Telegram Web Link
#JigjigaUniversity

ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ የመውጫ ፈተና የወሰዱ የተቋሙ ተማሪዎች ውጤታቸውን መመልከት እንደሚችሉ ገልጿል።

ዩኒቨርሲቲው ያስፈተናቸው ተማሪዎች ውጤት በተቋሙ ሬጅስትራር አማካኝነት ይፋ መደረጉንና ተማሪዎችም ውጤታቸውን ማየት እንደሚችሉ አሳውቋል።

@tikvahuniversity
#HawassaUniversity

ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የ2016 ዓ.ም ሃገር አቀፍ የመውጫ ፈተና ለመጀመሪያ ግዜ ከወሰዱ የቅድመ ምረቃ መደበኛ ዕጩ ተመራቂ ተማሪዎች መካከል ከ 89 በመቶ በላይ የሚሆኑት የማለፊያ ውጤት ማስመዝገባቸውን አሳውቋል።

@tikvahuniversity
#WerabeUniversity

ወራቤ ዩኒቨርሲቲ የ2016 ዓ.ም ሃገር አቀፍ የመውጫ ፈተና ለመጀመሪያ ግዜ ከወሰዱ የቅድመ ምረቃ መደበኛ ዕጩ ተመራቂ ተማሪዎች መካከል ከ 84 በመቶ በላይ የሚሆኑት የማለፊያ ውጤት ማስመዝገባቸውን አሳውቋል።

@tikvahuniversity
#MizanTepiUniversity

ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ለ2016 ዓ.ም ሃገር አቀፍ የመውጫ ፈተና በተቋሙ ከተቀመጡት ተማሪዎች ውስጥ 74.5 በመቶ ተፈታኞች የማለፊያ ውጤት ማምጣታቸውን አሳውቋል።

ዩኒቨርሲቲው በስምንት ኮሌጆች ለመውጫ ፈተና ካስቀመጣቸው 1438 ዕጩ ተመራቂዎች መካከል 1071 ተማሪዎች ማለፋቸውን ገልጿል።

@tikvahuniversity
#MattuUniversity

አዲሱ የመቱ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት አለሙ ዲሳሳ (ዶ/ር) የሥራ ርክክብ አድርገዋል፡፡

ተጠባባቂ ፕሬዝዳንቱ የትምህርት ሚኒስቴር ተወካዮች በተገኙበት ከዩኒቨርሲቲው ማኔጅመንትና ሴኔት አባላት ጋር የሥራ ርክክብና ትውውቅ አድርገዋል፡፡

በቆይታቸው መልካም የሥራ ባህልን በመፍጠር የዩኒቨርሲቲውን ራዕይ ለማሳካትና ወደ ራስገዝ ዩኒቨርሲቲነት የሚደረገውን ጉዞ ከመላው የተቋሙ ማኅበረሰብ ጋር በመሆን እንደሚያፋጥኑ ገልፀዋል።

@tikvahuniversity
ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ የክረምት መርሐግብር የመጀመሪያ ዲግሪ ነባር ተማሪዎች ምዝገባ ከሐምሌ 12-14/2016 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል፡፡

ትምህርት ሐምሌ 15/2016 ዓ.ም እንደሚጀምር ዩኒቨርሲቲው ገልጿል፡፡

የበጋ ኮርስ ተከታትላችሁ ነገር ግን ኦፊሺያል ትራንስክሪፕት ያላስላካችሁ እስከ ሐምሌ 12/2016 ዓ.ም ድረስ ማስላክ ይኖርባችኋል፡፡

ይህ የጥሪ ማስታወቂያ የ PGDT ተማሪዎችን ያካትታል ተብሏል፡፡ ተጨማሪ መረጃ ከላይ ተያይዟል፡፡

@tikvahuniversity
#2024_Commencement
#የቀጠለ

የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠኗቸውን ተማሪዎች ከነገ ሰኔ 23/2016 ዓ.ም ጀምሮ ያስመርቃሉ፡፡

ጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 29/2016 ዓ.ም
ወራቤ ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 27/2016 ዓ.ም

@tikvahuniversity
#InjibaraUniversity

እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የ2016 ዓ.ም አገር አቀፍ የመውጫ ፈተና ለመጀመሪያ ጊዜ ከወሰዱ የቅድመ ምረቃ መደበኛ ዕጩ ተመራቂዎች መካከል 83 በመቶ የሚሆኑት ተማሪዎች የማለፊያ ውጤት ማምጣታቸውን ገልጿል።

@tikvahuniversity
#BongaUniversity

ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በ2016 ዓ.ም የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና ከወሰዱ ዕጩ ተመራቂዎች መካከል 87.47 በመቶ ተማሪዎች የማለፊያ ውጤት ማምጣታቸውን አሳውቋል።

ዩኒቨርሲቲው ካስፈተናቸው 1,269 ተማሪዎች 1,110 (87.47 በመቶ) ተማሪዎች የማለፊያ ውጤት ማምጣታቸው ተገልጿል፡፡

@tikvahuniversity
#WolkiteUniversity

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ በመደበኛ መርሐግብር በ50 ፕሮግራሞች የመውጫ ፈተና ካስፈተናቸው ዕጩ ተመራቂዎች 85.07 በመቶ ተማሪዎች የማለፊያ ውጤት ማምጣታቸውን አሳውቋል።

በተከታታይ ፕሮግራም የተፈተኑ ተማሪዎች ጨምሮ የ2016 አማካይ ውጤቱ 82 በመቶ መሆኑን ገልጿል።

@tikvahuniversity
#WachemoUniversity

ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የ2016 ዓ.ም የቅድመ ምረቃ ፕሮግራም የመውጫ ፈተና ከወሰዱ ዕጩ ተመራቂዎቹ መካከል 86.13 በመቶ ተማሪዎች የማለፊያ ውጤት ማምጣታቸውን ገልጿል።

@tikvahuniversity
#DebreBerhanUniversity

በደብረ ብረሃን ዩኒቨርሲቲ የ2016 ዓ.ም አገር አቀፍ የመውጫ ፈተና ለመጀመሪያ ግዜ ከወሰዱ የቅድመ ምረቃ መደበኛ ፕሮግራም ዕጩ ተመራቂ ተማሪዎች መካከል 90.8 በመቶ ተማሪዎች የማለፊያ ውጤት ማስመዝገባቸውን ዩኒቨርሲው ገልጿል።

ዩኒቨርሲቲው በመደበኛ ፕሮግራም በ13 የትምህርት ክፍሎች የመውጫ ፈተና ያስፈተነ ሲሆን በአምስት ትምህርት ክፍሎች ሙሉ በሙሉ ያሳለፈ ሲሆን፤ በሌሎች ትምህርት ክፍሎች ደግሞ ከ80-95 በመቶ የማለፊያ ውጤት መመዝገቡን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

@tikvahuniversity
#DebreTaborUniversity

በደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ የ2016 ዓ.ም አገር አቀፍ የመውጫ ፈተና ለመጀመሪያ ግዜ ከወሰዱ የቅድመ ምረቃ መደበኛ ፕሮግራም ዕጩ ተመራቂ ተማሪዎች መካከል 92 በመቶ ተማሪዎች የማለፊያ ውጤት ማስመዝገባቸውን ዩኒቨርሲው ገልጿል።

@tikvahuniversity
#SalaleUniversity

በሰላሌ ዩኒቨርሲቲ የ2016 ዓ.ም አገር አቀፍ የመውጫ ፈተና ለመጀመሪያ ግዜ ከወሰዱ የቅድመ ምረቃ መደበኛ ፕሮግራም ዕጩ ተመራቂ ተማሪዎች መካከል 86.07 በመቶ ተማሪዎች የማለፊያ ውጤት ማስመዝገባቸውን ዩኒቨርሲው ገልጿል።

@tikvahuniversity
የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስና ሕክምና ኮሌጅ ሰሞኑን የተሰጠውን ሀገር አቀፍ የመውጫ ፈተና በሁለት የትምህርት መስኮች ያስፈተነ ሲሆን፤ ካስፈተናቸው ዕጩ ተመራቂዎች የአነስቴዢያ ተማሪዎች ሙሉ በሙሉ እንዲሁም የሕክምና ተማሪዎች 90 በመቶ ማለፋቸውን ገልጿል።

@tikvahuniversity
#MaddaWalabuUniversity

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያስተማራቸውን ከ1,400 በላይ ተማሪዎች አስመርቋል።

ዩኒቨርሲቲው በቅድመ እና ድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች ትምህርታቸውን የተከታተሉ 1,489 ተማሪዎችን አስመርቋል፡፡

@tikvahuniversity
2024/09/30 05:31:03
Back to Top
HTML Embed Code: