Telegram Web Link
ዙል–ሒጃና አሥርቱ ቀናቶቹ!!

በአቡ ሀይደር

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው

ክብርና ምስጋና ለዓለማቱ ጌታ ለአላህ የተገባ ይሁን፡፡(አል-ፋቲሓ 2) የአላህ ሰላምና ውዳሴ የሰው ዘር ታላቅ መሪ ለሆኑት ለነቢዩ ሙሐመድ (አል-አሕዛብ 56) ለመላው የአላህ መልክተኞች (አል-ሷፍፋት 181) የሐቅንም መንገድ በተከተለ ሁሉ ላይ ይሁን (ጣሀ 47)፡፡
እንግዲሕ በአላህ ፈቃድ ካላንደር እንደሚያሳየው ነገ የፊታችን ጁምዓ የዙል-ሒጃ ወር ይጀምራል፡፡ ዛሬ ዙል–ቂዕዳህ 29 ነው። ዙል-ሒጃ በእስልምና ወር አቆጣጠር አስራ ሁለተኛው (የመጨረሻው) ወር ነው፡፡ በዚህ ወር ውስጥ ካሉት 29/30 ቀናት ውስጥ የመጀመሪያዎቹ አሥር ቀናት እጅግ የተከበሩ ቀናቶች ናቸው፡፡ መከበራቸውን ከሚያመላክቱት ውስጥ:–

ሀ. አላህ የማለባቸው መሆኑ:–

" በጎህ እምላለሁ።በዐሥር ሌሊቶችም።" (ሱረቱል ፈጅር 1-2)።
ታላቅ የሆነው ጌታችን አላህ የሚምለውም ታላቅ በሆነ ነገር ስለሆነ የቀኑን ክብደት ይገልጽልናል፡፡ እነዚህ አሥር ሌሊቶች የተባሉት የዙል-ሒጃ የመጀመሪያዎቹ አሥር ቀናት እንደሆኑ አብዝሓኞቹ የቅዱስ ቁርኣን ተንታኞች ይገልጻሉ፡፡

ለ. እኔን አስታውሱባቸው ማለቱ:–

" ለነሱ የሆኑ ጥቅሞችን ይጣዱ ዘንድ፣ በታወቁ ቀኖችም ውስጥ ከማለዳ እንሰሳዎች በሰጣቸው ሲሳይ ላይ የአላህን ስም ያወሱ ዘንድ፣ (ይመጡሃል)፤ ከርሷም ብሉ፤ ችግረኛ ድኻንም አብሉ።" (ሱረቱል-ሐጅ 28)።

" የታወቁ ቀኖች " የተባሉት እነዚሁ አሥርቱ ቀናት እንደሆኑ ሙፈሲሮች ያስረዳሉ፡፡ ታዲያ አላህን በማንኛውም ጊዜ ማውሳትና ማወደስ ከመቻሉ ጋር በነዚህ ቀኖች አወድሱት ብሎ ቀኖቹን ለይቶ መጥቀሱ የተለየ ደረጃና ክብር እንዳላቸው ይጠቁማል፡፡

ሐ. ከዱንያ ቀናት ሁሉ በላጭ መሆናቸው:–

ከጃቢር ኢብኒ ዐብዲላህ (ረዲየላሁ ዐንሁ) በተላለፈው ሐዲሥ ረሱላችን (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል፡-" ከዱንያ ቀናቶች ሁሉ በላጩ (የዙል-ሒጃ) አሥሩ ቀናት ናቸው " (ሶሒሕ አል-ጃሚዑ ሰጊር 1133)፡፡
በዚህ መሰረት እነዚህ አስርት ቀናቶች ልዩ ክብር የሚሰጣቸው ናቸው፡፡

ምን እንስራባቸው?

ዐብደላህ ኢብኑ አባስ (ረዲየላሁ ዐንሁማ) እንዳስተላለፉት የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል፡- "መልካም ሥራ ከዙል-ሒጃ አሥርቱ ቀናት በልጦ አላህ ዘንድ እጅግ ተወዳጅ የሆነበት ቀናት የለም፡፡" ሶሓባዎችም፡- በአላህ መንገድ ጂሐድ ማድረግም (ጠላትን መታገልም) ቢሆን? ሲሉ፡ እሳቸውም፡- አዎ ጂሐድም ቢሆን! ሰውየው ከነፍሱና ከንብረቱ ጋር በዛው ሳይመለስ የቀረ ካልሆነ በስተቀር አይበልጥም " (ቡኻሪይ)።

ታዲያ ያለምንም የመግቢያ ክፍያ እንዲህ ዐይነት ታላቅ ኤግዚቢሽን ከተዘጋጀልን እኛስ ለመሳተፍ ምን ያህል ወስነናል?፡፡ ጠላታችን ሸይጣን እንዳንጠቀምበት ደፋ ቀና ማለቱ አይቀርምና እኛም አላህን ይዘን እሱን ድል በመምታት ቀኑን እንጠቀምበት፡፡ ከሚሰሩ መልካም ስራዎች ውስጥ፡-

1. ሐጅና ዑምራህ:–

" ዑምራህ ቀጣዩ አመት ዑምራ እስኪመጣ ድረስ (በመሃል ለተፈጸሙ ጥቃቅን ኃጢአት) ማስተሰረያ ነው፣ ትክክለኛ ሐጅ ደግሞ ከጀነት ውጪ ክፍያ የለውም" (ቡኻሪና ሙስሊም)።

2. ጾም:–

የፈለገ ሙሉውን ዘጠኝ ቀን: ካልሆነም የቻለውን ያክል መጾም ይችላል፡፡ዐብደላ ኢብኑ አባስ (ረዲየላሁ ዐንሁማ) እንዳስተላለፉት የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል፡- "መልካም ስራ ከዙል-ሒጃ አስርቱ ቀናት በልጦ አላህ ዘንድ እጅግ ተወዳጅ የሆነበት ቀናት የለም፡፡" በዚህ ሐዲሥ መሠረት ጾም "መልካም ሥራ" የተባለው ሐዲሥ ውስጥ ስለሚካተት በጾሙ የቻለውን ያክል መበርታት ይችላል፡፡

3. አላህን ማውሳት:–

" ለነሱ የሆኑ ጥቅሞችን ይጣዱ ዘንድ፣ በታወቁ ቀኖችም ውስጥ ከማለዳ እንሰሳዎች በሰጣቸው ሲሳይ ላይ የአላህን ስም ያወሱ ዘንድ፣ (ይመጡሃል)፤ ከርሷም ብሉ፤ ችግረኛ ድኻንም አብሉ።" (ሱረቱል-ሐጅ 28)።

ይህ ቅዱስ አንቀጽ አላህን በነዚህ ቀናት ማውሳት: መዘከር እንዳለብን ይነግረናል፡፡ ዐብደላህ ኢብኑ ዑመር (ረዲየላሁ ዐንሁማ) ባስተላለፉት ሐዲሥ ላይ ነቢዩ (ዐለይሂ-ሶላቱ ወስ-ሰላም) እንዲህ ብለዋል፡- "በነዚህ ቀናት ውስጥ ተህሊል (ላ ኢላሀ ኢልለሏህ)፤ተክቢር (አላሁ አክበር)፤ተሕሚድ (አል-ሐምዱ ሊላህ) ማለትን አብዙ" (አህመድ 7/224)

ዐብዱላህ ኢብኑ ኡመር እና አቢ ሁረይራህ (ረዲየላሁ ዐንሁም) ወደ ገበያ በመውጣት በተክቢራ ሲያሞቁት ሰዎቹም እነሱን ተከትለው ተክቢራ ይሉ ነበር (ኢርዋዑል-ገሊል: አልባኒይ 651)።

4. ተውበት ማብዛት:–

"…ምእምናኖች ሆይ! ትድኑ ዘንድ ሁላችሁም ወደ አላህ (በመመለስ) ተጸጸቱ።" (ሱረቱል አሕዛብ 31)።

5. መልካም ሥራዎችን ማብዛት:–

በኢስላም የመልካም ሥራ በሮች ብዙ ናቸው፡፡ ተቆጥረው አይዘለቁም፡፡ ከኛ የሚጠበቀው ስራው ላይ ተሳታፊ መሆን ነው፡፡ ከቤተሰብ ጀምረን እሰከ ሩቅ ሰው ድረስ አቅማችን የቻለውን ያህል በመርዳት ወደ አላህ እንቃረብ፡፡

6. በዒባዳህ መጠናከር:–

ከፈርድ ሶላት ቀጥሎ ያሉትን ሱንና ሶላቶችን ማብዛት፤ቁርኣንን ማንበብና ማዳመጥ፡፡

7. ከሐራም መቆጠብ:–

ከላይ የተጠቀሱት መልካም ሥራዎች ላይ በመሳተፍ የአላህን ተውፊቅ ያላገኘ ሰው ቢያንስ ከሱ እጅና ምላስ ሌሎች ሰላም እንዲሆኑ እራሱን ማቀብ፡፡እሱም ትልቅ ተውፊቅ ነውና፡፡
አላህ ተጠቃሚ ያርገን

#የኡድሑይያህ እርድ

1/ ኡድሑይያህ ማለት:– በዙል ሒጃህ ወር ከአሥረኛው ቀን አንስቶ እስከ አያመ–ተሽሪቅ (አስራ ሶስተኛው ቀን ድረስ) ወደ አላህ ለመቃረብ ሲባል ከቤት እንሰሳት (ግመል፣ ከብት፣ ፍየል/በግ) አንዳቸውን በመምረጥ የማረድ ስርአት ማለት ነው።

2/ የኡድሑይያህ ስርአት በጣም ጠንካራ ሱንና ከሆኑ የአምልኮ ዘርፎች ይመደባል። የአላህ ቃልም:– "ለጌታህም ስገድ፣ በስሙም እረድ" (አል–ከውሠር 3)። ባለው መሠረት በአላህ ሥም ይታረዳል።

3/ የኡድሑይያህ የእርድ ስርአት ሱንና ነው። ዋጂብ አይደለም። የተወው ሰው በኃጢአት አይከሰስም። ሲታረድም ለአላህ ተብሎና በአላህ ሥም ነው የሚታረደው።

4/ የኡድሑይያህ የእርድ ቀናት ከዒዱ ቀን ሶላት መጠናቀቅ ጀምሮ (የውሙ–ነሕር 10ኛው ቀን ማለት ነው) እስከ አያሙ–ተሽሪቅ የመጨረሻው ቀን (11፣ 12 እና 13ኛው ቀን ፀሀይ መግባት ድረስ) የሚቆይ ይሆናል። በጥቅሉ አራት ቀናት ይኾናል ማለት ነው። 10ኛው ሶላቱል ዒድ የሚሰገድበት ቀን (የውሙ–ነሕር)፣ 11ኛው ቀን፣ 12ኛው ቀን፣ 13ኛው ቀን።

5/ በዋጋ ጠንከር ያለ፣ ስጋው በዛና ሞላ ያለ፣ ከነውር የፀዳ፣ የእርድ አይነት መግዛቱ በላጭ ይኾናል። ኡድሑይያህ የነየተውም አካል: ከእርዱ ላይ እራሱም ሊበላ፣ ቤተሰቡንም ሊያበላ፣ ዘመድና ወዳጆቹንም ሊጋብዝ፣ ለምስኪኖችም ሊያከፋፍል ይወደድለታል።

6/ የሚታረደው የእርድ አይነት ግመል ከሆነ አምስት አመት የሞላው፣ ከብት (በሬ/ላም) ከሆነ ሁለት አመት የሞላው፣ ፍየል ከሆነ አመት የሞላው፣ በግ ከኾነ ስድስት ወር ያለፈው ከኾነ ለእርድ የበቃ ይኾናል።

7/ የእርዱ አይነት እውር ወይም አንካሳ ወይም በሽተኛ ከሆነ አይበቃም። ጆሮው ወይም ጭራው የተቆረጠ፣ ጥርሶቹ በመላ የረገፉ ከኾነ ደግሞ እሱን ለእርድ ማቅረብ የተጠላ ይኾናል።
8/ የዒዱል አድሓን እርድ ለመፈጸም የነየተ የአላህ ባሪያ (ወንድም ሆነ ሴት) ወሩ ከገባበት ጊዜ ጀምሮ፡- የሰውነት ጸጉሩን መላጨትም ሆነ መቀነስ፣ የእጁንም ሆነ የእግሩን ጥፍር ማስተካከል፣ ከገላው ላይ የተወሰነ ቆዳንም ቢሆን ቆርጦ ማንሳት አይፈቀድለትም፡፡ ይህ ብይን የሚመለከተው የዒዱን እርድ በራሱ ወጪ ለማረድ የነየተውን ግለሰብ ብቻ ነው፡፡ ቤተሰቦቹን ብይኑ አይመለከታቸውም፡፡

ሰውየው በቀጥታ እራሱም አራጅ ሆነ፡ ወይም በወኪል ቢያሳርድ ኃላፊው እሱ እስከሆነ ድረስ ብይኑ ይመለከተዋል፡፡ ወኪል ሆኖ የሚያርደውን ሰው ግን ብይኑ አይመለከተውም፡፡

ኡሙ ሰለማህ (ረዲየላሁ ዐንሃ) እንደነገረችን የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ፡- "የዙል-ሒጃህን ጨረቃ ካያችሁና አንዳችሁም ኡድሑያን (እርድን) ከነየተ፡ ጸጉሩንና ጥፍሩን (ከመቀነስ) ይቆጠብ" (ሙስሊም 1977)፡፡

በሌላ ዘገባ ላይ ደግሞ ‹‹ከጸጉሩና ከሰውነቱ (ቆዳው) ይቆጠብ›› ይላል፡፡
ስለዚህ ዛሬ ዕለተ ቅዳሜ የዚል-ቂዕዳህ 29ኛው ቀን ስለሆነ፡ ወሩ በዚያው ሊጠናቀቅም ስለሚችል፡ የመግሪብ አዛን ከተሰማ በኋላ ያለው ምሽት የዙል-ሒጃህ 1ኛ ቀን ሆኖ ይጀምራል ማለት ነው፡፡ ወሩ ሠላሳ ከሞላ ደግሞ፡ ከእሁድ መግሪብ በኋላ ወሩ የዙል-ሒጃህ 1ኛ ቀን ይሆናል ማለት ነው፡፡ እናም ለዒዱ እርድን የነየታችሁ ወንድምና እህቶች ሆይ! ከዛሬ መግሪብ አዛን በፊት (የጸጉር፣ የጥፍርና የቆዳ) ጣጣችሁን ጨርሱ፡፡

ሌላው ሊታወቅ የሚገባው ነገር፡ እርዱን የነየተ ሰው፡ በዙል-ሒጃህ የመጀመሪያዎቹ ዘጠኝ ቀናት ውስጥ ጸጉሩን ወይም ጥፍሩን ቢቀንስ፡ ከፋራው ‹ካሳው› ተውበትና ኢስቲግፋር ብቻ ነው በማለት ዑለሞች ፈትዋ ሰጥተዋል (ኢብኑ ቁዳማህ፡ አል-ሙግኒይ 9/346)፡፡
አላህ ተጠቃሚ ያድርገን።

Click and Like ➤➤ https://www.facebook.com/Ustaz.Abuhyder
Join us ➤➤ http://www.tg-me.com/abuhyder
እንኳን ለተወደደውና ለተከበረው ለ1,443ኛው ዓመተ ሂጅራ የኢዱል-አድሓ በዓል አላህ በሰላምና በጤና አደረሳችሁ!
ተቀበለላሁ ሚንና ወሚንኩም ሷሊሐል አዕማል
ዒዱኩም ሙባረክ
السلام عليكم ورحمة الله
ياريت كل من يصله هذا الخير ينشره قدر إستطاعته لعله يكون الصدقة الجارية بعد رحيلنا اللهم بارك لمن قام بهذا المجهود ما شاء الله ولا حول ولا قوة إلا بالله التفسير الصوتي ، ليس عندك وقت للقراءة ، جاءك الحل ، اضغط على الرابط واستمع ، وتلذذ بفهم معاني كتاب الله العزيز ، في بيتك في سيارتك ، أثناء فراغك وانتظارك أو سفرك ، اختر الكتاب الذي تريده من ضمن باقة منوعة من كتب التفسير ، واحتسب أجر طلب العلم ، وتعلم تفسير القرآن الكريم .
https://read.tafsir.one/

*انشره قدر إستطاعتك*
አሰላሙ ዐለይኩም ወራሕመቱላሂ ወበረካቱሁ

ይህነረን የዩቱብ ሊንክ በመክፈት ሰብስክራይብ አድርጋችሁ ቤተሰብ ሁኑ። በአላህ ፈቃድ ትጠቀሙበታላችሁ። ለሰውም ሼር አድርጉ

https://youtube.com/channel/UC1phBbwcq_sXeSKKV_JtUMg
አስቸኳይ የድጋፍ ጥሪ

በሰጋጆች ድርቅ የተመታውን የዱራሜውን ቢላል መስጂድ ሁላችንም ለመታደግ እንረባረብ

አቡ ዳውድ ኡስማን

መዕክቱን አንብበው ሲጨርሱ ለሌሎችም ሼር ያድርጉት

በደቡብ ክልል በከምባታ ጠምባሮ ዞን በዱራሜ ከተማ በካሻ ቀበሌ አሮጌ ሰፈር የሚገኘው ቢላል መስጂድ አካባቢው የነበሩ ሙስሊሞች እንዲሁም የመስጂዱ ኢማም ሚስታቸው እና ልጃቸው ሳይቀር ከፍረው የመስጁዱ ሙዓዚን እና ኢማም የሆኑት ሼይኽ መሐመድ ኑር ብቻቸውን በመስጂዱ እየሰገዱ እንደሚገኙ መገለፁ ይታወሳል::

በዚህ ትልቅ መስጂድ ውስጥ ብቻቸውን አዛን እያወጡ ብቻቸውን ኢቃም ብለው እንደሚሰግዱ መገለፁን ተከትሎ ከፍተኛ ቁጭት እና ሀዘን በሁላችንም ላይ ተፈጥሯል::

መስጁዱ በእድሳት እጥረት በመጎዳቱ ዝናብም እያፈሰሰ እንደሚገኝ እንዲሁም ሌሎች እድሳቶችም እንደሚያስፈልገው ተገልፆ ነበር::

የአካባቢውን ሙስሊሙ ማህበረሰብ ወደ ዲናቸው እንዲመለሱ፣ ባዶ የሆነው መስጂድም በጀምዓ እንዲሞላ፣ የከፈሩትንም ለመመለስ ህዝበ ሙስሊሙ በአንድነት ትብብር እንዲያደርግ ጥሪ ቀርቦ ነበር::

ይህን አሳሳቢ ጉዳይ ቀድሞ መረጃው የደረሳቸው በደቡብ ክልል የአክፍሮት ሃይላትን የኩፍር ዘመቻ ለመመከት መሬት ላይ የወረዱ በርካታ ፕሬጀክቶችን፣ መስጂዶችን እና መድረሳዎችን እያሰሩ የሚገኙት ተወዳጁ ኡስታዛችን ኡስታዝ ሷዲቅ መሐመድ(አቡ ሐይደር) ይህንንም የዱራሜ መስጂድ ጉዳይ መፍትሄ እንዲያገኝ እየለፉ ይገኛሉ::

በዚህም መሰረት ይህን መስጂድ ለመታደግ እና የአክፍሮት ሃይላትን እንቅስቃሴ በመመከት የአካባቢውን ህዝበ ሙስሊም ወደ ዲኑ ለመመለስ ይቻል ዘንድ ሁሉም ህዝበ ሙስሊም ያቅሙን ያህል ድጋፍ የሚያደርግበት ሁኔታ ተመቻችቷል::

በኡስታዝ ሷዲቅ መሐመድ (አቡ ሃይደር ) አስተባባሪነት
በዱራሜ ከተማ በካሻ ቀበሌ አሮጌ ሰፈር የሚገኘው በዚሁ የቢላል መስጂድን ማዕከል የሚያደርግ እንቅስቃሴ ተጀምሯል::

በቀዳሚነት ለመስጂዱ ቋሚ ኡስታዝ መቅጠር እንዲሁም መስጂዱ በሚገኝበት በዱራሜ ከተማ በዱራሜ ዩኒቨርሲቲ ለሚገኙ የዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች በዚህ መስጁድ ላይ ታላቅ የዳዕዋ ኮንፍረንስ ለማካሄድ ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል::

ይህ ኮንፍረንስ ከነሐሴ 13-15/2014 ለሶስት ቀናት ኢማሙ ብቻቸውን ሲሰግዱበት በነበረው ቢላል መስጂድ የሚሰጥ ይሆናል::

ይህ ታላቅ ኮንፍረስ ሙስሊም የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ማዕከል በማድረግ በአካባቢው ያለውን የኩፍር ዘመቻ ለመመከት እና ሰዎች ወደ ዲናቸው እንዲመለሱ እንዲሁም የመስጁዱን ጀምዓ በማጠናከር ሰፊ ስራዎችን ለመስራት የሚያግዝ ነው::

አሁን ላይ የሁላችንንም ርብርብ እና ድጋፍ የሚሹ ወጪዎች ያሉ ሲሆን እነዚህም:-

1/ ቋሚ የኢማም ደሞዝ ክፍያ
2/ የመሰጂዱ አጥርን ማሳጠር
3/ መስጁዱ የጎደለውን ነገር ሁሉ ማሟላት እና
4/ ለታሰበው ታላቅ የዳዕዋ ኮንፍራንስ ወጪውን መሸፈን ይገኝበታል:

በአሁኑ ሰዓት ብቸኛ የነበሩትን ሼይኽ መሐመድኑርን የሚያግዝ በመስጁዱ በቋሚነት ሊያገልግል የሚችል ብቁ ኡስታዝ የተገኘ ሲሆን በዋናነት ኡስታዙም የመስጁዱ ኢማም በቋሚነት በመሆን እንዲያገለግል፣ ከዐሱር በኋላ ልጆችን እንዲያቀራ እንዲሁም ለካምፓሱ ተማሪዎች ኪታብ እንዲያቀራ ታስቧል::

እነዚህን አስቸኳይ ስራዎች በመስጂዱ ለመስራት በሀገር ውስጥም ሆነ ከሃገር ውጪ ያላችሁ የበኩላችሁም ድጋፍ ታደርጉ ዘንድ በአላህ ስም እንጠይቃለን::

በተከሰተው ነገር ከንፈር መምጠት እና ማዘን ብቻ ሳይሆን የመፍትሄ ሃሳብ ሲቀርብም ሁላችንም በቻልነው ያህል ማገዝ ይጠበቅብናል:: መፍትሄው በአንድነት መሬት ላይ ሊወርድ የሚችል ስራ መስራት ስንችል ብቻ ነው::

ለተዘረዘሩት ወጪዎች ድጋፍ ማድረግ ለምትፈልጉ ሁሉ በኡስታዝ ሷዲቅ መሐመድ ስም በተከፈተው አካውንት ድጋፍ ማድረግ ትችላላችሁ

1. COMMERCIAL BANK OF ETHIOPIA
1000317507589
SADIK MOHAMMED AHMED

2. ABYSSINIA BANK
83047178
SADIK MOHAMMED AHMED

3. ኦሮሚያ ህብረት ሥራ ባንክ
1011300008645
SADIK MOHAMMED AHMED

ለበለጠ መረጃ በዚህ ስልክ መደወል ትችላላችሁ
0911103231

ይህን መልዕክት ሁላችንም ሼር በማድረግ እናዳርስ!
የዱራሜው መስጂድ ቢላል ጉዳይ ከምን ደረሰ?

በአቡ ሀይደር

በአላህ ሥም እጅግ በጣም ሩህሩኅ በጣም አዛኝ በሆነው

ከሁሉ በፊት አማኝ ባሪያዎቹን በማነሳሳትና በማገዝ: ከፊሉ በገንዘቡ፣ ከፊሉ በዕውቀቱ፣ ከፊሉ በማስተዋወቅና የተቀረው ደግሞ በቦታው ላይ በመሳተፍ ለመስጂዱ ህልውና አስተዋጽኦ እንዲያደርግ: ተውፊቁ (እገዛው) ላልተለየን ጌታ አላህ ምስጋና ይድረሰው። ያለሱ እገዛና ፈቃድ ምንም ነገር ሊከሰት አይችልምና።

በመቀጠልም: የዱራሜው ቢላል መስጂድ ሁኔታ፤ ሙአዚንና ኢማም በሆኑት ሰውዬ ብቻ ሶላት መከናወኑ: እረፍት የነሳው ወንድማችን የ Islam Selam አካውንት እና የዚህ ዩቱብ https://youtube.com/channel/UC1phBbwcq_sXeSKKV_JtUMg ባለቤት ጉዳዩን በፌቡ በመልቀቅ ለሙስሊሞች መነሳሳት ሰበብ ስለሆንከን ጀዛከላሁ ኸይራ።

በመሰለስም: ይህ ጉዳይ ለሁሉም ወንድምና እሕቶች በሰፊው እንዲዳረስና ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይል በተደጋጋሚ በመፖሰት ሰፊ ተደራሽነት እንዲኖረው ለለፋኸው ወንድም አቡ ዳዉድ ዑሥማን ጀዛከላሁ ኸይራ።

በመረበዕም:– በተለያዩ የሶሻል ሚዲያዊች (በፌቡ፣ በቴሌግራም፣ በዋትስአፕ፣ በቲክቶክና በዩቱብ) ስርጭቱ እንዲስፋፋ ላደረጋችሁ ወንድምና እሕቶች በመላ ጀዛኩሙላሁ ኸይራ።

በመጨረሻም:– በሀገር ውስጥም ከሀገር ውጭም በመሆን ይህ የዱራሜው ቢላል መስጂድ ጉዳይ የኔ ጉዳይ ነው በማለት በገንዘባቹ የተሳተፋችሁ ወንድምና እሕቶች: ገንዘብና ልጆች በማይጠቅሙበት ቀን አላህ ባወጣችሁት ገንዘብ ተጠቃሚ ያድርጋችሁ።

እንዲሁም ቦታው ድረስ በመገኘት ለተሰበሰበው ሕዝብ ኢስላማዊ ትምሕርት የሰጣችሁ (ኡስታዝ ዐብዲ፣ ኡስታዝ ጁንዱላህ፣ ኡስታዝ መሐመድ ሸምሱ)፣ በቦታው በመገኘት የፕሮግራሙ ድምቀት የሆናችሁ ተሳታፊዎች በሙሉ (በተለይ የሐላባ ጀመዓዎች)፣ ቦታውን በማበጃጀት ላስተካከላችሁ በመላ (በተለይ ወንድም ሱልጣን ናሲር፣ ወንድም መሐመድ ኢብራሂም እና ወንድም ፉአድ) ጀዛኩሙላሁ ኸይራ።

አዲስ ነገር ምን ተሰራ ምንስ ቀረ?

1/ በመስጂዱ ላይ ሙአዚን እና ኢማም ከነበሩት አባት በተጨማሪ: ለመስጂዱ ቋሚ ኢማም (በመግሪብ፣ ዒሻእና ፈጅር ላይ አሰጋጅ) ተመድቧል። ይህ ኢማም ከኢማምነት በተጨማሪ:– የአካባቢውን ህፃናት ቁርኣን ማስቀራት፣ ከመግሪብ እስከ ዒሻእ ለመጣው ሰው ቋሚ የሙሐደራ ፕሮግራም መስጠት፣ በግላቸው የተለያየ ኪታብ መቅራት የሚፈልጉ ወንድሞችን ማቅራት ሥራው ይሆናል።

2/ ቅዳሜና እሕዱ (ከ 14/12/14—15/12/14) ለሁለት ቀናት በመስጂዱ ላይ ለተሰበሰበው ህዝብ ኢስላማዊ ት/ት መስጠት። በዳዕዋው ሰበብም ወደ 9 ሰዎች ሸሀዳ በመስጠት ሰልመዋል። ለተሰበሰበው ሰውም በሁለቱ ቀናት የምሳ ግብዣ ፕሮግራም ተካሂዷል።

3/ የመስጂዱ ውስጣዊ ችግር (ኮርኒስ) እደሳ ተካሂዷል።

በአሁን ሰአት ከአዲሱ ኢማም በደረሰኝ መረጃ መሰረት ከ10 እስከ 15 የሚደርሱ ሰዎች ወደ መስጂዱ በመመላለስ የጀመዓ ሶላት እንደሚሰግዱ ማወቅ ተችሏል። ቁርኣን መማር የጀመሩ ህፃናትም (ወንድና ሴትን ጨምሮ) ወደ 15 ደርሰዋል።
የቀረው ሥራ ደግሞ:– መስጂዱን ዙሪያውን ማጠር: በሶስት ወይም በየ አራት ወራት በመስጂዱ ላይ የዳዕዋ ፕሮግራሞችን ማዘጋጀት።

ምን ያህል ገንዘብ ተሰበሰበ? ምን ያህልስ ወጪ ተደረገ?

የተሰበሰበው ገንዘብ ከገመትነውና ከጠበቅነው በላይ ነው። በአጠቃላይ እስካሁኑ ሰአት ድረስ የተሰበሰበው ገንዘብ 2,585,113·32 ሳ (ሁለት ሚሊየን አምስት መቶ ሰማንያ አምስት ሺህ፣ አንድ መቶ አሥራ ሶስት ብር ከሰላሳ ሁለት ሳንቲም) ነው።

ወጪ የተደረገው ደግሞ:– 242,997 ብር ነው። ከወጪ ቀሪ የሚሆነው:– 2,342,116·32 ሳ ይሆናል።

በቀጣይ ምን ታሰበ?

ይህ የተሰበሰበው ገንዘብ ለቢላል መስጂድ ሙአዚን እና ኢማም እንዲሁም ኡስታዝ ለሆኑት በተጨማሪም ለአጥር ግንባታው ከሚያስፈልገው በላይ የተረፈ በመሆኑ: ይህ የተረፈ ገንዘብ ለሌላ ኸይር ሥራ እንዲውል:–

1/ በዋንኝት በአካባቢው የሚገኘውን የካምፓሱ ሙስሊም ተማሪዎችን ማገዝ። የዱራሜ ካምፓስ ሙስሊም ተማሪዎች ከካምፓሱ ፊትለፊት ወደ ውስጥ ገባ ብሎ የሰሩትን መስጂድ ጎብኝቼዋለሁ። መስጂዱ ቀሪ ሥራዎች (በተለይ በሴቶች በኩል ምንጣፍ፣ በርና መስኮት እንዲሁም ችፑድና መፀዳጃ ቤት)፣ መድረሳው ሙሉ እድሳት ያስፈልጉታል። እንደተነገረኝ ከሆነ ወደዚህ መስጂድ በመመላለስ የሚሰግዱ ወንድምና እሕቶች ወደ 300 ይጠጋሉ። ስለዚህ እነዚህ ሰጋጆች: ከሶላት በተጨማሪ መንፈሳዊ ማንነታቸውን የሚያጠናክርላቸው ሁለት ኡስታዞችን መቅጠር ያስፈልጋል።

2/ በዛው ዱራሜ ከተማ: ከቢላል መስጂድ ራቅ ብሎ በገጠራማው ክፍል ለሚገኙ ሙስሊም ነዋሪዎች የኡስታዝ እጥረት ያለባቸውን ቦታዎች ጥናት በማድረግ ኡስታዞችን መቅጠር ዋነኛ ስራችን ይሆናል።

3/ ገንዘቡ የሚተርፍ ከሆነ ከሀላባ ከተማ ወደ ከንባታ በሚወስደው መንገድ 12 ኪ ሜ ርቃ የምትገኘውን የአቦኪቾ ከተማ በኡስታዞችና በዳዕዋ መድረስ ሌላው ስራችን ይሆናል። ይህ ከተማ ከ1000–1,500 የሚደርሱ አባወራዎች አሉት። 85 በመቶ የሚሆነው ሙስሊም ነው። ያሉት መስጂዶች ብዛት በጭቃ የተሰሩ 3 ብቻ ናቸው። መደረሳ ማፊ፣ ኡስታዝ ማፊ!! ስለዚህ ቦታው የኡስታዝና የመድረሳ ትኩረት ይሻል።

ወንድምና እሕቶቼ ሆይ!

ይህ የኸይር ሥራ ቀጣይነት እንዲኖረው የናንተን እገዛ ይሻልና: በቻላችሁት መጠን አሁንም ከመተባበር ወደ ኋላ አትበሉ። አላህ ያግዛችሁ ወሰላሙ ዐለይኩም ወራሕመቱላሂ ወበረካቱሁ
እህታችን በብድር ተይዛ ተጨንቃለች፣ከእዳ ብድር ጭንቀት አላህ ይጠብቃችሁ ፣የቻልነውን ያህል እንተባበራት እህታችን እንዲህ ትላለች

አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱሁ
የአላህ እዝነትና ቸርነት በናንተ በወገኖቼ ላይ ይሁን እኔ እህታቹ ወ/ሮ ሀናን ጀማል በጓደኞቼ እና ባመንኩዋቸው የስራ ባልደረቦቼ የደረሰብኝን መከዳትና መጭበርበር ስገልፅላችሁ አላህ ከእንደዚህ አይነት ነገር እንዲጠብቃችሁ በመመኘት ጭምር ነዉ
ወገኖቼ ያዋጣኛል ነገ ህይወቴን ይቀይርልኛል ብዬ አስቤ ከብዙ ሰዎች ላይ ተበድሬ የሰጠዃቸዉን 3,200,000 (ሶስት ሚሊየን ሁለት መቶ ሺህ) ብር ይዘዉብኝ ተሰዉረዋል አበዳሪዎቼ ደግሞ ወደ ክስ ሄደዉ ከ አንዴም ሁለቴ ታስሬ አሁን ላይ በዋስ ወጥቼ በፍጥነት አምጥቼ እንድከፍል አ ስጠንቅቀዉኛል አሁን ላይ ደሞ የ 7 ወር ነብሰ ጡር ነኝ በዛ ላይ ደግሞ ታምሚያለሁ በዚህ ሰአት ደሞ ይሄንን ገንዘብ የመክፈል አቅም የለኝም ይሄን ገንዘብ ካልከፈልኩ ደሞ በድጋሚ ለእስር እንደምዳረግ አስጠንቅቀውኛል:: ውድ ወገኖቼ እንደኔ ካልታሰበ ኪሳራ እና ችግር አላህ ይጠብቃችሁ እያልኩ እዳዬን እንድከፍል የበኩላችሁን ታደርጉልኝ ዘንድበ አላህ ስም እጠይቃችሁአለዉ
የባንክ አካዉንት Nigd bank 1000491549916 ሀናን ጀማል ሽፋ
abysinya 88569048 ሀናን ጀማል ሽፋ
Awash 01425589998100 ሀናን ጀማል ሽፋ
◉ ይህ▸ https://youtu.be/5YYX3k9Orho የኡስታዝ ኢልያህ ማሕሙድ ይፋዊ የዩቲዩብ ቻናል ነው። የተለያዩ ኢስላማዊ እና ንፅፅራዊ ትምህርቶች የሚለቀቁበት ብቸኛው ገጹ ስለሆነ Subscribe/Like/Share በማድረግ ዳዕዋውን ለወገኖቻችን በፍጥነት ያድርሱ።

® Ustaz Eliyah Mahmoud Telegram Channel.
የምስራች
...
ማዕከላችን ሒዳያ ኢስላማዊ ማዕከል በአሏህ ﷻ እገዛ ከዚያም በታች በብርቱ ወንድሞችና እህቶች ጥረት ህጋዊ ሒደቱን አጠናቆ በይፋ ስራዎችን ጀምሯል። በሀገራችን እየተንሰራፋ የሚገኘውን የአክፍሮተ ሀይላት እንቅስቃሴ በዳዕዋ ለመመከትና እስልምና ያልደረሰባቸው አካባቢዎች ሪሳላውን ለማስፋት ትኩረት አድርጎ የሚሰራው ማዕከላችን ስራውን በተጠናከረ መልኩ ለመስራት ጉዞውን በአሏህ ﷻ ፍቃድ ጀምሯል።
...
በተጨማሪም የበጎ አድራጎት ስራዎች የሚያስፈልግባቸው አካባቢዎች ላይ ስራዎችን ለመስራት ራሱን የቻለ ህጋዊ የበጎ አድራጎት ፍቃድ ያለው ሲሆን በተለያዩ ቦታዎች በወገኖቻችን ላይ ለሚደርሱ እምነት ፈታኝ መከራዎች በተቻለው መጠን ለመስራት እንቅስቃሴውን ጀምሯል። የማዕከላችን አባል በመሆን በጉልበት እንዲሁም በገንዘብ የአቅማችሁን መደገፍ ለምትፈልጉ ከዚህ በታች ባለው የጎግል ፎርም አባል እንድትሆኑ እየጠየቅን በቀጥታ ለመደገፍ ከዚህ በታች ያለውን የማዕከሉ ኦፊሺያል አካውንት መጠቀም ትችላላችሁ።

አካውንት - 1000499318212
የአካውንት ስም - Hidaya Islamic Center
በአጭር ቁጥር - 8212 መጠቀም ይችላሉ።
____
በተሰማሩበት መስክ የሒዳያ ኢስላማዊ ማዕከል አባል በመኾን ዳዕዋውን ማገዝ ከፈለጉ በሚከተለው ማስፈንጠሪያ የአባልነት ቅፅ በመሙላት ሊቀላቀሉን ይችላሉ፦

https://bit.ly/3r7DhoY
📌 የትብብር ጥያቄ

📌 270,000 ብር ብቻ

''እኛ መስማት የተሳናቸው ሙስሊሞች ዙርያ የምንሰራ ኢማን የኢትዮጵያ መስማት የተሳናቸው ልማት ድርጅት እንባላለን። ከማህበራት ማደራጃ ፍቃድ ያለን ህጋዊ ተቋም ነን።

ህዳር 19 ላይ አለም አቀፍ የመስማት የተሳናቸው ሙስሊሞች ኮንፈረንስ ጋምቢያ ላይ እንድንሳተፍ የጥሪ ደብዳቤ ተልኮልናለን። ስብሰባው ለመላው ኢትዮጵያዊ ሙስሊም መስማት የተሳናው ይጠቅማል ብለንም እናምናለን። ግን አሁን እኛ የደርሶ መልስ የአየር ጉዞ ቲኬት ለመክፈል አቅሙ የለንም። የምንሄደው 3 ሰዎች ነን።

ለያንዳንዳችን ከ80 እስከ 90ሺህ ብር ወይም ለ3ታችን 270ሺህ ብር ገደማ ይጠበቅብናል። የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት የትብብር ደብዳቤ ፅፎልናል። እባካችሁ በኮንፈረንሱ ላይ እንድንሳተፍ ለአላህ ብላቹ ተባበሩን ይላሉ'' መልዕክታቸው።

ሁላችንም ብንተባበራቸው ቀላል ገንዘብ ናት። መስማት የተሳናቸውን፣ አይነ ስውራንን የመሳሰሉ ወገኖቻችንን በእምነታቸው እንዲጠነክሩ ማገዝ የሁላችንም ግዴታ ነው።

ከታች ባሉ አካውንቶች ድጋፍ በማድረግ እናግዛቸው።

📌 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት
📌 1000461347936
📌 IMAN ETHIO DEAF DEVT ORGA (IEDDO)

🔴 ሒጅራ ባንክ
🔴 1002450020001
🔴 IMAN ETHIO DEAF DEVT ORGA (IEDDO)

📌 ዘምዘም ባንክ
📌 0009389910301
📌 IMAN ETHIO DEAF DEVT ORGAN
2024/09/28 11:18:31
Back to Top
HTML Embed Code: