Telegram Web Link
#ጥቆማ

የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ በ2017 ትምህርት ዘመን በድኅረ-ምረቃ መርሐግብር በ Extension (ቅዳሜና እሁድ) ፕሮግራም አመልካቾችን ተቀብሎ ማስተማር ይፈልጋል።

የትምህርት መስኮች

- General Public Health,
- Health Care Quality,
- Reproductive Health and
- Epidemology

የምዝገባ ጊዜ፦
ከመስከረም 8-30/2017 ዓ.ም


የምዝገባ ቦታ፦
በኮሌጁ ሬጅስትራር ቢሮ

መስፈርቶች
- ከታወቀ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም በጤና ሳይንስ የመጀመሪያ ዲግሪ
- የድኅረ ምረቃ መግቢያ ፈተና (GAT) ያለፈ/ች

@tikvahuniversity
#GambellaUniversity

ጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ ነባር የቅድመ ምረቃ እና የድኅረ ምረቃ መደበኛ ተማሪዎች የምዝገባ ጊዜ መስከረም 20 እና 21/2017 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል።

ትምህርት መስከረም 22/2017 ዓ.ም ይጀመራል ተብሏል።

አዲስ ገቢ የድኅረ ምረቃ ፕሮግራም አመልካቾች የመግቢያ ፈተና ውጤት እንደተለቀቀ ጥሪ እንደሚደረግ ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።

የሪሚዲያል ተማሪዎች እና የ2017 ዓ.ም አዲስ ገቢ ተማሪዎች ጥሪ በጋራ ወደፊት ይደረጋል ተብሏል።

@tikvahuniversity
Tikvah-University
#AddisAbabaUniversity በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ2017 ዓ.ም #በቀን_መደበኛ መርሐግብር በመንግስት ስኮላርሽፕ እና በግል ከፍላችሁ የመጀመሪያ ዲግሪ ትምህርት ለመማር የምታመለክቱ ዝርዝር መስፈርቶችን በማሟላት በ https://portal.aau.edu.et ወይም www.aau.edu.et ላይ መመዝገብ ትችላላችሁ ተብሏል። አመልካቾች የዩኒቨርሲቲውን የመግቢያ ፈተና (UAT) እና ዩኒቨርሲቲው…
Application Procedure :For Addis Ababa University Undergraduate Programs

1. Open the portal of Addis Ababa University https://portal.aau.edu.et 

2. Click on 'Apply for Admission' on the left side

3. On the top bar, you will find the undergraduate drop-down menu. You can click on the Programs button to view Undergraduate programs

4. After reviewing the programs, Click on Apply.

5. You will find the general information and the application steps on the front page of the apply button. Once you read it, click on the 'Continue' button and it will direct you to the programs for choosing.

6. Once you decide on the program of your choice, click on the program and press the 'Continue' button to create an applicant account.

7. Fill out the required information on the Create Undergraduate Applicant Account page. Use a valid email and phone number and record the password you entered on the page for future use. Once finished, click the 'CREATE ACCOUNT' button.

8. Log in using the 'LOG IN' button on the top-right corner of the page with the email address and password you used to create the account.

9. Fill out the required information on the Your Academic Profile page, Click on UPDATE, and then click NEXT.

10. Select admission Type(Regular/Extension)

11. Choose Government Scholarship/Self-Sponsorship on the Financing Your Study form

12. If you choose a Government Scholarship, upload an official letter from your regional Woreda or Sub-City in Addis Ababa resident indicating your family’s financial status. Then  Select your Program of Choice and Click on Continue

13. If you select Self-Sponsored, select the four options provided on the Program Choice form and Click Continue.

14. Upload your 12th-grade result certificate and transcript for the grades 9 to 12

15. Undergraduate Admission Test (UAT) Exam Location Select the location of the entrance exam from the options provided

16. Read the Consent Statement, select Accept and Click CONTINUE.

17. To pay the amount specified for the registration and UAT test, Click on Continue to Payment and then Click on Proceed.

18. Complete your payment through Telebirr

19. Click on UAT ADMISSION TICKET to get UAT exam ticket

20. Click on EXAM SCHEDULE to review your UAT exam schedule

21. Click on EXAM RESULT to review your UAT results once available.

22. Open SEE ADMISSION STATUS to know the final result of admission

(Addis Ababa University)

@tikvahuniversity
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የ2017 የመጀመሪያ ሴሚስትር ምዝገባ ቀናት ይፋ አድርጓል።

የመጀመሪያ ዲግሪ መደበኛ ፕሮግራምና ሁሉም የድህረ ምረቃ ተማሪዎች (መደበኛ እና የእረፍት ቀናት) ምዝገባ መስከረም 20-21 /2017 ነው።

የማታና የእረፍት ቀናት የመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎች ምዝገባ መስከረም 23 -25/2017 ዓ/ም ነው።

@tikvahuniversity
#ጥቆማ

በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ቴክስታይል እና ፋሽን ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት በአዲስ አበባና ዙሪያዋ ለሚገኙ ትምህርት ፈላጊዎች የ2ኛ ዲግሪ የትምህርት ዕድል አመቻችቷል።

ኢንስቲትዩት በአዲስ አበባ ቅርንጫፍ የሁለተኛ ዲግሪ ተማሪዎችን ተቀብሎ በተከታታይ እና በማታ መርሐግብር ማስተማር ይፈልጋል፡፡

የሁለተኛ ዲግሪ የትምህርት መስኮች

- በፋሽን ዲዛይን
- በጨርቃጨርቅ ማኑፋክቸሪንግ
- በፋሽን ቴክኖሎጂ
- በፋይበር ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ
- በቴክስታይል ኬምስትሪ
- በቆዳ ውጤቶች ዲዛይንና ኢንጂነሪንግ

የምዝገባ ጊዜ፦
እስከ መስከረም 14/2017 ዓ.ም

የማመልከቻውን ቅፅ በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ድረ-ገጽ https://bdu.edu.et/registrar/ ላይ ማግኘት ይቻላል።

@tikvahuniversity
#AAU #GAT

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (GAT) በመጀመሪያ ዙር ለመውሰድ አመልክታችሁ ፈተናውን ሳትወስዱ የቀራችሁ ቀጣይ ፈተናውን የምትወስዱበት ቀን በቅርቡ እንደሚገለፅ ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

የተራዘመው የሁለተኛ ዙር GAT ፈተና የማመልከቻ ግዜ ዛሬ መስከረም 8/2017 ዓ.ም እንደሚጠናቀቅ ይታወቃል፡፡

እስካሁን ካላመለከቱ በቀሩት ሰዓታት በኦንላይን https://portal.aau.edu.et ያመልክቱ።

@tikvahuniversity
በፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን በቃሊቲ ማረሚያ ማዕከል በመደበኛ የትምህርት መርሐግብር ትምህርታቸውን ተከታትለው የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከወሰዱ 21 የተፈጥሮ ሳይንስ የህግ ታራሚ ተማሪዎች መካከል ሰባቱ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ማምጣት መቻላቸው ተገለፀ።

የቃሊቲ ማረሚያ ማዕከል የመጀመሪያ ደረጃና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ሳምሶን ወንድሜነህ የህግ ታራሚ ተማሪዎች ምንም እንኳ በህግ ጥላ ስር ቢሆኑም ትምህርታቸውን በአግባቡ ሲከታተሉ መቆየታቸውንና ለውጤት እንደበቁ ገልፀዋል፡፡

የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት ያመጡት የህግ ታራሚ ተማሪዎች ያመጡት ውጤት ለመታረማቸው ማሳያ በመሆኑ የፍትህ ሚኒስቴር በይቅርታና ምህረት መልቀቅ የሚችልበትን ዕድል እንዲያገኙ፣ ካልሆነም ትምህርታቸውን በርቀት እንዲከታተሉ ዩኒቨርሲቲዎች እንዲያመቻችሏቸው ጠይቀዋል፡፡ #ebc

@tikvahuniversity
Tikvah-University
Photo
#Update
#AASTU #ASTU

አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በ2017 ዓ.ም በአፕላይድ ሳይንስ እና በኢንጂነሪንግ የትምህርት ዘርፎች ትምህርታችሁን መከታተል ለምትፈልጉ ተቋማቱ መስፈርቶችን ይፋ ማድረጋቸው ይታወቃል።

ሁለቱ ዩኒቨርሲቲዎች ለመግባት ተከታዩን ሊንክ በመጠቀም በኦንላይን ይመዝገቡ 👇
https://stuoexam.astu.edu.et/registrationnew.php

@tikvahuniversity
#የቴክኖ የአዲስ ዓመት ልዩ የበዓል ስጦታ!

የአዲስ ዓመት ልዩ ስጦታ ከቴክኖ ሞባይል ኢትዮጵያ! ከየትኛውም የቴክኖ ሱቅ የቴክኖ ስማርት ስልክን ሲገዙ አብሮዎት ካለ ወዳጅ ዘመድ ወይም ጓደኛ ጋር ፎቶ በመነሳት የማኅበራዊ ገፅዎት ላይ በመለጠፍ እና ብዙ ላይክ በማግኘት የዱባይ ደርሶ መልስ የቢዝነስ ክላስ የአውሮፕላን ትኬት፣ ላፕቶፖች፣ የቴክኖ ስማርት ስልኮች እና ገደብ አልባ የኢንተርኔት ፓኬጆችን ይሸለሙ፡፡

የውድድሩ መመሪያ
1. የቴክኖ ኢትዮጵያን ፌስቡክ፣ ኢንስታግራም እና ቲክቶክ ገፆችን ፎሎው ያድርጉ፡፡
2. የተነሱትን ፎቶ በመረጡት ማኅበራዊ ሚዲያ ሲለጥፉ የቴክኖ ኢትዮጵያን ገፅ ከፖስትዎት ጋር ታግ ያድርጉ፡፡ ብዙ ላይክ እና ኢንጌጅመንት ያገኘው ተሸላሚ ይሆናል፡፡

Tag ሲያደርጉን
ለ Facebook @ TecnoEt https://www.facebook.com/share/KpViroSyJgPe1bML/?mibextid=qi2Omg
ለ Instagram @ TecnoMobileEthiopia https://www.instagram.com/tecnomobileethiopia?igsh=cjdwdjQzbGlvaDV1
ለ TikTok @ TecnoEt
https://www.tiktok.com/@tecnoet?_t=8pQuOpSYlGP&_r=1 ሜንሽን ማድረግ እንዳይረሱ።
በተጨማሪም #TecnoEt2017 ኪወርድን መጠቀም እንዳይረሱ!
#Update

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቅድመ ምረቃ እና የድኅረ ምረቃ ተማሪዎችን ለመቀበል የማመልከቻ ግዜን አራዝሟል።

የመግቢያ ፈተና የሚሰጥባቸውን ቀናትም ይፋ አይርጓል፡፡

በዚህም የቅድመ ምረቃ #መደበኛ መርሐግብር የማመልከቻ ቀን እስከ ነገ መስከረም 9/2017 ዓ.ም የተራዘመ ሲሆን የመግቢያ ፈተና (UAT) መስከረም 11/2017 ዓ.ም ይሰጣል።

የቅድመ ምረቃ #የማታ መርሐግብር የማመልከቻ ቀን እስከ መስከረም 13/2017 ዓ.ም የተራዘመ ሲሆን የመግቢያ ፈተና (UAT) መስከረም 15/2017 ዓ.ም ይሰጣል።

የድኅረ ምረቃ መርሐግብር የማመልከቻ ቀን እስከ መስከረም 13/2017 ዓ.ም የተራዘመ ሲሆን የመግቢያ ፈተና (GAT) መስከረም 15/2017 ዓ.ም ይሰጣል።

(ተጨማሪ መልዕክት ከላይ ተያይዟል።)

@tikvahuniversity
Tikvah-University
#AAU #GAT በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (GAT) በመጀመሪያ ዙር ለመውሰድ አመልክታችሁ ፈተናውን ሳትወስዱ የቀራችሁ ቀጣይ ፈተናውን የምትወስዱበት ቀን በቅርቡ እንደሚገለፅ ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል። የተራዘመው የሁለተኛ ዙር GAT ፈተና የማመልከቻ ግዜ ዛሬ መስከረም 8/2017 ዓ.ም እንደሚጠናቀቅ ይታወቃል፡፡ እስካሁን ካላመለከቱ በቀሩት ሰዓታት በኦንላይን…
AAUGAT_Schedule neww.xls
146 KB
#AAU #GAT

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (GAT) በመጀመሪያ ዙር ለመውሰድ አመልክተው ፈተናውን ሳትወስዱ ለቀሩ አመልካቾች ፈተናውን መስከረም 15/2017 ዓ.ም እንደሚሰጥ ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

ረዕቡ መስከረም 15/2017 ዓ.ም ጠዋት ለሚሰጠው ፈተና የተፈታኞች ኮድና ስም ዝርዝር፣ የመፈተኛ ካምፓስ፣ የመፈተኛ ላብ እንዲሁም የኮምፒውተር ክፍል ከላይ ከተያያዘው ኤክሴል ይመልከቱ፡፡

@tikvahuniversity
#AssosaUniversity

አሶሳ ዩኒቨርሲቲ የ2017 ትምህርት ዘመን የመደበኛ ተማሪዎች መግቢያ ጊዜ መስከረም 27 እና 28/2017 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል።

የዕረፍት ቀናት ተማሪዎች የመመዝገቢያ ቀን መስከረም 25 እና 26/2017 ዓ.ም መሆኑ ተገልጿል።

(የዩኒቨርሲቲው መልዕክት ከላይ ተያይዟል።)

@tikvahuniversity
#Update

የመፈተኛ ጣቢያዎች ማስተካከያ ያድርጉ!

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለ2017 ዓ.ም በቅድመ ምረቃ ፕሮግራም ለመማር ያመለከታችሁ አመልካቾች የመግቢያ ፈተና (UAT) ለመውሰድ የፈተና ቦታዎችን መምረጣችሁ ይታወቃል፡፡

ይሁን እንጂ ፈተናው በተወሰኑ ጣቢያዎች ብቻ እንዲሰጥ መወሰኑን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል፡፡

በዚህም አመልካቾች የመፈተኛ ቦታችሁን ከዚህ በታች በተዘረዘሩት ዩኒቨርሲቲዎች ከሚገኙ ጣቢያዎች ብቻ በመምረጥ ማስተካከያ ቅያሪ እንድታደርጉ ዩኒቨርሲቲው ጠይቋል።

- አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ
- አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቢሾፍቱ ካምፓስ
- አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ
- አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ
- ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ
- ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ
- ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
- ጅማ ዩኒቨርሲቲ
- መቐለ ዩኒቨርሲቲ
- ወሎ ዩኒቨርሲቲ
- የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ
- ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ
- ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ሜዲካል ኮሌጅ

@tikvahuniversity
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ስኮላርሺፕ

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ2016 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ወስደው 500 እና ከዚያ በላይ ውጤት ላስመዘገቡ 200 ተማሪዎች በውድድር ነፃ የትምህርት ዕድል ሊሰጥ ነው።

በውድድር ነፃ የትምህርት ዕድሉን የሚያገኙ ተማሪዎች የዶርሚታሪ እንዲሁም የካፌ አገልግሎት ተጠቃሚም ይሆናሉ ተብሏል።

ዩኒቨርሲቲው በውድድሩና ነፃ የትምህርት ዕድሉ ዙሪያ ተጨማሪ መረጃዎችን በቀጣይ ይፋ እንደሚያደርግ ይጠበቃል።

@tikvahuniversity
#ArsiUniversity

አርሲ የኒቨርሲቲ የመደበኛ ነባር ተማሪዎች እንዲሁም በ2017 ዓ. ም ወደ አርሲ ዩኒቨርሲቲ በመጀመሪያ ዲግሪ መደበኛ መረሐግብር የተመደባችሁ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ መግቢያ እና የመመዝገቢያ ቀናት መስከረም 20 እና 21/2017 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል።

ዩኒቨርሲቲው የነባር ተማሪዎች የካምፓስ ሽግሽግ ያደረገ ሲሆን፤ የሜዲሲን 1ኛ እና 2ኛ ዓመት፣ የኮምፒዩተር ሳይንስ 1ኛ እና 2ኛ ዓመት እንዲሁም የህግ 1ኛ እና 2ኛ ዓመት ዲንሾ ካምፓስ የተመደባችሁ መሆኑ ተገልጿል። የ2014 ዓ.ም ባች የፋርማሲ፣ የሜዲካል ላቦራቶሬ እና የነርሲንግ ተማሪዎች ጤና ኮሌጅ ካምፓስ ተመድባችኋል፡፡

@tikvahuniversity
Tikvah-University
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ስኮላርሺፕ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ2016 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ወስደው 500 እና ከዚያ በላይ ውጤት ላስመዘገቡ 200 ተማሪዎች በውድድር ነፃ የትምህርት ዕድል ሊሰጥ ነው። በውድድር ነፃ የትምህርት ዕድሉን የሚያገኙ ተማሪዎች የዶርሚታሪ እንዲሁም የካፌ አገልግሎት ተጠቃሚም ይሆናሉ ተብሏል። ዩኒቨርሲቲው በውድድሩና ነፃ የትምህርት ዕድሉ ዙሪያ ተጨማሪ…
#Update

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ2016 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ወስደው 500 እና ከዚያ በላይ ውጤት ላስመዘገቡ 200 ተማሪዎች በውድድር ነፃ የትምህርት ዕድል እንደሚሰጥ ዛሬ መግለፁ ይታወቃል።

እንዴት ማመልከት ይችላሉ?

በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ወስደው ከ500 በላይ ውጤት ያመጡ የተፈጥሮ እና የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪ ከሆኑ ያመልክቱ።

https://portal.aau.edu.et በመግባት Apply for Admission የሚለውን በመጫን መሰረታዊ መረጃዎች ከሞሉ በኋላ Sponsorship ለሚለው Government Scholarship የሚለውን በመምረጥ Other Reason ለሚለው “more than 500 and above” በማለት በክፍት ቦታው ላይ በመፃፍ የ12ኛ ውጤት ያስመዘገባችሁበትን የሚያሳይ ማስረጃ ማያያዝ ያስፈልጋል፡፡

የማመልከቻ ጊዜ 👇
ሐሙስ መስከረም 9/2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 1፡00 ሰዓት እስከ ምሽቱ 12፡00 ሰዓት ድረስ

ይህ ጥሪ ከዚህ ቀደም ያመለከቱት አመልካቾች አያካትትም።

@tikvahuniversity
Tikvah-University
#Update የጤና ባለሙያዎች የብቃት ምዘና ፈተና መርሐግብር የጤና ባለሙያዎች የብቃት ምዘና ፈተና ከመስከረም 8-10/ 2017 ዓ.ም ይሰጣል። የብቃት ምዘና ፈተናው መርሃሐግብር፦ መስከረም 8/2017 ዓ.ም Medicine, Pharmacy, Anesthesia, Dental Medicine, Environmental Health, Psychiatric Nursing and Surgical Nursing. መስከረም 9/2017…
የጤና ባለሙያዎች የብቃት ምዘና ፈተና ዛሬ መስከረም 8/ 2017 ዓ.ም መሰጠት ጀምሯል። ፈተናው እስከ መስከረም 10/ 2017 ዓ.ም ለሦስት ተከታታይ ቀናት ይሰጣል።

የብቃት ምዘና ፈተናውን ለመውሰድ Addis Ababa Science and Technology Institute (አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት) የመፈተኛ ጣቢያ የመረጣችሁ ተመዛኞች ፈተናው የሚሰጠው በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ (5 ኪሎ ካምፓስ) መሆኑን ጤና ሚኒስቴር ገልጿል፡፡

@tikvahuniversity
Tikvah-University
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና ዩኒቲ ዩኒቨርሲቲ ከቡሉምበርግ ሚዲያ ኢኒሼቲቭ አፍሪካ ጋር በመተባበር የፋይናሻል ጋዜጠኝነት ስልጠና ሊሰጡ ነው፡፡ ስልጠናውን በተመለከተ የፕሮግራም ትውውቅ በዛሬው ዕለት የተካሔደ ሲሆን፤ ስልጠናው በዩኒቨርሲቲዎቹ የጋዜጠኝነት ተማሪዎች እንዲሁም በሥራ ላይ ላሉ ጋዜጠኞች የፋይናሻል ዘገባ ግንዛቤያቸውን የሚያሳድግ መሆኑ ተገልጿል፡፡ በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ፣ የካፒታል ገበያ ሌሎች…
ብሉምበርግ ሚዲያ ኢኒሼቲቭ አፍሪካ (BMIA) የፋይናንሺያል ጋዜጠኝነት ስልጠና ፕሮግራም በኢትዮጵያ መስጠት ጀመረ።

55 ከመገናኛ ብዙሃን፣ ከፋይናንስ ዘርፍ እና ከመንግስት ሴክተሮች የተውጣጡ ሰልጣኞች በመጀመሪያው ዙር ስልጠና ይሳተፋሉ ተብሏል።

የንግድ እና የፋይናንስ ጋዜጠኝነትን ለማሳደግ ያለመው ፕሮገራሙ፤ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ ከዩኒቲ ዩኒቨርሲቲ እና ከኬንያው ስትራትሞር ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ይሰጣል።

ተሳታፊዎች በመረጃ ትንተና፣ ካፒታል ገበያ፣ ኢኮኖሚክስ እና ፐብሊክ ፖሊሲ ​​ላይ ስልጠና ይወስዳሉ ተብሏል።

@tikvahuniversity
ጂንካ ዩኒቨርሲቲ በአቅራቢያው ለሚገኙ ዞኖች ነፃ የትምህርት ዕድል እንደሚሰጥ ይታወቃል።

አሪ፣ ደቡብ ኦሞ፣ ኮንሶ፣ ቡርጂ፣ ጋርዱላ፣ ኮሬ፣ አሌ እና ባስኬቶ ዞኖች የዕድሉ ተጠቃሚ የሆኑ ስምንት ዞኖች ናቸው።

ዞኖቹ የዕድሉ ተጠቃሚ ሊሆኑ የሚችሉ ሰዎችን መልምለው በአካል ተገኝተው እንዲያመለክቱ ጠይቆ የነበረ ቢሆንም፤ በዩኒቨርሲቲው የመደበኛ ተማሪዎች ጥሪ ላልተወሰነ ጊዜ በመራዘሙ ምክንያት ለነፃ ትምህርት የተመለመሉ አመልካቾች ምዝገባም ተራዝሟል።

ሌላ ጥሪ እስከሚደረግ ድረስ በትዕግስት እንዲጠብቁ ዩኒቨርሲቲው ጠይቋል።

@tikvahuniversity
2024/09/30 19:20:10
Back to Top
HTML Embed Code: