስጥ ይኖር የነበረ አባት ነው:: ከቅድሰና ሕይወቱ ባሻገር በደፋርነቱ [ ጥብዐቱ ] ይታወቃል:: በ፫፻፵ [ 340 ] ዎቹ ዓ/ም ታናሹ ቆስጠንጢኖስ አርዮሳዊ በሆነ ጊዜ ይሔ አባት በይፋ ገስጾታል:: በዚህም ምክንያት መከራ ተቀብሏል: ታስሯል: ተገርፏል:: እግዚአብሔርም መናፍቁን ንጉሥ ለጦርነት በወጣበት ቀስፎታል::
የአባቶቻችን አምላክ ልዑለ ባሕርይ ክርስቶስ ጸጋ ክብራቸውን ያድለን::
[ † ግንቦት ፳፪ [ 22 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅዱስ እንድራኒቆስ ሐዋርያ [ከ፸፪ [72] ቱ አርድእት]
፪. ቅዱስ ያዕቆብ ምሥራቃዊ [ለክርስቶስ የታመነ]
[ † ወርኃዊ በዓላት ]
፩፡ ቅዱስ ዑራኤል ሊቀ መላእክት
፪፡ ቅዱስ ደቅስዮስ
፫፡ ቅዱስ ዮልዮስ ሰማዕት
፬፡ ቅዱስ ሉቃስ ወንጌላዊ
፭፡ አባ እንጦንስ አበ መነኮሳት
፮፡ አባ ጳውሊ የዋህ
" ስለ እናንተ ብዙ ለደከመች ለማርያ ሰላምታ አቅርቡልኝ:: በሐዋርያት መካከል ስመ ጥሩዎች ለሆኑ: ደግሞም ክርስቶስን በማመን ለቀደሙኝ: አብረውኝም ለታሰሩ ለዘመዶቼ ለአንድራኒቆንና ለዮልያን [እንድራኒቆስና ዮልዮስ] ሰላምታ አቅርቡልኝ:: " + [ሮሜ.፲፮፥፮] (16:6)
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
🕊
[ † እንኩዋን ለቅዱሳን ሐዋርያት ዮልዮስና አፍሮዲጡ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ † ]
🕊 † ዮልዮስ ወአፍሮዲጡ ሐዋርያት † 🕊
ቅዱሳን ሐዋርያትና አርድእት በቁጥር ፹፬ [84] ቢሆኑም በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ታሪኩ በዝርዝር የተጻፈለት ቅዱስ ዻውሎስ ነው:: የሌሎቹ አልፎ አልፎ የተጠቀሰ ሲሆን ከግማሽ በላይ የሚሆኑት ግን የት እንደ ደረሱም አልተጻፈም::
በዚሕ ምክንያት ወደድንም ጠላንም አዋልድ መጻሕፍትን መጠቀማችን አይቀርም:: ምክንያቱም "ሑሩ ወመሐሩ" ያላቸው ሁሉንም ሐዋርያትና አርድእት ነውና::
የቅዱሳን ሐዋርያትን ሕይወት ከያዙ ቅዱሳት መጻሕፍት መካከል በቀዳሚነት ዜና ሐዋርያትና ገድለ ሐዋርያት የሚጠቀሱ ሲሆን ስንክሳራችንም አልፎ አልፎ ያወሳቸዋል:: በዚሕም መሠረት ዛሬ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ከ72ቱ አርድእት የሚቆጠሩትን ቅዱስ ዮልዮስንና ቅዱስ አፍሮዲጡን ታከብራለች::
ሁለቱም ከጌታችን እግር ሥር ለ፫ [3] ዓመታት ተምረው: በበዓለ ሃምሳ መንፈስ ቅዱስን ተቀብለው: ከባልንጀሮቻቸው ሐዋርያት ጋር ለወንጌል አገልግሎት ሃገራትን ዙረዋል:: በሐዋርያት ሲኖዶስም ዽዽስናን ተሹመዋል::
በአገልግሎት በነበሩባቸው የእስያና አውሮዻ ሃገራት አእላፍ ነፍሳትን ወደ ሕይወት ሲማርኩ ግፍን በአኮቴት ተቀብለዋል:: ከጌታቸውም የማይጠፋ የሕይወት አክሊልን ተቀዳጅተዋል::
በተለይ ቅዱስ ዮልዮስ ከቅዱስ ዻውሎስ ጋር መከራን በመቀበሉ በሮሜ መልዕክቱ ፲፮፥፯ [16:7] ላይ አወድሶታል:: ከቅዱስ እንድራኒቆስ ጋርም በጣም ይዋደዱ ነበርና ትናንት እርሱን ገንዞ ቀብሮ በእንባ ወደ ጌታው ፀለየ:: ጌታችንም በማግስቱ [ማለትም ዛሬ] አሳርፎታል::
አምላከ ቅዱሳን ከሐዋርያቱ ትጋትና በረከት ያድለን::
🕊
[ † ግንቦት ፳፫ [ 23 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅዱስ ዮልዮስ [ዮልያን] ሐዋርያ [ከ፸፪ [72] ቱ አርድእት]
፪. ቅዱስ አፍሮዲጡ ሐዋርያ [ከ፸፪ [72] ቱ አርድእት]
፫. ቅዱሱ ሕጻን ሰማዕት [በዘመነ ሰማዕታት ገና የ፪ [2] ወር ሕጻን ቢሆንም ጌታችን አፉን ከፍቶለት ክርስቲያን ነኝ በማለቱ ከእናቱ ጋር ተሠይፏል]
፬. አባ አንስያ ሰማዕት
፭. ቅዱስ ታኦድራጦስ
[ † ወርኀዊ በዓላት ]
፩. ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት
፪. ቅዱስ ጊዮርጊስ ሊቀ ሰማዕታት
፫. ቅዱስ ሰሎሞን ንጉሠ እስራኤል
፬. አባ ጢሞቴዎስ ገዳማዊ
፭. አባ ሳሙኤል
፮. አባ ስምዖን
፯. አባ ገብርኤል
" ስለ እናንተ ብዙ ለደከመች ለማርያ ሰላምታ አቅርቡልኝ:: በሐዋርያት መካከል ስመ ጥሩዎች ለሆኑ: ደግሞም ክርስቶስን በማመን ለቀደሙኝ: አብረውኝም ለታሰሩ ለዘመዶቼ ለአንድራኒቆንና ለዮልያን [እንድራኒቆስና ዮልዮስ] ሰላምታ አቅርቡልኝ:: " [ ሮሜ.፲፮፥፮ ] (16:6)
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
[ † እንኩዋን ለቅዱሳን ሐዋርያት ዮልዮስና አፍሮዲጡ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ † ]
🕊 † ዮልዮስ ወአፍሮዲጡ ሐዋርያት † 🕊
ቅዱሳን ሐዋርያትና አርድእት በቁጥር ፹፬ [84] ቢሆኑም በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ታሪኩ በዝርዝር የተጻፈለት ቅዱስ ዻውሎስ ነው:: የሌሎቹ አልፎ አልፎ የተጠቀሰ ሲሆን ከግማሽ በላይ የሚሆኑት ግን የት እንደ ደረሱም አልተጻፈም::
በዚሕ ምክንያት ወደድንም ጠላንም አዋልድ መጻሕፍትን መጠቀማችን አይቀርም:: ምክንያቱም "ሑሩ ወመሐሩ" ያላቸው ሁሉንም ሐዋርያትና አርድእት ነውና::
የቅዱሳን ሐዋርያትን ሕይወት ከያዙ ቅዱሳት መጻሕፍት መካከል በቀዳሚነት ዜና ሐዋርያትና ገድለ ሐዋርያት የሚጠቀሱ ሲሆን ስንክሳራችንም አልፎ አልፎ ያወሳቸዋል:: በዚሕም መሠረት ዛሬ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ከ72ቱ አርድእት የሚቆጠሩትን ቅዱስ ዮልዮስንና ቅዱስ አፍሮዲጡን ታከብራለች::
ሁለቱም ከጌታችን እግር ሥር ለ፫ [3] ዓመታት ተምረው: በበዓለ ሃምሳ መንፈስ ቅዱስን ተቀብለው: ከባልንጀሮቻቸው ሐዋርያት ጋር ለወንጌል አገልግሎት ሃገራትን ዙረዋል:: በሐዋርያት ሲኖዶስም ዽዽስናን ተሹመዋል::
በአገልግሎት በነበሩባቸው የእስያና አውሮዻ ሃገራት አእላፍ ነፍሳትን ወደ ሕይወት ሲማርኩ ግፍን በአኮቴት ተቀብለዋል:: ከጌታቸውም የማይጠፋ የሕይወት አክሊልን ተቀዳጅተዋል::
በተለይ ቅዱስ ዮልዮስ ከቅዱስ ዻውሎስ ጋር መከራን በመቀበሉ በሮሜ መልዕክቱ ፲፮፥፯ [16:7] ላይ አወድሶታል:: ከቅዱስ እንድራኒቆስ ጋርም በጣም ይዋደዱ ነበርና ትናንት እርሱን ገንዞ ቀብሮ በእንባ ወደ ጌታው ፀለየ:: ጌታችንም በማግስቱ [ማለትም ዛሬ] አሳርፎታል::
አምላከ ቅዱሳን ከሐዋርያቱ ትጋትና በረከት ያድለን::
🕊
[ † ግንቦት ፳፫ [ 23 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅዱስ ዮልዮስ [ዮልያን] ሐዋርያ [ከ፸፪ [72] ቱ አርድእት]
፪. ቅዱስ አፍሮዲጡ ሐዋርያ [ከ፸፪ [72] ቱ አርድእት]
፫. ቅዱሱ ሕጻን ሰማዕት [በዘመነ ሰማዕታት ገና የ፪ [2] ወር ሕጻን ቢሆንም ጌታችን አፉን ከፍቶለት ክርስቲያን ነኝ በማለቱ ከእናቱ ጋር ተሠይፏል]
፬. አባ አንስያ ሰማዕት
፭. ቅዱስ ታኦድራጦስ
[ † ወርኀዊ በዓላት ]
፩. ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት
፪. ቅዱስ ጊዮርጊስ ሊቀ ሰማዕታት
፫. ቅዱስ ሰሎሞን ንጉሠ እስራኤል
፬. አባ ጢሞቴዎስ ገዳማዊ
፭. አባ ሳሙኤል
፮. አባ ስምዖን
፯. አባ ገብርኤል
" ስለ እናንተ ብዙ ለደከመች ለማርያ ሰላምታ አቅርቡልኝ:: በሐዋርያት መካከል ስመ ጥሩዎች ለሆኑ: ደግሞም ክርስቶስን በማመን ለቀደሙኝ: አብረውኝም ለታሰሩ ለዘመዶቼ ለአንድራኒቆንና ለዮልያን [እንድራኒቆስና ዮልዮስ] ሰላምታ አቅርቡልኝ:: " [ ሮሜ.፲፮፥፮ ] (16:6)
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
🕊
[ † እንኩዋን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ የስደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ † ]
የአርያም ንግሥት: የፍጥረታት ሁሉ እመቤት ድንግል ማርያም የባሕርይ አምላክ ልጇን አዝላ በዚህች ቀን ወደ ምድረ ግብፅ ወርዳለች::
በወንጌል ላይ [ማቴ.፪፥፩-፲፰] (2:1-18) እንደተጻፈው ጌታችን በተወለደ በ፪ [2] ዓመቱ የጥበብ ሰዎች [ሰብአ ሰገል] ወደ ቤተ ልሔም መጥተው ሰግደውለት: ወርቅ እጣን ከርቤውን ገበሩ: አገቡለት::
ንጉሥ ተወልዷል መባሉን የሰማ ሔሮድስ መቶ አርባ አራት ሺህ 144,000 ሕጻናትን ሲፈጅ በቅዱስ ገብርኤል ትዕዛዝ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ፩ [1] አምላክ ልጇን አዝላ: በአንዲት አህያ ጥቂት ስንቅ ቁዋጥራ: ከዮሴፍና ከሰሎሜ ጋር ስደት ወጣች::
ከገሊላ ተነስታ በጭንቅ በመከራ: በረሃብና በጥም: በሐዘንና በድካም: በላበትና በእንባ ተጉዛ በዚሕች ቀን ምድረ ግብፅ ገብታለች::
- የአምላክ እናቱ
- እሳትን አዝላ በብርድ ተንገላታለች::
- ለእኛ የሕይወት እንጀራን ተሸክማ እርሷ ተራበች::
- የሕይወትን ውሃ ተሸክማ ተጠማች::
- የሕይወት ልብስን ተሸክማ ተራቆተች::
- የሕይወት ፍስሐን ተሸክማ አዘነች::
- እመ አምላክ ተራበች: ተጠማች: ታረዘች: ደከመች: አዘነች: አለቀሰች: እግሯ ደማ: ተንገላታች::
ለሚገባው ይሕ ሁሉ የተደረገው ለእኛ ድኅነት ነው:: በእውነት ይህንን እያወቀ ለድንግል ማርያም ክብር የማይሰጥ ሰይጣን ብቻ ነው:: አራዊት: ዕፀዋትና ድንጋዮች እንኩዋ ለአመላክ እናት ክብር ይሰጣሉ::
አረጋዊው ቅዱስ ዮሴፍና ቅዱስ ሰሎሜ ደግሞ የክብር ክብር ይገባቸዋል:: ከአምላክ እናት ከድንግል ማርያምና ከቸር ልጇ ጋር መከራ መቀበልን መርጠዋልና::
መድኃኔ ዓለም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለምን ተሰደደ? ለምንስ ስደቱን ወደ ግብፅና ኢትዮዽያ አደረገ?
፩. ትንቢቱን ይፈጽም ዘንድ:: በፈጣን ደመና ወደ ግብፅ እንደሚወርድ ተነግሯልና [ኢሳ.፲፱፥፩ 19:1, ዕን.፫፥፯ 3:7]
፪. ምሳሌውን ለመፈጸም:: የሥጋ አባቶቹ እነ አብርሃም: ያዕቆብ [እሥራኤል]: ኤርምያስ ወደዚያው ተሰደዋልና::
፫. ከግብፅ ጣዖት አምልኮን ያጠፋ ዘንድ:: [ኢሳ.፲፱፥፩] (19:1)
፬. የግብፅና የኢትዮዽያ ገዳማትን ይቀድስ ዘንድ::
፭. ሰው መሆኑ በአማን እንጂ ምትሐት እንዳልሆነ ለማጠየቅ:: ሰው ባይሆን ኑሮ አይሰደድም ነበርና:: ሔሮድስ ቢያገኘው ደግሞ ሊገድለው አይችልም:: ያለ ፈቃዱና ያለ ዕለተ ዐርብ ደሙ አይፈስምና::
፮. ስደትን ለሰማዕታት ባርኮ ለመስጠት:: እና
፯. የአዳምን ስደት በስደቱ ለመካስ ነው::
ቸሩ መድኃኔ ዓለም የድንግል እናቱን ስደት አስቦ ከመንግስተ ሰማያት ስደት ይሠውረን:: ከስደቱ በረከትም ያድለን::
🕊
[ † ግንቦት ፳፬ [ 24 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅዱስ ዕንባቆም ነቢይ
፪. ቅዱስ ዮሴፍ አረጋዊና ቅድስት ሰሎሜ
፫. ቅዱስ አብቁልታ ሰማዕት
፬. ቅዱስ አልዓዛር ካህን [የአሮን ልጅ]
[ † ወርኀዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት
፪. ቅዱስ አጋቢጦስ [ጻድቅ ኤዺስቆዾስ]
፫. ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ
፬. ቅዱስ ሙሴ ፀሊም
፭. ቅዱስ ቶማስ ዘመርዐስ
፮. ቅዱስ አብላርዮስ ታላቁ
፯. "፳፬ 24ቱ" ካኅናተ ሰማይ [ሱራፌል]
፰. አቡነ ዘዮሐንስ ጻድቅ [ኢትዮዽያዊ]
" ዘንዶውም ሴቲቱ በወለደች ጊዜ ሕጻኑዋን እንዲበላ ልትወልድ ባላት ሴት ፊት ቆመ:: አሕዛብንም ሁሉ በብረት ዘንግ ይገዛቸው ዘንድ ያለውን ልጅ: ወንድ ልጅ ወለደች:: ልጇም ወደ እግዚአብሔርና ወደ ዙፋኑ ተነጠቀ:: ሴቲቱም ሺህ ከሁለት መቶ ስድሳ ቀን በዚያ እንዲመግቧት በእግዚአብሔር ተዘጋጅቶላት ወደ ነበረው ሥፍራ ወደ በረሃ ሸሸች:: " [ራዕይ.፲፪፥፬-፯] (12:4-7)
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
[ † እንኩዋን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ የስደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ † ]
የአርያም ንግሥት: የፍጥረታት ሁሉ እመቤት ድንግል ማርያም የባሕርይ አምላክ ልጇን አዝላ በዚህች ቀን ወደ ምድረ ግብፅ ወርዳለች::
በወንጌል ላይ [ማቴ.፪፥፩-፲፰] (2:1-18) እንደተጻፈው ጌታችን በተወለደ በ፪ [2] ዓመቱ የጥበብ ሰዎች [ሰብአ ሰገል] ወደ ቤተ ልሔም መጥተው ሰግደውለት: ወርቅ እጣን ከርቤውን ገበሩ: አገቡለት::
ንጉሥ ተወልዷል መባሉን የሰማ ሔሮድስ መቶ አርባ አራት ሺህ 144,000 ሕጻናትን ሲፈጅ በቅዱስ ገብርኤል ትዕዛዝ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ፩ [1] አምላክ ልጇን አዝላ: በአንዲት አህያ ጥቂት ስንቅ ቁዋጥራ: ከዮሴፍና ከሰሎሜ ጋር ስደት ወጣች::
ከገሊላ ተነስታ በጭንቅ በመከራ: በረሃብና በጥም: በሐዘንና በድካም: በላበትና በእንባ ተጉዛ በዚሕች ቀን ምድረ ግብፅ ገብታለች::
- የአምላክ እናቱ
- እሳትን አዝላ በብርድ ተንገላታለች::
- ለእኛ የሕይወት እንጀራን ተሸክማ እርሷ ተራበች::
- የሕይወትን ውሃ ተሸክማ ተጠማች::
- የሕይወት ልብስን ተሸክማ ተራቆተች::
- የሕይወት ፍስሐን ተሸክማ አዘነች::
- እመ አምላክ ተራበች: ተጠማች: ታረዘች: ደከመች: አዘነች: አለቀሰች: እግሯ ደማ: ተንገላታች::
ለሚገባው ይሕ ሁሉ የተደረገው ለእኛ ድኅነት ነው:: በእውነት ይህንን እያወቀ ለድንግል ማርያም ክብር የማይሰጥ ሰይጣን ብቻ ነው:: አራዊት: ዕፀዋትና ድንጋዮች እንኩዋ ለአመላክ እናት ክብር ይሰጣሉ::
አረጋዊው ቅዱስ ዮሴፍና ቅዱስ ሰሎሜ ደግሞ የክብር ክብር ይገባቸዋል:: ከአምላክ እናት ከድንግል ማርያምና ከቸር ልጇ ጋር መከራ መቀበልን መርጠዋልና::
መድኃኔ ዓለም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለምን ተሰደደ? ለምንስ ስደቱን ወደ ግብፅና ኢትዮዽያ አደረገ?
፩. ትንቢቱን ይፈጽም ዘንድ:: በፈጣን ደመና ወደ ግብፅ እንደሚወርድ ተነግሯልና [ኢሳ.፲፱፥፩ 19:1, ዕን.፫፥፯ 3:7]
፪. ምሳሌውን ለመፈጸም:: የሥጋ አባቶቹ እነ አብርሃም: ያዕቆብ [እሥራኤል]: ኤርምያስ ወደዚያው ተሰደዋልና::
፫. ከግብፅ ጣዖት አምልኮን ያጠፋ ዘንድ:: [ኢሳ.፲፱፥፩] (19:1)
፬. የግብፅና የኢትዮዽያ ገዳማትን ይቀድስ ዘንድ::
፭. ሰው መሆኑ በአማን እንጂ ምትሐት እንዳልሆነ ለማጠየቅ:: ሰው ባይሆን ኑሮ አይሰደድም ነበርና:: ሔሮድስ ቢያገኘው ደግሞ ሊገድለው አይችልም:: ያለ ፈቃዱና ያለ ዕለተ ዐርብ ደሙ አይፈስምና::
፮. ስደትን ለሰማዕታት ባርኮ ለመስጠት:: እና
፯. የአዳምን ስደት በስደቱ ለመካስ ነው::
ቸሩ መድኃኔ ዓለም የድንግል እናቱን ስደት አስቦ ከመንግስተ ሰማያት ስደት ይሠውረን:: ከስደቱ በረከትም ያድለን::
🕊
[ † ግንቦት ፳፬ [ 24 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅዱስ ዕንባቆም ነቢይ
፪. ቅዱስ ዮሴፍ አረጋዊና ቅድስት ሰሎሜ
፫. ቅዱስ አብቁልታ ሰማዕት
፬. ቅዱስ አልዓዛር ካህን [የአሮን ልጅ]
[ † ወርኀዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት
፪. ቅዱስ አጋቢጦስ [ጻድቅ ኤዺስቆዾስ]
፫. ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ
፬. ቅዱስ ሙሴ ፀሊም
፭. ቅዱስ ቶማስ ዘመርዐስ
፮. ቅዱስ አብላርዮስ ታላቁ
፯. "፳፬ 24ቱ" ካኅናተ ሰማይ [ሱራፌል]
፰. አቡነ ዘዮሐንስ ጻድቅ [ኢትዮዽያዊ]
" ዘንዶውም ሴቲቱ በወለደች ጊዜ ሕጻኑዋን እንዲበላ ልትወልድ ባላት ሴት ፊት ቆመ:: አሕዛብንም ሁሉ በብረት ዘንግ ይገዛቸው ዘንድ ያለውን ልጅ: ወንድ ልጅ ወለደች:: ልጇም ወደ እግዚአብሔርና ወደ ዙፋኑ ተነጠቀ:: ሴቲቱም ሺህ ከሁለት መቶ ስድሳ ቀን በዚያ እንዲመግቧት በእግዚአብሔር ተዘጋጅቶላት ወደ ነበረው ሥፍራ ወደ በረሃ ሸሸች:: " [ራዕይ.፲፪፥፬-፯] (12:4-7)
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
🕊
[ † እንኳን ለእናታችን ቅድስት ሰሎሜ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል እና ለበዓለ ቅዱስ ሜሮን በሰላም አደረሳችሁ † ]
† 🕊 ቅድስት ሰሎሜ 🕊 †
የክብር ባለቤት መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመዋዕለ ስብከቱ ከመረጣቸው ፴፮ [36] ቱ ቅዱሳት አንስት የቅድስት ሰሎሜን ያሕል ያገለገለ: ክብርም የተቀበለ የለም:: ከእመቤታችን ቀጥሎ ከጽንሰቱ እስከ ዕርገቱ ያልተለየች ብቸኛዋ ሰው ናትና::
ይሕስ እንደ ምን ነው ቢሉ:- ቅድስት ሰሎሜ ከነገደ አሮን በሚመዘዝ የዘር ሐረግ እናቷ ማርያም ትባል ነበር:: አባቷ ደግሞ ክቡር አረጋዊ ቅዱስ ዮሴፍ ነው:: ቅድስት ሰሎሜና እመቤታችን የእህትማማች ልጆች ናቸው::
ቅድስት ኤልሳቤጥም ዝምድናዋ ተመሳሳይ ነው:: የ ፫ [3] ቱ እናቶች [ሐና: ማርያምና ሶፍያ] የማጣትና የሔርሜላ ልጆች በመሆናቸው እህታማቾች ናቸው::
"ጥቂት ነገሮች ስለ እናታችን ቅድስት ሰሎሜ "
፩. የአረጋዊ ዮሴፍ ልጆችን [ወንድሞቿን] እንደሚገባ አሳድጋለች::
፪. ጌታችን በተወለደ ጊዜ በቤተ ልሔም ነበረች:: የእመቤታችን መውለድ እንደ ሌሎች ሴቶች መስሏት ድንግልን ስለ ነካች እጆቿ ተቃጥለዋል:: ምሕረት ጠይቃ ጌታን ስትዳስሰው ግን ተፈወሰች::
፫. እመ ብርሃን ስደት ስትወጣ ቅድስት ሰሎሜ "ባንቺ የደረሰ በኔም ይድረስ" ብላት አብራ ተሰዳለች:: ረሐቧን ተርባለች:: ጥሟን ተጠምታለች:: በሐዘኗ አዝናለች:: አብራት አልቅሳለች:: ለ፫ [3] ዓመታት ከ፮ [6] ወራት ያን ሁሉ ጭንቅ አብራ ተካፍላለች::
ድንግል እመቤታችን እሾህ ሲወጋት ታወጣላት: እንቅፋት ሲመታት ደሟን ትጠርግላት ነበር:: ባለቤቱ አድሏታልና ጌታችንን አንዴ በጎኗ ታቅፈው: አንዴም በጀርባዋ ታዝለው: አንዳንዴም ትስመው ነበር::
"መለኮትን ማቀፍ: ማዘልና መሳም ምን ይደንቅ! ለቅድስት እናታችን አንክሮና ምስጋና በጸጋ ይገባል!"
ከስደት ከተመለሱ በሁዋላም ለ፳፭ [25] ዓመታት ከጌታና ከድንግል ማርያም ጋር ኑራለች: አገልግላቸዋለችም:: ጌታችን ተጠምቆ ማስተማር ሲጀምርም ተከተለችው:: እርሱም ከ፴፮ [36] ቱ ቅዱሳት አንስት ደምሯታል:: ለ፫ [3] ዓመታት ከ፮ [6] ወራት ከዋለበት ውላ: ካደረበት አድራ ተምራለች:: እንደሚገባም አገልግላለች::
አምላክ ሲሰቃይ ከጐኑ: ሲሰቀልም ከእግረ መስቀሉ ነበረች:: ብርሃነ ትንሳኤውም ከተገለጠላቸው ቅዱሳት አንስት አንዷ ናት:: ከመድኃኔ ዓለም ዕርገት በሁዋላ መንፈስ ቅዱስን ተቀብላ በሐዋርያት ዘመን የነበረችውን ቤተ ክርስቲያን አገልግላለች::
እድሜዋ ምን ቢገፋ ለወንጌልና ለማዕድ ተግባር ተግታለች:: ወገኖቿ አይሁድ ብዙ አሰቃይተዋት በዚህች ዕለት በመልካም ዕረፍት ወደ ፈጣሪዋ ሔዳለች::
† 🕊 ቅብዐ ሜሮን 🕊 †
ዳግመኛ በዚሕ ቀን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እኛ የምንከብርበትን ቅብዐ ሜሮን አፍልቆልናል::
በስደቱ ጊዜ ጌታችን በምድረ ግብፅ ደክሟቸው ካረፉበት ቦታ ላይ የዮሴፍ በትርን ቆራርጦ: በኪነ ጥበቡ ውሃ አፍልቆ: አጠጥቶ: ትልልቅ ዛፎች አደረጋቸው:: እዛውም ላይ ቅብዐ ሜሮንን አፈለቀ:: ቅብዐ በለሶንም ይሏቸዋል::
በሁዋላም የጌታችን ወዙ በታጠበ ጊዜ ተቀላቅሎበታል:: ዛሬ እኛም: ንዋየ ቅድሳትም የምንከብረው በዚሁ ቅዱስ ቅብዐት ነው::
አምላካችን እግዚአብሔር በቅድስት ሰሎሜ ላይ ያሳደረውን ጸጋ በእኛም ላይ ያሳድርልን::
🕊
[ † ግንቦት ፳፭ [ 25 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. እናታችን ቅድስት ሰሎሜ [ከ ፵፮ [36] ቱ ቅዱሳት አንስት]
፪. ታላቁ አባ ሔሮዳ ሰማዕት
፫. ፴ ሺህ "30,000" ሰማዕታት [የአባ ሔሮዳ ማሕበር]
፬. ቅዱስ አብቁልታ ሰማዕት
፭. ቅዱስ ቅብዐ ሜሮን
[ † ወርሐዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ መርቆሬዎስ ሰማዕት
፪. ቅድስት ቴክላ ሐዋርያዊት
፫. ቅዱስ አበከረዙን ሰማዕት
፬. ቅዱስ ዱማድዮስ ሶርያዊ
፭. አቡነ አቢብ [አባ ቡላ]
፮. ቅዱስ አባ አቡፋና ጻድቅ
" ሰንበትም ካለፈ በሁዋላ መግደላዊት ማርያም: የያዕቆብም እናት ማርያም: ሰሎሜም መጥተው ሊቀቡት ሽቱ ገዙ:: ከሳምንቱም በፊተኛው ቀን እጅግ በማለዳ ፀሐይ ከወጣ በሁዋላ ወደ መቃብር መጡ . . . ወደ መቃብርም ገብተው ነጭ ልብስ የተጐናጸፈ ጐልማሳ በቀኝ በኩል አዩና ደነገጡ:: እርሱ ግን አትደንግጡ የተሰቀለውን የናዝሬቱን ኢየሱስን ትፈልጋላችሁ:: ተነስቷል: በዚህ የለም . . . አላቸው:: " [ማር.፲፮፥፩-፰] (16:1-8)
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
[ † እንኳን ለእናታችን ቅድስት ሰሎሜ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል እና ለበዓለ ቅዱስ ሜሮን በሰላም አደረሳችሁ † ]
† 🕊 ቅድስት ሰሎሜ 🕊 †
የክብር ባለቤት መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመዋዕለ ስብከቱ ከመረጣቸው ፴፮ [36] ቱ ቅዱሳት አንስት የቅድስት ሰሎሜን ያሕል ያገለገለ: ክብርም የተቀበለ የለም:: ከእመቤታችን ቀጥሎ ከጽንሰቱ እስከ ዕርገቱ ያልተለየች ብቸኛዋ ሰው ናትና::
ይሕስ እንደ ምን ነው ቢሉ:- ቅድስት ሰሎሜ ከነገደ አሮን በሚመዘዝ የዘር ሐረግ እናቷ ማርያም ትባል ነበር:: አባቷ ደግሞ ክቡር አረጋዊ ቅዱስ ዮሴፍ ነው:: ቅድስት ሰሎሜና እመቤታችን የእህትማማች ልጆች ናቸው::
ቅድስት ኤልሳቤጥም ዝምድናዋ ተመሳሳይ ነው:: የ ፫ [3] ቱ እናቶች [ሐና: ማርያምና ሶፍያ] የማጣትና የሔርሜላ ልጆች በመሆናቸው እህታማቾች ናቸው::
"ጥቂት ነገሮች ስለ እናታችን ቅድስት ሰሎሜ "
፩. የአረጋዊ ዮሴፍ ልጆችን [ወንድሞቿን] እንደሚገባ አሳድጋለች::
፪. ጌታችን በተወለደ ጊዜ በቤተ ልሔም ነበረች:: የእመቤታችን መውለድ እንደ ሌሎች ሴቶች መስሏት ድንግልን ስለ ነካች እጆቿ ተቃጥለዋል:: ምሕረት ጠይቃ ጌታን ስትዳስሰው ግን ተፈወሰች::
፫. እመ ብርሃን ስደት ስትወጣ ቅድስት ሰሎሜ "ባንቺ የደረሰ በኔም ይድረስ" ብላት አብራ ተሰዳለች:: ረሐቧን ተርባለች:: ጥሟን ተጠምታለች:: በሐዘኗ አዝናለች:: አብራት አልቅሳለች:: ለ፫ [3] ዓመታት ከ፮ [6] ወራት ያን ሁሉ ጭንቅ አብራ ተካፍላለች::
ድንግል እመቤታችን እሾህ ሲወጋት ታወጣላት: እንቅፋት ሲመታት ደሟን ትጠርግላት ነበር:: ባለቤቱ አድሏታልና ጌታችንን አንዴ በጎኗ ታቅፈው: አንዴም በጀርባዋ ታዝለው: አንዳንዴም ትስመው ነበር::
"መለኮትን ማቀፍ: ማዘልና መሳም ምን ይደንቅ! ለቅድስት እናታችን አንክሮና ምስጋና በጸጋ ይገባል!"
ከስደት ከተመለሱ በሁዋላም ለ፳፭ [25] ዓመታት ከጌታና ከድንግል ማርያም ጋር ኑራለች: አገልግላቸዋለችም:: ጌታችን ተጠምቆ ማስተማር ሲጀምርም ተከተለችው:: እርሱም ከ፴፮ [36] ቱ ቅዱሳት አንስት ደምሯታል:: ለ፫ [3] ዓመታት ከ፮ [6] ወራት ከዋለበት ውላ: ካደረበት አድራ ተምራለች:: እንደሚገባም አገልግላለች::
አምላክ ሲሰቃይ ከጐኑ: ሲሰቀልም ከእግረ መስቀሉ ነበረች:: ብርሃነ ትንሳኤውም ከተገለጠላቸው ቅዱሳት አንስት አንዷ ናት:: ከመድኃኔ ዓለም ዕርገት በሁዋላ መንፈስ ቅዱስን ተቀብላ በሐዋርያት ዘመን የነበረችውን ቤተ ክርስቲያን አገልግላለች::
እድሜዋ ምን ቢገፋ ለወንጌልና ለማዕድ ተግባር ተግታለች:: ወገኖቿ አይሁድ ብዙ አሰቃይተዋት በዚህች ዕለት በመልካም ዕረፍት ወደ ፈጣሪዋ ሔዳለች::
† 🕊 ቅብዐ ሜሮን 🕊 †
ዳግመኛ በዚሕ ቀን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እኛ የምንከብርበትን ቅብዐ ሜሮን አፍልቆልናል::
በስደቱ ጊዜ ጌታችን በምድረ ግብፅ ደክሟቸው ካረፉበት ቦታ ላይ የዮሴፍ በትርን ቆራርጦ: በኪነ ጥበቡ ውሃ አፍልቆ: አጠጥቶ: ትልልቅ ዛፎች አደረጋቸው:: እዛውም ላይ ቅብዐ ሜሮንን አፈለቀ:: ቅብዐ በለሶንም ይሏቸዋል::
በሁዋላም የጌታችን ወዙ በታጠበ ጊዜ ተቀላቅሎበታል:: ዛሬ እኛም: ንዋየ ቅድሳትም የምንከብረው በዚሁ ቅዱስ ቅብዐት ነው::
አምላካችን እግዚአብሔር በቅድስት ሰሎሜ ላይ ያሳደረውን ጸጋ በእኛም ላይ ያሳድርልን::
🕊
[ † ግንቦት ፳፭ [ 25 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. እናታችን ቅድስት ሰሎሜ [ከ ፵፮ [36] ቱ ቅዱሳት አንስት]
፪. ታላቁ አባ ሔሮዳ ሰማዕት
፫. ፴ ሺህ "30,000" ሰማዕታት [የአባ ሔሮዳ ማሕበር]
፬. ቅዱስ አብቁልታ ሰማዕት
፭. ቅዱስ ቅብዐ ሜሮን
[ † ወርሐዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ መርቆሬዎስ ሰማዕት
፪. ቅድስት ቴክላ ሐዋርያዊት
፫. ቅዱስ አበከረዙን ሰማዕት
፬. ቅዱስ ዱማድዮስ ሶርያዊ
፭. አቡነ አቢብ [አባ ቡላ]
፮. ቅዱስ አባ አቡፋና ጻድቅ
" ሰንበትም ካለፈ በሁዋላ መግደላዊት ማርያም: የያዕቆብም እናት ማርያም: ሰሎሜም መጥተው ሊቀቡት ሽቱ ገዙ:: ከሳምንቱም በፊተኛው ቀን እጅግ በማለዳ ፀሐይ ከወጣ በሁዋላ ወደ መቃብር መጡ . . . ወደ መቃብርም ገብተው ነጭ ልብስ የተጐናጸፈ ጐልማሳ በቀኝ በኩል አዩና ደነገጡ:: እርሱ ግን አትደንግጡ የተሰቀለውን የናዝሬቱን ኢየሱስን ትፈልጋላችሁ:: ተነስቷል: በዚህ የለም . . . አላቸው:: " [ማር.፲፮፥፩-፰] (16:1-8)
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
🕊
[ † እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም : ቅዱስ ዑራኤል እና ለቅዱሳኑ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፣ አደረሰን። † ]
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †
🕊 † ድንግል እመቤታችን እና ቅዱስ ዑራኤል † 🕊
† በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ትውፊት መሠረት በዚህች ቀን ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ የሆነው ቅዱስ ዑራኤል :-
፩. ድንግል ማርያም በአካለ ሥጋ እያለች ወደ ሰማይ አሳርጓታል:: በሠረገላ ብርሃን ጭኖ: በክንፎቹም ተሸክሞ: አስቀድሞ ገነትን ቀጥሎም ሲዖልን አስጐብኝቷታል:: በዚህም ምክንያት እመ ብርሃን ስለ ኃጥአን የምታለቅስ: የምትለምንና የምትማልድ ሆናለች:: ለምናም አልቀረች የምሕረት ቃል ኪዳን ተቀብላለች::
፪. ቅዱሱ መልአክ እመ ብርሃንን በስደቷ ጊዜ ወደ ኢትዮጵያ መርቶ አምጥቷታል:: በክንፉ ተሸክሞ: በአራቱም አቅጣጫ አዙሮ አሳይቶ አሥራት እንድትቀበል አድርጓል::
፫. ጌታችን በተሰቀለ ጊዜ ደሙን በጽዋዕ አድርጐ በኢትዮጵያ ወንዞች ላይ አፍስሷል::
፬. ለብዙ ቅዱሳን [አባ ጊዮርጊስን ጨምሮ] ጽዋዐ ልቡናን አጠጥቷል::
🕊 † አቡነ በጸሎተ ሚካኤል ኢትዮጵያዊ † 🕊
† ወላጆቻቸው ማርቆስ እና እግዚእ ክብራ ይባላሉ:: ተአምራትን ገና ከእናታቸው ማኅጸን ጀምሮ ይሠሩ የነበሩት ጻድቁ በልጅነታቸው መጻሕፍትን ተምረው መንነዋል:: በስብከተ ወንጌልም ትግራይና አካባቢውን አድርሰዋል:: በነዚህም ጊዜያት ብዙ አርድእትን አፍርተዋል::
በጋስጫ ገዳም መስርተው የወንድና የሴት ብለውም ለይተዋል:: ሲጸልዩም ሆነ ሲያስተምሩ ተደሞ ይመጣባቸው የነበረ ሲሆን አንድ ቀን እባቡን ዓሣ አድርገው ደቀ መዛሙርትን አስደንቀዋል::
ከጾም: ከጸሎትና ከስግደት ባሻገር ከወቅቱ ንጉሥ ዓምደ ጽዮን መከራ በመቀበላቸው እንደ ሰማዕትም ይቆጠራሉ:: ከብዙ የገድል ዓመታት በኋላም በ1330 ዓ/ም በዚህች ቀን ትግራይ ውስጥ ዐርፈዋል:: በቆይታ ግን ወደ ጋስጫ ዐጽማቸው ፈልሷል::
🕊 † ቅዱስ ላዕከ ማርያም ኢትዮጵያዊ † 🕊
† ቅዱሱ የአፄ ናዖድ የልጅ ልጅ : የቅድስት ሮማነ ወርቅ ልጅ : የልብነ ድንግል የእህት ልጅና የገላውዴዎስ አጐት ነው:: በግራኝ አህመድ ዘመን ተማርኮ ወደ የመን : ከዛም ቱርክ ተወስዷል::
ሃይማኖቴን አልክድም ስላለ ብዙ አሰቃይተው : አባለ ዘሩን ቆርጠው ጃንደረባ አደረጉት:: በድንቅ ተአምር ግን ወደ ሃገሩ ተመለሰ:: እስከ ዕለተ ሞቱም ነዳያንን ሲያበላ ኑሮ ዛሬ ዐርፏል::
🕊 † ቅዱስ ሱስንዮስ † 🕊
በ5ኛው መቶ ክ/ዘመን የነበረ የኤፌሶን ሰው ሲሆን ጃንደረባም ነበር:: በ431 ዓ/ም ሁለት መቶውን የጉባዔ ኤፌሶን ሊቃውንት አገልግሎ በዛው ዓመት አርፏል:: ቅዱስ ቄርሎስ ገንዞ ቀብሮታል::
🕊 † ብጹዕ አወ ክርስቶስ † 🕊
ከተባረከች ሚስቱ ጋር በአንድ ቤት ውስጥ : ግን ደግሞ በድንግልና ኑረዋል:: ቀን ቀን እንግዳ ሲቀበሉ: ነዳያንን ሲያበሉ ውለው ሌሊት ሲገሰግዱና ሲጸልዩ ያድሩ ነበር:: ጌታችን ከሰማይ መስክሮላቸው ዛሬ ዐርፈዋል::
🕊 † ቅዱስ ዮራኖስ † 🕊
በሉቃስ ወንጌል ላይ [ሉቃ.፳፫፥፵፯] የምናገኘው የመቶ አለቃው ሲሆን በጌታችን ትንሣኤ ቀን የጠፋች ዓይኑ በርታለት በክርስቶስ አምኖ ለሰማዕትነት በቅቷል::
† ከእመቤታችን ድንግል ማርያም ጣዕሟን ፍቅሯን : ከቅዱሳኑ ሁሉ ጸጋ በረከትን እግዚአብሔር ያድለን::
🕊
[ † ሐምሌ ፳፩ [ 21 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅድስት ድንግል እግዝእትነ ማርያም ወላዲተ አምላክ
፪. ቅዱስ ዑራኤል ሊቀ መላእክት
፫. አቡነ በጸሎተ ሚካኤል ጻድቅ [ኢትዮጵያዊ]
፬. ቅዱስ ላዕከ ማርያም ሔር [ኢትዮጵያዊ]
፭. አቡነ ኤዎስጣቴዎስ [ኢትዮጵያዊ] ልደታቸው
፮. ብጹዕ አወ ክርስቶስና ሚስቱ [ጻድቃን]
፯. ቅዱስ ሱስንዮስ ጻድቅ
፰. ቅዱስ ዮራኖስ መኮንን [የመቶ አለቃው]
[ † ወርኀዊ በዓላት ]
፩. አበው ጎርጎርዮሳት
፪. አቡነ ምዕመነ ድንግል
፫. አቡነ አምደ ሥላሴ
፬. አባ አሮን ሶርያዊ
፭. አባ መርትያኖስ ጻድቅ
† "እንግዲህ ምን እላለሁ? ስለ ጌዴዎንና ስለ ባርቅ: ስለ ሶምሶንም : ስለ ዮፍታሔም : ስለ ዳዊትና ስለ ሳሙኤልም : ስለ ነቢያትም እንዳልተርክ ጊዜ ያጥርብኛልና:: እነርሱ በእምነት መንግሥታትን ድል ነሡ:: ጽድቅንም አደረጉ:: . . ." † [ዕብ.፲፩፥፴፪]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
[ † እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም : ቅዱስ ዑራኤል እና ለቅዱሳኑ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፣ አደረሰን። † ]
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †
🕊 † ድንግል እመቤታችን እና ቅዱስ ዑራኤል † 🕊
† በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ትውፊት መሠረት በዚህች ቀን ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ የሆነው ቅዱስ ዑራኤል :-
፩. ድንግል ማርያም በአካለ ሥጋ እያለች ወደ ሰማይ አሳርጓታል:: በሠረገላ ብርሃን ጭኖ: በክንፎቹም ተሸክሞ: አስቀድሞ ገነትን ቀጥሎም ሲዖልን አስጐብኝቷታል:: በዚህም ምክንያት እመ ብርሃን ስለ ኃጥአን የምታለቅስ: የምትለምንና የምትማልድ ሆናለች:: ለምናም አልቀረች የምሕረት ቃል ኪዳን ተቀብላለች::
፪. ቅዱሱ መልአክ እመ ብርሃንን በስደቷ ጊዜ ወደ ኢትዮጵያ መርቶ አምጥቷታል:: በክንፉ ተሸክሞ: በአራቱም አቅጣጫ አዙሮ አሳይቶ አሥራት እንድትቀበል አድርጓል::
፫. ጌታችን በተሰቀለ ጊዜ ደሙን በጽዋዕ አድርጐ በኢትዮጵያ ወንዞች ላይ አፍስሷል::
፬. ለብዙ ቅዱሳን [አባ ጊዮርጊስን ጨምሮ] ጽዋዐ ልቡናን አጠጥቷል::
🕊 † አቡነ በጸሎተ ሚካኤል ኢትዮጵያዊ † 🕊
† ወላጆቻቸው ማርቆስ እና እግዚእ ክብራ ይባላሉ:: ተአምራትን ገና ከእናታቸው ማኅጸን ጀምሮ ይሠሩ የነበሩት ጻድቁ በልጅነታቸው መጻሕፍትን ተምረው መንነዋል:: በስብከተ ወንጌልም ትግራይና አካባቢውን አድርሰዋል:: በነዚህም ጊዜያት ብዙ አርድእትን አፍርተዋል::
በጋስጫ ገዳም መስርተው የወንድና የሴት ብለውም ለይተዋል:: ሲጸልዩም ሆነ ሲያስተምሩ ተደሞ ይመጣባቸው የነበረ ሲሆን አንድ ቀን እባቡን ዓሣ አድርገው ደቀ መዛሙርትን አስደንቀዋል::
ከጾም: ከጸሎትና ከስግደት ባሻገር ከወቅቱ ንጉሥ ዓምደ ጽዮን መከራ በመቀበላቸው እንደ ሰማዕትም ይቆጠራሉ:: ከብዙ የገድል ዓመታት በኋላም በ1330 ዓ/ም በዚህች ቀን ትግራይ ውስጥ ዐርፈዋል:: በቆይታ ግን ወደ ጋስጫ ዐጽማቸው ፈልሷል::
🕊 † ቅዱስ ላዕከ ማርያም ኢትዮጵያዊ † 🕊
† ቅዱሱ የአፄ ናዖድ የልጅ ልጅ : የቅድስት ሮማነ ወርቅ ልጅ : የልብነ ድንግል የእህት ልጅና የገላውዴዎስ አጐት ነው:: በግራኝ አህመድ ዘመን ተማርኮ ወደ የመን : ከዛም ቱርክ ተወስዷል::
ሃይማኖቴን አልክድም ስላለ ብዙ አሰቃይተው : አባለ ዘሩን ቆርጠው ጃንደረባ አደረጉት:: በድንቅ ተአምር ግን ወደ ሃገሩ ተመለሰ:: እስከ ዕለተ ሞቱም ነዳያንን ሲያበላ ኑሮ ዛሬ ዐርፏል::
🕊 † ቅዱስ ሱስንዮስ † 🕊
በ5ኛው መቶ ክ/ዘመን የነበረ የኤፌሶን ሰው ሲሆን ጃንደረባም ነበር:: በ431 ዓ/ም ሁለት መቶውን የጉባዔ ኤፌሶን ሊቃውንት አገልግሎ በዛው ዓመት አርፏል:: ቅዱስ ቄርሎስ ገንዞ ቀብሮታል::
🕊 † ብጹዕ አወ ክርስቶስ † 🕊
ከተባረከች ሚስቱ ጋር በአንድ ቤት ውስጥ : ግን ደግሞ በድንግልና ኑረዋል:: ቀን ቀን እንግዳ ሲቀበሉ: ነዳያንን ሲያበሉ ውለው ሌሊት ሲገሰግዱና ሲጸልዩ ያድሩ ነበር:: ጌታችን ከሰማይ መስክሮላቸው ዛሬ ዐርፈዋል::
🕊 † ቅዱስ ዮራኖስ † 🕊
በሉቃስ ወንጌል ላይ [ሉቃ.፳፫፥፵፯] የምናገኘው የመቶ አለቃው ሲሆን በጌታችን ትንሣኤ ቀን የጠፋች ዓይኑ በርታለት በክርስቶስ አምኖ ለሰማዕትነት በቅቷል::
† ከእመቤታችን ድንግል ማርያም ጣዕሟን ፍቅሯን : ከቅዱሳኑ ሁሉ ጸጋ በረከትን እግዚአብሔር ያድለን::
🕊
[ † ሐምሌ ፳፩ [ 21 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅድስት ድንግል እግዝእትነ ማርያም ወላዲተ አምላክ
፪. ቅዱስ ዑራኤል ሊቀ መላእክት
፫. አቡነ በጸሎተ ሚካኤል ጻድቅ [ኢትዮጵያዊ]
፬. ቅዱስ ላዕከ ማርያም ሔር [ኢትዮጵያዊ]
፭. አቡነ ኤዎስጣቴዎስ [ኢትዮጵያዊ] ልደታቸው
፮. ብጹዕ አወ ክርስቶስና ሚስቱ [ጻድቃን]
፯. ቅዱስ ሱስንዮስ ጻድቅ
፰. ቅዱስ ዮራኖስ መኮንን [የመቶ አለቃው]
[ † ወርኀዊ በዓላት ]
፩. አበው ጎርጎርዮሳት
፪. አቡነ ምዕመነ ድንግል
፫. አቡነ አምደ ሥላሴ
፬. አባ አሮን ሶርያዊ
፭. አባ መርትያኖስ ጻድቅ
† "እንግዲህ ምን እላለሁ? ስለ ጌዴዎንና ስለ ባርቅ: ስለ ሶምሶንም : ስለ ዮፍታሔም : ስለ ዳዊትና ስለ ሳሙኤልም : ስለ ነቢያትም እንዳልተርክ ጊዜ ያጥርብኛልና:: እነርሱ በእምነት መንግሥታትን ድል ነሡ:: ጽድቅንም አደረጉ:: . . ." † [ዕብ.፲፩፥፴፪]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖