Telegram Web Link
#BongaUniversity

ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ለመጀመሪያ ጊዜ በቡና ሳይንስ የትምህርት መስክ ያሰለጠናቸው 34 ተማሪዎች አስመርቋል።

ዩኒቨርሲቲው በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን 1,250 ተማሪዎችን በዛሬው ዕለት አስመርቋል፡፡

ከአጠቃላይ ተመራቂዎቹ መካከል 142ቱ በሁለተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ መሆናቸው ተገልጿል።

ዩኒቨርሲቲው በቡና ሳይንስ በድኅረ ምረቃ መርሐግብርም 11 ተማሪዎችን እያሰለጠነ እንደሚገኝ የተቋሙ ፕሬዝዳንት ጴጥሮስ ወልደጊዮርጊስ (ዶ/ር) ተናግረዋል።

በቀጣይ በዘርፉ እስከ ዶክትሬት ዲግሪ ለማሰልጠን ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑንም ገልፀዋል።

@tikvahuniversity
#AksumUniversity

አክሱም ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን ከ1 ሺህ በላይ ተማሪዎች አስመርቋል።

በሰሜኑ ጦርነት ከፍተኛ ውድመት ያስተናገደው ዩኒቨርሲቲው፤ 1,050 ተማሪዎችን አስመርቋል።

በነሐሴ 2015 ዓ.ም ዳግም የማስተማር ሥራውን የጀመረው ዩኒቨርሲቲው፤ 14ኛ ዙር ሰልጣኝ ተማሪዎቹን በዛሬው ዕለት ማስመረቁ ታውቋል።

@tikvahuniversity
#SamaraUniversity

በሠመራ ዩኒቨርሲቲ የ2016 ዓ.ም አገር አቀፍ የመውጫ ፈተና ለመጀመሪያ ግዜ ከወሰዱ የቅድመ ምረቃ መደበኛ ፕሮግራም ዕጩ ተመራቂ ተማሪዎች መካከል 93 በመቶ ተማሪዎች የማለፊያ ውጤት ማስመዝገባቸውን ዩኒቨርሲቲው ገለፀ።

የዩኒቨርሲቲው ሁለት ኮሌጆች ያስፈተኗቸውን ተማሪዎች ሙሉ በሙሉ ማሳለፍ እንደቻሉ ተቋሙ ያደረሰን መረጃ ያሳያል።

@tikvahuniversity
#National_GAT

ብሔራዊ የድኅረ ምረቃ መግቢያ ፈተና (GAT) መቼ ይሰጣል?

የ2016 ዓ.ም የድኅረ ምረቃ መግቢያ ፈተና (GAT) መቼ እንደሚሰጥ በርካቶች ለቲክቫህ ጥያቄያቸውን አድርሰዋል።

በጉዳዩ ላይ አንድ የትምህርት ሚኒስቴር አመራርን የጠየቅን ሲሆን፤ 3ኛ ዙር አገር አቀፍ የድኅረ ምረቃ መግቢያ ፈተና (GAT) በሐምሌ ወር የመጨረሻ ሳምንት እንደሚሰጥ ለማወቅ ችለናል።

2ኛው ዙር የድህረ-ምረቃ ተማሪዎች የመግቢያ ፈተና በህዳር 2016 ዓ.ም መሰጠቱ ይታወሳል።

@tikvahuniversity
በወሎ ዩኒቨርሲቲ የፋርማሲ ትምህርት ቤት አገር አቀፍ የመውጫ ፈተናን የወሰዱ የ2016 ዕጩ ተመራቂዎች ሙሉ በሙሉ ማለፋቸውን አሳውቋል፡፡

የህክምና ትምህርት ቤቱ ደግሞ ካስፈተናቸው 97.5 በመቶ ተማሪዎች የማለፊያ ውጤት ማምጣታቸው ተገልጿል።

@tikvahuniversity
#2024_Commencement

የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠኗቸውን ተማሪዎች ማስመረቅ ጀምረዋል፡፡

ደብረታቦር ዩኒቨርሲቲ -ሰኔ 25/2016 ዓ.ም
ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 27/2016 ዓ.ም
ጂንካ ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 27/2016 ዓ.ም
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 27/2016 ዓ.ም
ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 27/2016 ዓ.ም

@tikvahuniversity
በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የአስራት ወልደየስ ጤና ሳይንስ ካምፓስ የ2016 ዕጩ ተመራቂዎች አገር አቀፍ የመውጫ ፈተናን ሙሉ በሙሉ ማለፋቸውን ካምፓሱ ገልጿል፡፡

@tikvahuniversity
#WolloUniversity

በወሎ ዩኒቨርሲቲ የ2016 ዓ.ም አገር አቀፍ የመውጫ ፈተና ለመጀመሪያ ግዜ ከወሰዱ የቅድመ ምረቃ መደበኛ ፕሮግራም ዕጩ ተመራቂ ተማሪዎች መካከል 83.27 በመቶ ተማሪዎች የማለፊያ ውጤት ማስመዝገባቸውን ዩኒቨርሲቲው ገለፀ።

የዩኒቨርሲቲው አምስት ትምህርት ክፍሎች ያስፈተኗቸውን ተማሪዎች ሙሉ በሙሉ ማሳለፍ እንደቻሉ ከተቋሙ የተገኘ መረጃ ያሳያል።

@tikvahuniversity
#TVTI_Exit_Exam

የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ለዕጩ ተመራቂ ተማሪዎቹ የመውጫ ፈተና እየሰጠ ነው፡፡

በዛሬው ዕለት እየተሰጠ የሚገኘውን የመውጫ ፈተና፣ በኢንስቲትዩቱ ለአራት ዓመታት ስልጠናቸውን ያጠናቀቁ እንዲሁም ፈተናውን በድጋሜ የሚወስዱ ሰልጣኞች መሆናቸው ተገልጿል፡፡

ትምህርት ሚኒስቴር ከኢንስቲትዩቱ ጋር በመተባበር እየተሰጠ በሚገኘው በዚህ ፈተና 2,135 ዕጩ ተመራቂዎች የመውጫ ፈተናውን እየወሰዱ ይገኛሉ።

በኢንስቲትዩቱ እንዲሁም በተቋሙ ሳተላይት ካምፓሶች አቅራቢያ የሚገኙ ዩኒቨርሲዎችን ጨምሮ በ11 የተለያዩ የፈተና ማዕከላት ፈተናው እየተሰጠ መሆኑን የኢንስቲትዩቱ ም/ዋ/ዳይሬክተር ሀፍቶም ገ/እግዚአብሄር ገልፀዋል፡፡

ከመውጫ ፈተናው አስቀድሞ ሰኔ 21/2016 ዓ.ም ለመስጠት ታቅዶ የነበረው #ሞዴል የመውጫ ፈተና አለመሰጠቱን ቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ሰምቷል፡፡

@tikvahuniversity
🎓🎓 ፕሮፌሰሮቹ አባት እና ልጅ

ፕሮፌሰር ባዬ ይማም (አባት) እና ፕሮፌሰር ቃለአብ ባዬ ይማም (ልጅ) በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሙያቸው እያገለገሉና ተተኪ ምሁራንን እያፈሩ የሚገኙ ፕሮፌሰሮች ናቸው።

ፕሮፌሰር ባዬ ይማም 44 ዓመታትን እንዲሁም ፕሮፌሰር ቃለዓብ ባዬ 15 ዓመታትን በመምህርነት፣ በተመራማሪነት እና በተለያዩ የሥራ ኃላፊነቶች ያገለገሉና እያገለገሉ የሚገኙ ምሁራን ናቸው።

ሁለቱም የፒኤችዲ ዲግሪያቸውን በሰሩ በ10ኛው ዓመት የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አገኝተዋል።

ፕሮፌሰር ቃለዓብ ባዬ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ዘንድሮ የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ከሰጣቸው ምሁራን መካከል አንዱ ናቸው። #AAU

@tikvahuniversity
ጅማ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን ከ 1,700 በላይ ተማሪዎችን ነገ ያስመርቃል።

ከተመራቂዎቹ መካከል 20 በሦስተኛ ዲግሪ እንዲሁም 253 በሁለተኛ ዲግሪ  ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው።

@tikvahuniversity
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን ከ3,500 በላይ ተማሪዎች ያስመርቃል።

በቅድመ እና ድኅረ ምረቃ መርሐግብር ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁት ተማሪዎቹ፤ ሰኔ 26/2016 ዓ.ም በሳውላ ካምፓስ እና ሰኔ 27/2016 ዓ.ም በአባያ ካምፓስ እንደሚመረቁ ተገልጿል፡፡

@tikvahuniversity
#WoldiaUniversity

በወልድያ ዩኒቨርሲቲ የ2016 ዓ.ም አገር አቀፍ የመውጫ ፈተና ለመጀመሪያ ግዜ ከወሰዱ የቅድመ ምረቃ መደበኛ ፕሮግራም ዕጩ ተመራቂ ተማሪዎች መካከል 93.1 በመቶ ተማሪዎች የማለፊያ ውጤት ማስመዝገባቸውን ዩኒቨርሲቲው ገለፀ።

ዩኒቨርሲቲው በ11 የትምህርት ክፍሎች ተማሪዎችን ያስፈተነ ሲሆን፤ አራት የትምህርት ክፍሎች ያስፈተኗቸውን ተማሪዎች ሙሉ በሙሉ ማሳለፍ እንደቻሉ ከተቋሙ የተገኘ መረጃ ያሳያል።

@tikvahuniversity
2024/09/30 03:23:27
Back to Top
HTML Embed Code: