Telegram Web Link
#ይመዝገቡ

ዓለም አቀፍ ተቀባይነት ያለው ሰርትፍኬት ማግኘት የሚያስችልዎትን ስልጠና ይውሰዱ።

አምስት ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደሮች ኢንሼቲቭ በአራት የስልጠና ዘርፎች የኦንላይን ስልጠና ይሰጣል፦

► በዌብ-ፕሮግራሚንግ፣
► በአንድሮይድ ማበልፀግ፣
► በዳታ ሳይንስ እና
► በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ።

ስልጠናውን በተሰጠው ጊዜ (ስምንት ሳምንት) ያጠናቀቁ ሰልጣኞች ዓለም አቀፍ ተቀባይነት ያለው ሰርተፊኬት ይበረከትላቸዋል።

ለመመዝገብ 👇
https://www.ethiocoders.et/

@tikvahuniversity
#DebreBerhanUniversity

ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ነባር የቅድመ ምረቃ እና የድኅረ ምረቃ መደበኛ ተማሪዎች የ2017 ትምህርት ዘመን ምዝገባ መስከረም 29 እና 30/2017 ዓ.ም እንደሚከናወን አሳውቋል።

በቅጣት የመመዝገቢያ ጊዜ ጥቅምት 1/2017 ዓ.ም ሲሆን፤ ትምህርት ጥቅምት 4/2017 ዓ.ም ይጀምራል ተብሏል።

@tikvahuniversity
#OdaBultumUniversity

ኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ ነባር የመደበኛ ፕሮግራም ተማሪዎች የ2017 ትምህርት ዘመን ምዝገባ መስከረም 21 እና 22/2017 ዓ.ም እንደሚከናወን አሳውቋል።

የሪሚዲያል ፕሮግራም ስትከታተሉ ቆይታችሁ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ነጥብ ላስመዘገባችሁ እና በ2017 ዓ.ም በኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ አዲስ ለምትመደቡ ተማሪዎች የመመዝገቢያ ቀን በሌላ ማስታወቂያ ወደፊት ጥሪ ይደረጋል ተብሏል።

@tikvahuniversity
👏🏽  ሞራል ለኮከቦቻችን! ቪድዮአቸውን ላይክ እያደረግን ምርጥ 20 ውስጥ እናስገባቸው!  👏🏽 

እስከ መስከረም 20/2017 ዓ.ም ብቻ!

የዲጂታል ሙዚቃ ውድድርን ለመቀላቀል፦

🎥 የአንድ ደቂቃ የራሳችን ሙዚቃ ቪዲዮ በTikTok ላይ እንፖስት
🏷 #1Wedefit እና #የምትኖሩበት ከተማ አድራሻ ማስገባት እንዳትረሱ
📲 የTikTok ደረገጽ @Safaricomet ታግ እናድርግ

እንዝፈን! እንፖስት! እናሸንፍ!

መልካም ዕድል!

#SafaricomEthiopia
#1Wedefit
#FurtherAheadTogether #DigitalMusicChallenge
#የቴክኖ የአዲስ ዓመት ልዩ የበዓል ስጦታ!

የአዲስ ዓመት ልዩ ስጦታ ከቴክኖ ሞባይል ኢትዮጵያ! ከየትኛውም የቴክኖ ሱቅ የቴክኖ ስማርት ስልክን ሲገዙ አብሮዎት ካለ ወዳጅ ዘመድ ወይም ጓደኛ ጋር ፎቶ በመነሳት የማኅበራዊ ገፅዎት ላይ በመለጠፍ እና ብዙ ላይክ በማግኘት የዱባይ ደርሶ መልስ የቢዝነስ ክላስ የአውሮፕላን ትኬት፣ ላፕቶፖች፣ የቴክኖ ስማርት ስልኮች እና ገደብ አልባ የኢንተርኔት ፓኬጆችን ይሸለሙ፡፡

የውድድሩ መመሪያ
1. የቴክኖ ኢትዮጵያን ፌስቡክ፣ ኢንስታግራም እና ቲክቶክ ገፆችን ፎሎው ያድርጉ፡፡
2. የተነሱትን ፎቶ በመረጡት ማኅበራዊ ሚዲያ ሲለጥፉ የቴክኖ ኢትዮጵያን ገፅ ከፖስትዎት ጋር ታግ ያድርጉ፡፡ ብዙ ላይክ እና ኢንጌጅመንት ያገኘው ተሸላሚ ይሆናል፡፡

Tag ሲያደርጉን
ለ Facebook @TecnoEt https://www.facebook.com/share/KpViroSyJgPe1bML/?mibextid=qi2Omg
ለ Instagram @TecnoMobileEthiopia https://www.instagram.com/tecnomobileethiopia?igsh=cjdwdjQzbGlvaDV1
ለ TikTok @TecnoEt
https://www.tiktok.com/@tecnoet?_t=8pQuOpSYlGP&_r=1 ሜንሽን ማድረግ እንዳይረሱ።
በተጨማሪም #TecnoEt2017 ኪወርድን መጠቀም እንዳይረሱ!
ራያ ዩኒቨርሲቲ የነባር መደበኛ የቅድመ ምረቃ መርሐግብር ተማሪዎችን እየተቀበለ ነው።

ዩኒቨርሲቲው ለነባር ተማሪዎች መስከረም 13 እና 14/2017 ዓ.ም ጥሪ ማድረጉ ይታወቃል።

@tikvahuniversity
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የፎረንሲክ ምርመራ ማዕከል ሥራ አስጀምሯል።

የማዕከሉ ሥራ መጀመር አገልግሎቱን በአካባቢው ለሚገኙ ማኅበረሰብ ለመስጠት ያስችላል ተብሏል።

@tikvahuniversity
#ጥቆማ

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቻይንኛ ቋንቋ አጭር ስልጠና ምዝገባ ላይ ነው።

ስልጠናው ቅዳሜ ጠዋት ከ3:00-5:00 ለአስር ተከታታይ ሳምንት የሚሰጥ ሲሆን፤ ስልጠናውን ለሚያጠናቅቁ ሰርተፊኬት ይሰጣል።

የምዝገባ ቦታ፦
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ኮንፊሽየስ ኢንስቲትዩት፥ 6 ኪሎ ዋና ግቢ፣ 8ኛ ፍሉር ፎረም ህንጻ

ምዝገባ የሚያበቃው፦
መስከረም 21/2017 ዓ.ም

ስልጠናው የሚጀምረው፦
መስከረም 25/2017 ዓ.ም

የስልጠናው ቦታ፦
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 6 ኪሎ ካምፓስ

@tikvahuniversity
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ስቴም ማዕከል ለአስር ተከታታይ ሳምንታት ሲሰጥ የቆየውን ስልጠና አጠናቋል።

ማዕከሉ Brighter Generation ከተባለ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ጋር በመተባበር ከአምስት የመንግስትና የግል ትምህርት ቤቶች ተመርጠው ለመጡ 18 ተማሪዎች ስልጠናውን ሰጥቷል።

@tikvahuniversity
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ራስ ገዝ ለመሆን ቅድመ ዝግጅት እያደረገ ነው።

ዩኒቨርሲቲው በቀጣይ ራስገዝ ሲሆን ትኩረት የሚያደርግባቸው አምስት ዘርፎች ተለይተው የቅድመ ዝግጅት ሥራ መጀመሩን የተቋሙ አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ፍስሀ ጌታቸው (ዶ/ር) ለኢዜአ ተናግረዋል።

ግብርናና ላይፍ ሳይንስ፣ የጤና ሳይንስና ህክምና፣ ፊዚካል ሳይንስ፣ ማኅበራዊ ሳይንስና ሂዩማኒቲስ እንዲሁም የመምህራን ስልጠና የተለዩ አምስቱ ዘርፎች መሆናቸውን ገልጸዋል።

የእነዚህ ዘርፎች ልየታና የስርዓተ ትምህርት ክለሳ እንደሚደረግም ጠቁመዋል።

@tikvahuniversity
#AAU #GAT

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (GAT) ሁለተኛ ዙር ፈተና ነገ መሰጠት ይጀምራል።

ፈተናው ከነገ መስከረም 15/2017 ዓ.ም ጀምሮ ለሁለት ቀናት ይሰጣል።

በጠዋት እና ከሰዓት ክፍለ ጊዜ ለሚሰጠው ፈተና የተፈታኞች ኮድና ስም ዝርዝር እንዲሁም የመፈተኛ ክፍል ከላይ ከተያያዙት ኤክሴሎች ይመልከቱ፡፡

ሦስተኛ ዙር ፈተና የድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (GAT) የሚሰጥበትን ቀን በቅርቡ እንደሚያሳውቅ ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።

@tikvahuniversity
2024/10/04 09:31:14
Back to Top
HTML Embed Code: