Telegram Web Link
#ArbaMinchUniversity

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ለነባር መደበኛ ተማሪዎቹ ጥሪ አድርጓል።

በዚህም የኮሌጁ የመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎች የ2017 ትምህርት ዘመን የመግቢያ ቀን መስከረም 9/2017 ዓ.ም፣ የመመዝገቢያ ቀን መስከረም 10/2017 ዓ.ም እና ትምህርት የሚጀምርበት ቀን መስከረም 11/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

@tikvahuniversity
Tikvah-University
#JinkaUniversity ጂንካ ዩኒቨርሲቲ የነባር መደበኛ ተማሪዎች፣ በ2016 ዓ.ም በሪሚዲያል ፕሮግራም በጂንካ ዩኒቨርሲቲ በመደበኛ መርሐግብር ትምህርታችሁን ተከታትላችሁ የማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ እንዲሁም በ2017 ዓ.ም በፍሬሽማን ፕሮግራም በትምህርት ሚኒስቴር ጂንካ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ ተማሪዎች የ2017 ትምህርት ዘመን ምዝገባ የሚከናወነው መስከረም 7 እና 8/2017 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል።…
#JinkaUniversity

ጂንካ ዩኒቨርሲቲ ለነባር መደበኛ ተማሪዎች አድርጎት የነበረውን ጥሪ አራዝሟል፡፡

ዩኒቨርሲቲው የነባር ተማሪዎች የ2017 ትምህርት ዘመን ምዝገባ መስከረም 7 እና 8/2017 ዓ.ም ይከናወናል ብሎ የነበረ ቢሆንም፤ ምዝገባው ላልተወሰነ ጊዜ የተራዘመ መሆኑን አሳውቋል፡፡

በቀጣይ ሌላ የጥሪ ማስታወቂያ እስከሚደረግ ድረስ ተማሪዎቹ በትዕግስት እንድትጠብቁ ዩኒቨርሲቲው ጠይቋል፡፡

@tikvahuniversity
ለቻርጀር መሯሯጥ ድሮ ቀረ!
ገና ቀኑ ሳይጋመስ የሚያልቅ ባትሪ አላማረራችሁም? እንግዲያውስ ቅመም Itel Pro ለእናንተ ነው! ባለ የ4000mAh የባትሪ አቅም ያለው ቅመም Itel በአንድ ጊዜ ቻርጅ ብቻ ለሁለት ቀናት እንደልባችሁ ስልካችሁን መጠቀም ያስችላችኋል! ቅመም Itel Pro በሄዳችሁበት ሁሉ አብሯችሁ ነው!
ሁለት የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የ2016 ዓ.ም የብሩህ ኢትዮጵያ የቢዝነስ ሃሳብ ውድድር አሸናፊ ሆነዋል፡፡

በመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የኮምፒዩቲንግ ኮሌጅ ተማሪዎች የሆኑት በእምነት ጥላሁን እና ቶማስ ግዛው የ2016 ዓ.ም የብሩህ ኢትዮጵያ የቢዝነስ ሃሳብ ውድድር አሸናፊ ሆነዋል፡፡

ተማሪዎቹ በሠሯቸው የቴክኖሎጂ ውጤቶች (Mesob እና Pain የተባሉ የሞባይል መተግበሪያዎች) እያንዳንዳቸው የ 2,000 የአሜሪካ ዶላር ተሸላሚ ሆነዋል፡፡

@tikvahuniversity
#SamaraUniversity

ሠመራ ዩኒቨርሲቲ ለሁሉም ነባር መደበኛ ተማሪዎቹ ጥሪ አድርጓል።

ነባር መደበኛ ተማሪዎች (ቅድመ ምረቃ እና ድኅረ ምረቃ) የ2017 ትምህርት ዘመን የመመዝገቢያ ጊዜ መስከረም 09 እና 10/2017 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል፡፡

ትምህርት የሚጀምረው መስከረም 13/2017 ዓ.ም መሆኑ ተገልጿል፡፡

በ2016 ዓ.ም በሪሚዲያል ፕሮግራም በሠመራ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታችሁን ተከታትላችሁ የማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ እንዲሁም በ2017 ዓ.ም በፍሬሽማን ፕሮግራም በትምህርት ሚኒስቴር ሠመራ ዩኒቨርሲቲ የምትመደቡ አዲስ ተማሪዎች የመግቢያ ጊዜ ወደፊት በሌላ ማስታወቂያ የሚገለፅ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡

@tikvahuniversity
Tikvah-University
#ASTU አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ለነባር መደበኛ ተማሪዎቹ ጥሪ አድርጓል። በዚህም የ2ኛ ዓመትና ከዚያ በላይ ነባር መደበኛ የቅድመ እና የድኅረ ምረቃ ተማሪዎች የ2017 ትምህርት ዘመን የምዝገባ ቀናት መስከረም 21 እና 22/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል። ትምህርት የሚጀመርበት ቀን መስከረም 23/2017 ዓ.ም መሆኑ ተገልጿል፡፡ በቅጣት ለመመዝገብ 👇 መስከረም 23 እና…
#ASTU

የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የ2ኛ ዓመት መደበኛ ተማሪዎች ከመስከረም 04/2017 ዓ.ም ጀምሮ በዩኒቨርሲቲው በመገኘት ሪፖርት አድርጉ ተብሏል፡፡

የ2016 ዓ.ም የሁለተኛ ሴሚስቴር ማጠናቀቂያ ፈተና የሚሰጠው ከመስከረም 07-14/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል፡፡

በመሆኑም ሁሉም የዩኒቨርሲቲው የ2ኛ ዓመት መደበኛ ተማሪዎች ከመስከረም 04/2017 ዓ.ም ጀምሮ ሪፖርት እንድታደርጉ ዩኒቨርሲቲው አሳስቧል፡፡

@tikvahuniversity
Tikvah-University
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ትናንት ጳጉሜን 1/2016 ዓ.ም ሊሰጠው የነበረውን የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ትምህርት ብሔራዊ የድኅረ ምረቃ ፕሮግራም መግቢያ ፈተና (NGAT) ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት መስጠት አለመቻሉን ገለፀ። ተፈታኞች ለደረሰባችሁ መጉላላት ይቅርታ የጠየቀው ዩኒቨርሲቲው፤ ፈተናውን መስከረም 3 እና 4/2017 ዓ.ም የሚሰጥ መሆኑን አሳውቋል። @tikvahuniversity
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ጳጉሜን 1/2016 ዓ.ም ሳይሰጥ የቀረውን የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ትምህርት ብሔራዊ የድኅረ ምረቃ ፕሮግራም መግቢያ ፈተና (NGAT) ነገ አርብ መስከረም 3/2017 ዓ.ም ከሰዓት 8፡00 ይሰጣል፡፡

በመሆኑም ተፈታኞች ከዚህ ቀደም በተመደባችሁበት የኮምፒውተር ላብራቶሪ ተገኝታችሁ ፈተናችሁን እንድትወስዱ ዩኒቨርሲቲው አሳስቧል።

@tikvahuniversity
Tikvah-University
#AAU #GAT አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በተቋሙ የድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (GAT) መስከረም 3/2017 ዓ.ም እንደሚሰጥ አሳውቋል፡፡  በተቋሙ የሚሰጠውን ፈተና ለመውሰድ የአመልካቾች ምዝገባ ከዛሬ ነሐሴ 30/2016 ዓ.ም እስከ መስከረም 1/2017 ዓ.ም ይከናወናል ተብሏል፡፡ @tikvahuniversity
#AAU #GAT Schedule.xls
203 KB
#AAU #GAT

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ነገ አርብ መስከረም 3/2017 ዓ.ም የሚሰጠውን የድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (GAT) መርሐግብር ይፋ አድርጓል፡፡

መስከረም 3/2017 ዓ.ም ጠዋት ከ2፡00-6፡00 ሰዓት ለሚሰጠው ፈተና የተፈታኞች ዝርዝር፣ የመፈተኛ ካምፓስ፣ የመፈተኛ ላብ እንዲሁም የኮምፒውተር ክፍል ከላይ ከተያያዘው ኤክሴል ይመልከቱ፡፡

@tikvahuniversity
Tikvah-University
#AAU #GAT አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በተቋሙ የድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (GAT) መስከረም 3/2017 ዓ.ም እንደሚሰጥ አሳውቋል፡፡  በተቋሙ የሚሰጠውን ፈተና ለመውሰድ የአመልካቾች ምዝገባ ከዛሬ ነሐሴ 30/2016 ዓ.ም እስከ መስከረም 1/2017 ዓ.ም ይከናወናል ተብሏል፡፡ @tikvahuniversity
#AAU #GAT Afternoon Schedule .xls
40.5 KB
#የቀጠለ

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ነገ አርብ መስከረም 3/2017 ዓ.ም የሚሰጠውን የድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (GAT) መርሐግብር ይፋ አድርጓል፡፡

መስከረም 3/2017 ዓ.ም ከሰዓት ከ7፡30-11፡00 ሰዓት ለሚሰጠው ፈተና የተፈታኞች ዝርዝር፣ የመፈተኛ ካምፓስ፣ የመፈተኛ ላብ እንዲሁም የኮምፒውተር ክፍል ከላይ ከተያያዘው ኤክሴል ይመልከቱ፡፡

@tikvahuniversity
#AAU #GAT

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (GAT) ዛሬ መስከረም 3/2017 ዓ.ም ይሰጣል፡፡

ፈተናው በጠዋት እና ከሰዓት ክፍለጊዜ እንደሚሰጥ ዩኒቨርሲቲው ያወጣው መርሐግብር ያሳያል።

ነገ መስከረም 4/2017 ዓ.ም ፈተናውን የሚወስዱ ተፈታኞች ዝርዝር እና የመፈተኛ ካምፓስ ዛሬ ይፋ እንደሚደረግ ተገልጿል።

ስማችሁ በዝርዝሩ ያልተካተተ አመልካቾች በቅርቡ ቀጣይ ዙር ፈተና እንደሚሰጥ ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

@tikvahuniversity
ለመስከረም 3 እና 4/2017 ዓ.ም የተዘዋወረው ሀገር አቀፍ የድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ከዛሬ ጀምሮ ለሁለት ቀናት በሰባት ማዕከላት ይሰጣል።

ይህ ፈተና የሚሰጠው ነሐሴ 30/2016 ዓ.ም በተሰጠው የNGAT ፈተና፣ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲን እንደ ፈተና ማዕከል መርጠው ለነበሩ ተፈታኞች መሆኑ ይታወቃል።

ፈተናው የሚሰጥባቸው ሰባት ተቋማት፦

1. በኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ፣
2. በኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ፣
3. በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ፣
4. በፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኢንስቲትዩት፣
5. በኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ፣
6. በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና
7. በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ሜዲካል ኮሌጅ፡፡

(የፈተናው ፕሮግራም ከላይ ተያይዟል፡፡)

@tikvahuniversity
#WallagaUniversity

ወለጋ ዩኒቨርሲቲ ለነባርና አዲስ ገቢ መደበኛ እና ተከታታይ መርሐግብር ተማሪዎቹ ጥሪ አድርጓል።

በዚህም የሁሉም የቅድመ ምረቃ እና የድኅረ ምረቃ ፕሮግራም የመደበኛ እና የተከታታይ መርሐግብር ነባር እንዲሁም አዲስ የሚመደቡ የመጀመሪያ ዓመት ተማሪዎች የምዝገባ ቀናት መስከረም 20 እና 21/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

ምዝገባው በዩኒቨርሲቲው ሦስቱም ካምፓሶች (ነቀምቴ፣ ጊምቢ እና ሻምቡ) የሚካሔድ ይሆናል።

ትምህርት የሚጀምረው መስከረም 22/2017 ዓ.ም መሆኑ ተገልጿል።

Note: ወደዩኒቨርሲቲው አዲስ የምትመደቡ የመጀመሪያ ዓመት ተማሪዎች የካምፓስ ምደባ በማስታወቂያ በቀጣይ ይገለፃል ተብሏል።

@tikvahuniversity
Tikvah-University
#AAU #GAT አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (GAT) ዛሬ መስከረም 3/2017 ዓ.ም ይሰጣል፡፡ ፈተናው በጠዋት እና ከሰዓት ክፍለጊዜ እንደሚሰጥ ዩኒቨርሲቲው ያወጣው መርሐግብር ያሳያል። ነገ መስከረም 4/2017 ዓ.ም ፈተናውን የሚወስዱ ተፈታኞች ዝርዝር እና የመፈተኛ ካምፓስ ዛሬ ይፋ እንደሚደረግ ተገልጿል። ስማችሁ በዝርዝሩ ያልተካተተ አመልካቾች በቅርቡ…
#AAU #GAT Sep 14 Morning Schedule.xls
136 KB
#AAU #GAT

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ነገ ቅዳሜ መስከረም 4/2017 ዓ.ም የሚሰጠውን የድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (GAT) መርሐግብር ይፋ አድርጓል፡፡

መስከረም 4/2017 ዓ.ም ጠዋት ከ2፡00-6፡00 ሰዓት ለሚሰጠው ፈተና የተፈታኞች ዝርዝር፣ የመፈተኛ ካምፓስ፣ የመፈተኛ ላብ እንዲሁም የኮምፒውተር ክፍል ከላይ ከተያያዘው ኤክሴል ይመልከቱ፡፡

@tikvahuniversity
M-PESA ጋር አዳዲስ ሽልማቶችን እያፈስን፣ ከነፃ ያልተናነሱ ቅናሾችን እያገኘን፣ ከ M-PESA ጋር በአዲሱ ዓመት እንጓዝ!

የ M-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያን በዚህ ሊንክ እናውርድ፦ https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle

የቴሌግራም ቻናላችንን እዚህ እንቀላቀል 👉 https://www.tg-me.com/Safaricom_Ethiopia_PLC

ስለ አገልግሎታችን ማንኛውንም ጥያቄ ወይም መረጃ በቴሌግራም ቻናላችን https://www.tg-me.com/Safaricom_Ethiopia_PLC 24/7 ማግኘት ይቻላል!

#MPESASafaricom #Furtheraheadtogether
#ETA

የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለሚሰጧቸው የትምህርት ፕሮግራሞች ዕውቅና መስጠት ሊጀምር መሆኑን የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን ገለፀ።

ባለሥልጣኑ ባለፉት ሁለት ዓመታት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን እንደገና መዝግቦ በጥራት እንዲሠሩ ለማድረግ የሚያግዝ መመሪያ እና አሰራር ሲያወጣ መቆየቱን ገልጿል፡፡

ከዚህ ቀደም በነበረው አሰራር ተቋማቱ በተመዘገቡበት የትምህርት ዘርፍ ማስተማር እንደሚችሉ ብቻ ታይቶ ፈቃድ ይሰጣቸው እንደነበረ የተነገረ ሲሆን፤ በአዲሱ የጥራት መመዘኛ መመሪያ መሠረት አስፈላጊውን የጥራት ደረጃ ማሟላታቸው እየተመዘነ ዳግም እንዲመዘገቡ ይደረጋል ተብሏል፡፡

በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ላይ የሚነሳውን የትምህርት ጥራት መጓደል ለማሻሻል ይረዳል የተባለው ይህ አሰራር፣ ከ2017 የትምህርት ዘመን አጋማሽ ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚሆን ተገልጿል፡፡

ምዝናው በሒደት በመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎችም ላይ ገቢራዊ ይደረጋል ተብሏል፡፡ #ShegerFM

@tikvahuniversity
#WoldiaUniversity

ወልድያ ዩኒቨርሲቲ ለሁሉም ነባር እና አዲስ ገቢ መደበኛ የቅድመ ምረቃ እና የድኅረ ምረቃ ተማሪዎቹ ጥሪ አድርጓል፡፡

በዚህም የሁሉም ነባር መደበኛ ተማሪዎች፣ በ2016 ዓ.ም በዩኒቨርሲቲው የሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርታችሁን ስትከታተሉ ቆይታችሁ የማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ ተማሪዎች እንዲሁም በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስዳችው የማለፊያ ውጤት አምጥታችሁ ወልድያ ዩኒቨርሲቲ የምትገቡ አዲስ ተማሪዎች የምዝገባ ቀናት መስከረም 27 እና 28/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡

የመማር ማስተማር ሥራ መስከረም 30/2017 ዓ.ም ይጀምራል ተብሏል፡፡

(የዩኒቨርሲቲው ሙሉ መልዕክት ከላይ ተያይዟል፡፡)

@tikvahuniversity
2024/10/01 04:17:20
Back to Top
HTML Embed Code: