Telegram Web Link
የድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች መግቢያ ፈተና (NGAT) ውጤት መለቀቅን ተከትሎ ዩኒቨርሲቲዎች አዲስ የድኅረ ምረቃ አመልካቾችን ለመቀበል ማስታወቂያ እያወጡ ይገኛሉ።

ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲም በ2017 ዓ.ም በሁለተኛ ዲግሪ እና በሦስተኛ ዲግሪ ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተማር ለአዲስ አመልካቾች አውጥቶት የነበረውን ማስታወቂያ እስከ መስከረም 30/2017 ዓ.ም አራዝሟል።

በመሆኑም መስፈርቱን የምታሟሉና መማር የምትፈልጉ አዲስ አመልካቾች በኦንላይን https://studentportal.bdu.edu.et ማመልከት ትችላላችሁ ተብሏል።

አመልካቾች ለምዝገባ ሊያሟሏቸው የሚገቡ፦

✍️ የማመልከቻ ፎረም፥
✍️ የማመልከቻ ክፍያ ብር 300፥
✍️ በመንግስት ስፖንሰር ለሚማሩ የስፖንሰርሺፕ ፎርም፥
✍️ አመልካቾች በትምህርት ሚኒስቴር የተሰጠውን የመግቢያ ፈተና (NGAT) ማለፍ ይጠበቅባቸዋል፡፡
✍️ ኦፊሺያል ትራንስክሪፕት ከምዝገባ በፊት ለባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ማስላክ ይኖርባቸዋል፡፡
✍️ ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የሚያዘጋጀውን የመግቢያ ፈተና ወስደው ማለፍ ይኖርባቸዋል፡፡

@tikvahuniversity
#WallagaUniversity

ወለጋ ዩኒቨርሲቲ ለነባር እና አዲስ ገቢ መደበኛ የቅድመ ምረቃ እና የድኅረ ምረቃ ተማሪዎቹ ጥሪ አድርጓል።

በዚህም፦

► ነባር የቅድመ ምረቃ እና የድኅረ ምረቃ መደበኛ ተማሪዎች፥
► በ2016 ዓ.ም የሪሚዲያል ትምህርታችሁን በወለጋ ዩኒቨርሲቲ ተከታትላችሁ የማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ እንዲሁም
► በ2017 ዓ.ም ወለጋ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ አዲስ ገቢ መደበኛ የቅድመ ምረቃ ተማሪዎች በሙሉ የ2017 ትምህርት ዘመን ምዝገባ መስከረም 20 እና 21/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡

የምዝገባ ቦታ፦
በ2017 ዓ.ም ወለጋ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ አዲስ ገቢ መደበኛ የቅድመ ምረቃ ተማሪዎች ብቻ በዋናው ግቢ ነቀምት ሲሆን፤ ሌሎቻችሁ በየነበራችሁበት ካምፓስ።

@tikvahuniversity
#DebreTaborUniversity

ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ ለነባር መደበኛ የቅድመ ምረቃ ተማሪዎቹ ጥሪ አድርጓል።

በዚህም በ2016 ዓ.ም አንደኛ ዓመትና ከዚያ በላይ የነበራችሁ የደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የ2017 ትምህርት ምዝገባ ከመስከረም 28 እስከ 30/2017 ዓ.ም መሆኑ ተገልጿል፡፡

በተለያዩ ምክንያቶች በ2016 ዓ.ም ወደ ዩኒቨርሲቲው መሔድ ያልቻለችሁ እንዲሁም ዊዝድሮዋል መሙላት ሳትችሉ የቀራችሁ ተማሪዎች በዚህ ዓመት ትምህርታችሁን እንድትቀጥሉ ዩኒቨርስቲው ስለፈቀደ ከላይ በተጠቀሱት ቀናት ማመልከት ትችላላችሁ።

Note:
በ2017 ዓ.ም የመጀመሪያ ዓመት የምትቀላቀሉ (በ2016 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ተማሪ የነበራችሁና የማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ እንዲሁም በትምህርት ሚኒስቴር አዲስ የምትመደቡ) ተማሪዎች በሌላ ማስታወቂያ ጥሪ ይደረግላችኋል ተብሏል፡፡

@tikvahuniversity
የድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ውጤት መለቀቅን ተከትሎ በርካታ ዩኒቨርሲቲዎች አዲስ የድኅረ ምረቃ አመልካቾችን ለመቀበል ማስታወቂያ እያወጡ ይገኛሉ።

አመልካቾች በትምህርት ሚኒስቴር የተሰጠውን የመግቢያ ፈተና (NGAT) ማለፍ ይጠበቅባቸዋል፡፡

(የተወሰኑ ዩኒቨርሲቲዎች ያወጧቸው የጥሪ ማስታወቂያዎች ከላይ ተያይዘዋል፡፡)

@tikvahuniversity
#AAU #GAT #UAT

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሁለተኛ ዙር የድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (GAT) ዛሬ መስጠት ጀምሯል። ፈተናው እስከ ነገ መስከረም 16/2017 ዓ.ም ይሰጣል።

ፈተናውን ለመውሰድ አመልክታችሁ ስማችሁ ያልወጣ እንዲሁም ፈተናው ላለፋችሁ አመልካቾች ቀጣይ የፈተና ቀን ወደፊት እንደሚያሳውቅ ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።

ዩኒቨርሲቲው ሦስተኛ ዙር የድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (GAT) በቅርቡ ይሰጣል ማለቱ አይዘነጋም።

በሌላ በኩል ለቅድመ ምረቃ ትምህርት ፕሮግራም በማታ መርሐግብር ለመከታተል የመግቢያ ፈተና (UAT) ለምትወስዱ የፈተና ቀን ወደፊት ይገለፃል ተብሏል።

@tikvahuniversity
#DillaUniversity

ዲላ ዩኒቨርሲቲ ለሪሚዲያል ተማሪዎች አድርጎት የነበረውን ጥሪ አራዝሟል።

በ2016 ዓ.ም በሪሚዲያል ፕሮግራም በዲላ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታችሁን ተከታትላችሁ የማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ ተማሪዎች ምዝገባ መስከረም 19 እና 20/2017 ዓ.ም ይከናወናል ተብሎ የነበረ ቢሆንም፤ በተለያዩ ምክንያቶች የምዝገባው ቀን የተራዘመ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

በዚህም በ2016 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ተከታትላችሁ የማለፊያ ውጤት ያመጣች ተማሪዎች ምዝገባ፣ በ2017 ዓ.ም አዲስ ከሚመደቡ ተማሪዎች ጋር የሚከናወን መሆኑ ተገልጿል።

Note:
የሌሎች ነባር የቅድመ እና የድኅረ ምረቃ መደበኛ ተማሪዎች ምዝገባ ከዚህ ቀደም በተገለጸው መሰረት መስከረም 19 እና 20/2017 ዓ.ም ይከናወናል ተብሏል።

@tikvahuniversity
እንኳን ለደመራ በዓል አደረሳችሁ!

ቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ለመላው የክርስትና ዕምነት ተከታዮች በሙሉ መልካም የደመራ በዓል ይመኛል!

@tikvahuniversity
#ETA

የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን የሁለተኛ ሳምንት የዳግም ምዝገባ ሥራ ከመስከረም 13/2017 ዓ.ም ጀምሮ እያከናወነ ይገኛል።

በደመራ እና መስቀል በዓላት ምክንያት ዛሬ ሐሙስ መስከረም 16 እና ዓርብ መስከረም 17/2017 ዓ.ም የዳግም ምዝገባ ሥራ የማይኖር መሆኑን ባለሥልጣኑ ገልጿል።

የዳግም ምዝገባ ሥራው ቅዳሜ መስከረም 18/2017 ዓ.ም የሚቀጥል መሆኑ ተገልጿል፡፡

@tikvahuniversity
#JimmaUniversity

ጅማ ዩኒቨርሲቲ የነባር የቅድመ ምረቃ መደበኛ ተማሪዎች የምዝገባ ጊዜን አራዝሟል።

ዩኒቨርሲቲው የነባር የቅድመ ምረቃ መደበኛ ተማሪዎች ምዝገባ መስከረም 20 እና 21/2017 ዓ.ም ይካሄዳል ብሎ የነበረ ቢሆንም፤ ባልተገለፀ ምክንያት የምዝገባ ጊዜው ተራዝሟል።

Note:
ነባር የድኅረ ምረቃ ፕሮግራም ተማሪዎች እንዲሁም የሕክምናና ጥርስ ሕክምና ተማሪዎች ምዝገባ በቀድሞው ጥሪ ማለትም መስከረም 20 እና 21/2017 ዓ.ም የሚካሄድ መሆኑ ተገለጿል።

@tikvahuniversity
#DebreBerhanUniversity

በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የርቀት እና ተከታታይ ትምህርት ፕሮግራም ማስተባበሪያ በ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ለነባር የመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎች የምዝገባ ጊዜ ከመስከረም 27 እስከ 29/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

የነባር የሁለተኛ ዲግሪ የርቀት እና ተከታታይ ትምህርት ፕሮግራም ተማሪዎች ምዝገባ ከጥቅምት 4 እስከ 6/2017 ዓ.ም መሆኑ ተገልጿል።

(የዩኒቨርሲቲው መልዕክት ከላይ ተያይዟል።)

@tikvahuniversity
2024/10/03 23:24:09
Back to Top
HTML Embed Code: