Telegram Web Link
ጳጉሜ 04
"ፍቅር ካለ..."
+ እንጸልይ ጸሎት ይለውጣል +

በቤታችን ፣ በሀገራችንና በምድራችን ልማትና ምርታማነት እንዲሆን የዘራነው ይበቅል ዘንድ ዝናብን በጊዜው የምታወርድ የበቀለውም ይበስል ዘንድ ጸሐይንም በጊዜዋ የምታወጣ የዘመን ሁሉ አፈራራቂ ቸር አምላካችን እግዚአብሔር ሆይ ዛሬም ጠለ ምህረትህን ስለሰጠኸን እናመሰግንሃለን 🙏

ስንፍናን የምትቃወመው ሆይ በረከትን እናገኝ ዘንድ ምድርን ሰጠኸን አርሰን ፣ ጥረን ግረን እንበላ ዘንድ ሰጠኸን መሬት የጣሉለትን ሁሉ በእጥፍ አድርጎ ይሰጣልና ጥሩ ዕድገት አምራችነት የሚረጋገጠውም ዝቅ ብለን ስንሰራ ነው። መጣር ፣ማረስ የእኛ ድርሻ ሲሆን ማብቀል መባረክ ግን ያንተ ነው ያላንተ ያመረተም ብኩን ነው።

ድሮ አባቶቻችን አንተን እያስቀደሙ በፍቅር ተጓዙ የእጃቸውንም ፍሬ ባረክላቸውና ጠግቡ ዛሬ ግን "ፍቅር ካለ......." የሚለው ብሂላችንን ዘንግተን በስግብግብ ማንነት ለየብቻችን ስንጓዝ በልቶ ማደርም ጭንቅ ሆነብን ብዙ ብናከማችም በረከት አልባ ሆንን ጥቂቱን የምታበዛው ሆይ የበረከት ምንጭ አምላካችን ሆይ በጥረታችን ሁሉ ላይ በጸሎት ፣በኑሮ አንተን ማስቀደም ይሆንልን ዘንድ ጥረታችንን ፣ ስራችንን ሁሉ ባርከህልን የራቀንን ፍቅር እንደሸማ አልብሰኸን የምናፈራው ፍሬ ከእኛ አልፎ ብዙዎች የሚረኩበት ይሆን ዘንድ፣ ማስተዋልን ታበዛልን ዘንድ እንማጸንሃለን በሰፊው እጅህ አሜን 🙏

ሊ/ዲ/ን መባጽዮን
ጳጉሜ 04/2015 ዓ/ም
👇👇👇👇👇👇👇
@Yahiwenesei
@Yahiwenesei
@Yahiwenesei
⛪️የኢኦተቤክ አስተምህሮ ና ስርአትን የጠበቁ የትኞቹን መዝሙራት ማግኝት ይፈልጋሉ⁉️

👏 የቸብቸቦ መዝሙራት
          📖▓⇨→vido    ⇨ግጥም
🎻 የበገና መዝሙራት  
         📖▓⇨→vido     ⇨ግጥም
👑 የቅዱሳን መዝሙራት
          📖▓⇨→vido    ⇨ግጥም
⛪️ የንግስ መዝሙራት
          📖▓⇨→vido    ⇨ግጥም
🤲 የምስጋና  መዝሙራት
          📖▓⇨→vido    ⇨ግጥም
🙏 የንስሐ  መዝሙራት
         📖▓⇨→vido   ⇨ግጥም
💍 የሠርግ መዝሙራት
          📖▓⇨→avido   ⇨ግጥም
🌦 ወቅታዊ መዝሙራት
          📖▓⇨→vido    ⇨ግጥም
🇪🇹 ለአገር የተዘመሩ

          📖▓⇨→vido   ⇨ግጥም
          👇👇
https://youtu.be/74f62hDwSA4

          👇🏽ከእስልምና ወደ ክርስትና በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሰረተ በYOUTUBE👇🏽

         👇🏽🔻 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 𝒏𝒐𝒘 🔻👇🏽
   https://www.youtube.com/channel/UCy1JtUNzSqHW-91lAHXN-NA

           👆🏽🔺 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 𝒏𝒐𝒘 🔺‌‌👆🏽
እንኳን ከ 2015 ዓ.ም ዘመነ ሉቃስ ወደ 2016 ዓ.ም ዘመነ ዮሐንስ በሰላምና በጤና አሸጋገራችሁ!

ዓመቱን ሙሉ ኖረው ይህችን ቀን ሳያዩ ትላንት የሞቱ አሉ። የኖርነው ስለ ፈለግን ሳይሆን ስለ ተፈቀደልን ነው፡ ፡ ይህች ቀን ከሰው የምትሰጥ ብትሆን ኖሮ ባላገኘናት ነበር። እነዚያ የሞቱት በሞኝነት ፣ እኛ የቀረነው በብልጠት አይደለም:: መኖር የአንድ አምላክ ስጦታ ነው:: እንኳን ለዚህች ቀን አበቃን! ዓመቱን የሰላም ያድርግልን!
@meba
👇👇👇👇👇👇
@Yahiwenesei
@Yahiwenesei
@Yahiwenesei
" እኛን ለውጠን "

ማይክሮ ሰከንድ ለማይገባን ዘመንን በቸርነትህ የቸርከን አምላካችን ሆይ እናመሰግንሃለን🙏

ዘመን ያንተ ስጦታ እንጂ የማንም ጥረት ውጤት አይደለም ያንተ ስጦታ ደግሞ ሁል ጊዜም መልካም ነው እኛ ግን እኩይ ምግባራችንን ለዘመኑ እያላከክን "ክፉ ዘመን ደግ ዘመን" እያልን ያሳለፍንበትን ጊዜ ይቅር ብለኸን እንደገና ለንስሃ ይህን ዘመን ስለቸርከን ተመስገን🙏

ሰሪያችን ሆይ ባልተለወጠ ማንነት ዛሬም ዘመኑ መልካም እንዲሆን የምንመኝ ምስኪናን ነንና ስህተታችንን አውቀን በሰጠኸን ዘመን መልካሙን ብቻ እንሰራ ዘንድ እኛን ትለውጠን ዘንድ እንለምንሃለን በማያልቀው ምህረትህ አሜን🙏

ሊ/ዲ/ን መባጽዮን (ኢ/ር)
ጳጉሜ 6/2015 ዓ/ም
@Yahiwenesei
@Yahiwenesei
@Yahiwenesei
አዲሱ ዓመት

በጎ ነገሮቻችን ሁሉ የሚከናወኑበት ፣ በደስታ ሳቅ የምንፈነድቅበት ፣ የቤተክርስቲያንም የሀገርም ሀዘን የማይሆንበት ፣ በኑሯችን የምንረካበት ፣ እግዚአብሔርን መፍራትና ትህትናን ገንዘብ የምናደርግበት ፣ ፍቅር እንደሸማ የምንለብስበት ፣ ሰላም በምድራችን የሚሰፍንበት፣ ከሰሜን እስከ ደቡብ ከምስራቅ እስከ ምዕራብ የጦርነትና የሞት ዜና የማንሰማበት፣ ህጻናት ያለሰቀቀን የሚቦርቁበት ፣ ወጣቶች በስራ የሚበረቱበት አዛውንቶች የሚከበሩበት ፣በሀገራችን ባይተዋር የማንሆንበት ፣ የእናቶቻችን ዕንባ የሚገታበት ፣ እንደድሮአችን በመልካም ምግባር ና በአንድነት የምንዋብበት ዓመት ይሁንልን🙏
እንኳን አደረሳችሁ ኢትዮጵያዊያን !
መልካም ርዕሰ አውደ ዓመት🌻!
ሊ/ዲ/ን መባጽዮን (ኢ/ር)
👇👇👇👇👇👇
@Yahiwenesei
@Yahiwenesei
@Yahiwenesei
+የስኬታማና የሚያስቀና ትዳር መርህ +

ይድረስ ለባለትዳሮችና ልትጋቡ ለወሰናችሁ እጮኛሞች.........

ሴቶች መወደድን ፍቅርን ይሻሉና ባል ሆይ ሚስትህን ውደዳት ፣ ፍቅር ስጣት ይኸ ማለት ዕንቁ ከመስጠትህ በፊት ጊዜ ስጣት ፣ በቁልምጫ ስም ጥራት

ወንዶች መከበርን ይሻሉና ሚስት ሆይ ባልሽን አክብሪው በጓደኞቹ በወዳጆቹ ፊት ክብር ስጪው ጌታዬ በይው ያኔ በትዳራችሁ ላይ ስትተዋወቁ የነበረው ፍቅር እንደሞቀ እንዳስቀና ይቀጥላል ....ደሞ እኔ አይደለሁም ይህን ያልኹት ታላቁ የሕይወት መዝገብ ነው ያለው👇👇👇

(ወደ ኤፌሶን ሰዎች ምዕራፍ 5)
----------
22፤ ሚስቶች ሆይ፥ ለጌታ እንደምትገዙ ለባሎቻችሁ ተገዙ፤

23፤ ክርስቶስ ደግሞ የቤተ ክርስቲያን ራስ እንደ ሆነ እርሱም አካሉን የሚያድን እንደ ሆነ ባል የሚስት ራስ ነውና።

24፤ ዳሩ ግን ቤተ ክርስቲያን ለክርስቶስ እንደምትገዛ እንዲሁ ሚስቶች ደግሞ በሁሉ ለባሎቻቸው ይገዙ።

25-26፤ ባሎች ሆይ፥ ክርስቶስ ደግሞ ቤተ ክርስቲያንን እንደ ወደዳት ሚስቶቻችሁን ውደዱ፤ በውኃ መታጠብና ከቃሉ ጋር አንጽቶ እንዲቀድሳት ስለ እርስዋ ራሱን አሳልፎ ሰጠ፤

27፤ እድፈት ወይም የፊት መጨማደድ ወይም እንዲህ ያለ ነገር ሳይሆንባት ቅድስትና ያለ ነውር ትሆን ዘንድ ክብርት የሆነችን ቤተ ክርስቲያን ለራሱ እንዲያቀርብ ፈለገ።

28፤ እንዲሁም ባሎች ደግሞ እንደ ገዛ ሥጋቸው አድርገው የገዛ ሚስቶቻቸውን ሊወዱአቸው ይገባቸዋል። የገዛ ሚስቱን የሚወድ ራሱን ይወዳል፤
አምላከ አብርሃም ወሳራ እንደቃሉ እንድትኖሩና በትዳራችሁ እንድትባረኩ ይርዳችሁ !
ሰናይ ምሽት !
ሊ/ዲ/ን መባጽዮን (ኢ/ር)
13/01/2016 ዓ/ም
@Yahiwenesei
@Yahiwenesei
@Yahiwenesei
+ መስቀል የድል አርማ +
" ከቀስት ፊት ያመልጡ ዘንድ፥ ለሚፈሩህ ምልክትን ሰጠሃቸው።"
(መዝሙረ ዳዊት 60:4)
ክርስቶስ ለዓለሙ ሁሉ ቤዛ ሆኖ ከመሰቀሉ አስቀድሞ መስቀል የወንጀለኞች መቅጫ ፣ መሰቀያ ፣ የሰቃዮች መዘባበቻ ማላገጫ ነበር 1ኛ ጴጥ 2:24 ጠላት ሊዘብትበት መስቀል ላይ ቢሰቅለው አምላካችን ግን መስቀሉን(መከራውን) የሰውና የእግዚአብሔር መታረቂያ ድልድይ አድርጎ ፣የጥልን ግድግዳ ንዶበት ጠላትንም ራስ ራሱን ቀጥቅጦ አሳፍሮበት ለምናምንበት ሁሉ ዕጸ መስቀሉን የድል ፣ የነጻነት አርማ ፣ ምልክት አድርጎ ሰጠን ክብር ለመድኃኔዓለም ይሁን።

ለዚህ ነው በክርስቶስ አዳኝነት የሚያምኑ አብያተክርስቲያናት ሁሉ በቤተክርስቲያናቸው ላይ ከፍ አድርገው የመስቀል ምልክትን ያስቀምጣሉ ምክንያቱም የድል ዓርማ ስለሆነ በተለይም የጸጋው ግምጃ ቤት የሆነችው ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ቤተክርስቲያናችን ደግሞ በቤተመቅደሶቿ ጉልላት ላይ ፣ በንወየቅድሳቶቿ ላይ በማማተብ ፣በልጆቿ አንገት በማሰር ፣ ብሎን ቀን ሰጥታ መስቀሉን በልዩ ክብር ታከብረዋለች ምክንያቱም ሙሽራዋ ፣ ጌታዋ ክርስቶስ ለእርስዋ ሲል ፣ደሙ የተንጠበጠበበት ተሰቅሎ ጠላትን ድል የነሳበት የነጻነት ፣ የድል አርማ ስለሆነ አሁን ልጆቿ ከጠላት ቀስት የሚያመልጡበት ምልክት ስለሆነ።

ይህን መስቀል አይሁድ ስላፈሩበት ቀበሩት እውነት ተቀብሮ አይቀርምና በጊዜው ወጣ .... ወገኖቼ ጥንት በአይሁዶች አድሮ ያን ሲያደርግ የነበረው የተሸነፈው መንፈስ ዛሬም ይህ አርማ ከፍ ብሎ ሲታይ ያንገፈግፈዋልና በሰዎች እያደረ መስቀሉን በመዘቅዘቅ ፣ "ለመስቀል ክብር መስጠት አያስፈልግም" በሚል ተቃውሞ ለመቅበር ሲሞክር እናያለን ግን አይችልም ክርስቶሳዊያኑ የዳኑበት ፣ የመርገም ዘመንን የተሻገሩበት ነውና ከፍ አድርገው ያከብሩታል እናከብረዋለን። ምክንያቱ የክርስቶስ መስቀል(መከራው) ኃይላችን ፣ ክብራችን ፣ ትምክህታችን ፣ ቤዛችን ምልክቱም የድል አርማችን ነውና እናከብረዋለን አይሁድ ቢክዱትም እኛ እናምንበታለን ምክንያቱም ድነንበታልና 1ኛ ቆሮ 1:18!!!
እንኳን አደረሳችሁ ክርስቶሳዊያን !

ሊ/ዲ/ን መባጽዮን (ኢ/ር)
16/01/2016 ዓ/ም
ዲላ ኢትዮጵያ
@Yahiwenesei
@Yahiwenesei
@Yahiwenesei
በኢየሱስ ልደት ወቅት ስጦታ ይዘው የመጡት የሶስቱ ጠቢባን ሰዎች ስም____ነው።
"የመጨረሻ post" ....የዚህ ሳምንት

"ብንሄድ ይሻለናል"

ሰው ወዶ እራሱን በማጥፋት እራሱ ላይ ከባዱን እርምጃ አይወስድም ይህን የመሰለ ከባድ ውሳኔ የሚወስነው ምናልባት የሆነ የሕይወት አጣብቂኝ ውስጥ ሲገባ ፣ የሚኖርለት ነገር ሲያጣ ፣ ተስፋ የሚያደርግበት ነገር ሲጠፋው ፣ በዚህ ዓለም መኖር ትርጉሙ ሲጠፋው ያኔ "ብሄድ ይሻለኛለኛል" ብሎ የጉዞ ቲኬቱን ይቆርጣል ....[ለዚህም ነው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ "ብንሄድ ይሻለናል"በሚል የመጨረሻ የመሰናበቻ ቃል ብዙዎች እራሳቸውን ያፈረሱት]
እናም.....

ምናልባት ዛሬም በዚህ ሰዓት ቀን ሳለ የመሸባችሁ፣ የሚያስጠጋ ወዳጅ ያጣችሁ፣ ጉልበታችሁ የከዳችሁ፣ አልቅሳችሁ እንባ አልቆባችሁ እዥ እያነባችሁ ያላችሁ፣ የሚረዳ ወዳጅ አይዞህ(ሽ) የሚል ቤተሰብ ያጣችሁ፣ የሚፈርድባችሁ እንጂ የሚፈርድላችሁ ያጣችሁ፣ሁሉም ጀርባውን ያዞረባችሁ የመሰላችሁ ፣ በምንም ነገር ተስፋ ያጣችሁ ፣ ጠላት አንድ መፍትሔ ያውም እራስን የማጥፋት መፍትሔ ብቻ የሚያሳያችሁ፣ አንድ መፍትሔ ልጠቁማችሁ ስብሐተ እግዚአብሔር ወደ ሚደርስበት ቃለ እግዚአብሔር ወደሚሰማበት ወደ እግዚአብሔር ቤት(ወደ ቤ/ክ) ብትሄዱ ይሻላችኋል አዎ እሱ ይሻላችኋል።

ለጥቂት ቀናት እራሳችሁን ከዓለም ጫጫታ ሰውራችሁ ሳትናገሩ የልባችሁን ከሚረዳችሁ የልብ አውቃ አምላካችሁ ጋር በጸሎት ፣ በጾም ተነጋገሩ ከቃሉ ጋር ህብረት አድርጉ፣ በተስፋ፣በደስታ ተሞልታችሁ ፣ታሪካችሁ ተቀይሮ ትመለሳላችሁ የማይሆን ይመስላል ግን ይሆናል የቀመስኩትን ነው ቅመሱ የምላችሁ እርሱ መድኃኔዓለም የጽልመታችን ንጋት ፣ በደከመን ሰዓት ብርታት ፣ ስንወድቅ ትንሳኤያችን ፣ የበረሃ ጥላችን ነው ቢመሽም ቢጨላልምብንም እርሱን ተስፋ በማድረግ ወደ ቤቱ ብንሄድ ይሻለናል ሌሊቱን ያነጋዋልና። ለዚህ ነው ንጉሱ ዳዊት ወደ እግዚአብሔር ቤት እንሂድ ባሉኝ ጊዜ ደስ አለኝ ያለው መዝ 122 :1 እናም ወደ እግዚአብሔር ቤት ብንሄድ ይሻለናል።

01/03/2016 ዓ/ም
ሊ/ዲ/ን መባጽዮን (ኢ/ር)
ዲላ_ኢትዮጵያ
👇👇👇👇👇👇
@Yahiwenesei
@Yahiwenesei
@Yahiwenesei
ብዙ የምትማሩበት የምትባረኩበት የFacebook ቻነል እነሆ 👇👇👇

https://www.fb.com/l/6lp1kJRRR
#ጪጩ(#ዳግማዊ_ዮርዳኖስ)#ወንዝን _የአለም_ህዝብ _የሚከትምበት _የቱሪስት _መዳረሻ_እናድርግ"

እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ በሰላም አደረሳችሁ እያልኩኝ በዲላና አካባቢዋ የምትገኙ ክርስቶሳዊያን በ11/05/2016 በዕለተ ጥምቀት ጠዋት ላይ የጥምቀት ስነ ሥርዓቱን የት ተገኝታችሁ ልትጠመቁ አሰባችሁ? እነሆ አንድ ድንቅ ስፍራ ልጠቁማችሁ
ጌታ እንደተጠመቀበት እንደዮርዳኖስ ወንዝ ሁለቱ ወንዞች በሚገናኙበት በጪጩ (ዳግማዊ ዮርዳኖስ) ወንዝ መጥታችሁ ብትጠመቁ ነፍሳችሁ ሀሴት አድርጋት ትመለሳላችሁ።
ለቀጣዩ ደግሞ እግዚአብሔር ፈቃዱ ቢሆን ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመናበብ የአለም ህዝብ መጥቶ የሚጎበኝበትና የሚያከብርበት ስፍራ ብናደርገውስ ?ይቻላል አይደል? እንግዲያውስ ማስተዋወቁን ካኑኑ እንጀምር በሉ እንግዲህ ሼር ይደረግ
እንኳን አደረሳችሁ !
ሊ/ዲ/ን መባጽዮን (ኢ/ር )
ዲላ
ኢትዮጵያ
👇👇👇👇👇👇
@Yahiwenesei
@Yahiwenesei
@Yahiwenesei
2024/06/28 21:47:09
Back to Top
HTML Embed Code: