Telegram Web Link
EXIT EXAM Schedule - Revised.xls
196.5 KB
#RevisedExitExamSchedule

ሀገር አቀፍ የመውጫ ፈተና ከአርብ ሰኔ 14/2016 ዓ.ም ጀምሮ እንደሚሰጥ ይታወቃል፡፡

የመውጫ ፈተና የተሻሻለ መርሐግብር ከላይ ተያይዟል።

@tikvahuniversity
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ይመልከቱ ፦ ይህ የመውጫ ፈተና የተመለከተ አጭር ቪድዮ የይለፍ ቃል (Password) እንዴት መቀየር እንደሚቻል ፣ ተፈታኞች በፈተና ወቅት መከተል ስላለባቸው ጉዳዮች ያሳያል።

#MoE

@TikvahUniversity
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተመራቂ ላልሆኑ የተቋሙ ተማሪዎች የመኝታ እና የምግብ አገልግሎት ከነገ ሰኔ 13/2016 ዓ.ም ጀምሮ እንደማይሰጥ አሳውቋል።

ለመጀመሪያ ዓመት ተማሪዎች ግን አገልግሎቶቹ መሰጠት እንደሚቀጥሉ ተገልጿል።

@tikvahuniversity
በአማራ ክልል ለመጀመሪያ ጊዜ የሚሰጠው የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ከነገ ሰኔ 13/ 2016 ዓ.ም ጀምሮ ለሁለት ቀናት ይሰጣል፡፡

170 ሺህ በላይ የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተናውን ለመውሰድ መመዝገባቸውን የክልሉ ትምህርት ቢሮ መግለፁ ይታወሳል።

በፀጥታ ችግር ምክንያት 99 ሺህ የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች ለፈተና እንደማይቀመጡ የቢሮው የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ጌታቸው ቢያዝን ለአሜሪካ ድምፅ ሰሞኑን መናገራቸው አይዘነጋም።

@tikvahuniversity
አምቦ ዩኒቨርሲቲ ዘንድሮ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ለሚወስዱ ተማሪዎች ገለፃ ሰጥቷል፡፡

ዩኒቨርሲቲው ከአምቦ ከተማ ትምህርት ቢሮ ጋር በመተባበር ገለፃውን የሰጠ ሲሆን፤ የተማሪዎቹን የስነ-ልቦና ዝግጁነት ለማጎልበት ያስቻለ እንደነበር ተገልጿል፡፡

በአምቦ ከተማ ከሚገኙ ሰባት የሁለተኛ ደረጃ፣ የመሰናዶ እና የአዳሪ ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች በመርሐግብሩ ተሳትፈዋል፡፡

@tikvahuniveristy
የአውሮፓ ህብረት ለ48 ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች የኢራስመስ+ ሁለተኛ ዲግሪ ስኮላርሺፕ መስጠቱን ገለፀ፡፡

ዕድሉ ተማሪዎቹ በ12 አገራት በሚገኙ ታዋቂ የአውሮጳ ዩኒቨርሲቲዎች የማስተርስ ዲግሪ ትምህርታቸውን ለሁለት ዓመታት (2024-2025) እንዲከታተሉ የሚያስችላቸው ነው፡፡

ኢትዮጵያ የአውሮጳ ህብረት ኢራስመስ+ ስኮላርሺፕ ፕሮግራም ተጠቃሚ ከሆኑ ቀዳሚ አገራት አንዷ ነች። የአውሮጳ ህብረት ከ2002 ዓ.ም ጀምሮ ከ600 ለሚበልጡ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች የኢራስመስ ሁለተኛ ዲግሪ ነፃ የትምህርት ዕድል ሰጥቷል፡፡

@tikvahuniveristy
መንገሻ አየነ (ዶ/ር) የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ሆነው ተመደቡ፡፡

መንገሻ አየነ (ዶ/ር) ከሰኔ 12/2016 ዓ.ም ጀምሮ የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ሆነው መመደባቸውን ሰኔ 10/2016 ዓ.ም በትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ተፈርሞ የወጣ የምደባ ደብዳቤ ያሳያል፡፡

የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት የነበሩት ፍሬው ተገኝ (ዶ/ር) የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሆነው መሾማቸውን ተከትሎ፤ ፕ/ር እሰይ ከበደ የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ሆነው በመወከል ሲሰሩ ቆይተዋል፡፡

አዲስ የተመደቡት የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት መንገሻ አየነ (ዶ/ር) ፤ ከመስከረም 2014 ዓ.ም ጀምሮ የወሎ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ሆነው ሲያገለግሉ ቆይተዋል፡፡

@tikvahuniversity
በአማራ ክልል የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና መሰጠት ጀምሯል።

ለመጀመሪያ ጊዜ እየተሰጠ የሚገኘውን ፈተና፤ ከ170 ሺህ በላይ ተፈታኞች በ4,355 ትምህርት ቤቶች እንደሚወስዱ ይጠበቃል።

በፀጥታ ችግር ምክንያት በክልሉ 99 ሺህ የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች ለሁለት ቀናት የሚሰጠውን ፈተና እንደማይወስዱ የክልሉ ትምህርት ቢሮ መግለፁ አይዘነጋም።

@tikvahuniversity
#ETA

የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በ2015 ዓ.ም እና በ2016 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ወስደው ያለፉ የመጀመሪያ ዲግሪ ተመራቂዎችን ዝርዝር እንዲልኩ የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን አሳስቧል።

ተቋማቱ ፈቃድ በተሰጣችሁ ትምህርት መስኮች፣ ትምህርት ደረጃ፣ መርሐግብር እና ካምፓስ ያስመረቋቸውንና ከዚህ በፊት ያልተላኩ የተመረቁ ተማሪዎች መረጃንም እንዲልኩ ተብሏል።

በዚህም መረጃዎቹን እስከ ሰኔ 30/2016 ዓ.ም በሶፍት እና በሀርድ ኮፒ እንድትልኩ ባለሥልጣኑ አሳስቧል።

@tikvahuniversity
#Update

የ2016 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች በሙሉ ከዛሬ ጀምሮ ለፈተና የሚጠቀሙበትን የይለፍ ቃል ከላይ ባሉት ሊንኮች በመግባት መቀየር ይችላሉ።

@tikvahuniversity
#MoH

የጤና ሚኒስቴር ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ፦
- በነርሲንግ፤
- ሜዲስን፤
- ጤና መኮንን፤
- አንስቴዥያ፤
- ፋርማሲ ፤
- ሜዲካል ላቦራቶሪ፤
- ሚድዋይፈሪ፤
- ዴንታል ሜዲስን፤
- ሜዲካል ራዲዮሎጂ፤
- ኢንቫይሮመንታል ሄልዝ፤
- ፔዲያትሪክ ኤንድ ቻይልድ ሄልዝ፤
- ሳይካትሪ ነርሲንግ፤
- ኢመርጀንሲ ኤንድ ክሪቲካል ኬር ነርሲንግ ፤
- ሰርጅካል ነርሲንግ፤
- ኦፕቶሜትሪ፤
- ፊዚዩቴራፒ እንዲሁም ሂውማን ኒውትሪሽን ሙያዎች በመጀመሪያ ዲግሪ ተመርቀው በትምህርት ሚኒስቴር በኩል ተመዝግበው የብቃት ምዘና ፈተና ለመውሰድ በመጠባበቅ ላይ የሚገኙ አዲስ እጩ ምሩቃን የጤና ባለሙያዎች ፈተናው ከትምህርት ሚኒስቴር የመውጫ ፈተና ጋር በጋራ ሰኔ 19/ 2016 ዓ.ም የሚሰጥ መሆኑን አሳውቋል።

ለዚህም ፈተና ተመዛኞች መዘጋጀት እና በፈተናው ወቅት በጠዋትም በከሰዓትም ክፍለ ጊዜ አቴንዳንስ ላይ በአግባቡ መፈረማቸውን ማረጋገጥ እንደሚጠበቅባቸው አሳስቧል።

በተጨማሪም ፦
° በሰርጅካል ነርሲንግ፤
° ኦፕቶሜትሪ፤
° ፊዚዩቴራፒ እንዲሁም ሂውማን ኒውትሪሽን ሙያዎች የሚመረቱ ባለሙያዎች ከሰኔ 1/2016 ዓ.ም ጀምሮ የሙያ ፈቃድ ለማግኘት የብቃት ምዘና ፈተና የሚጠበቅባቸው መሆኑን
አውቀው ከወዲሁ ከላይ በተጠቀሰው የፈትና ወቅት ዝግጅት አድርገው እንዲቀርቡ ማሳሰቢያ ሰጥቷል።

@tikvahuniversity
በትግራይ ክልል ለሦስት ተከታታይ ቀናት የተሰጠው የ8ኛ ክፍል ፈተና ተጠናቋል።

122 ሺህ በላይ የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ክልላዊ ፈተናውን ወስደዋል።

በክልሉ የ8ኛ ክፍል ፈተና በ1,129 ትምህርት ቤቶች መሰጠቱን የክልሉ የትምህርት ጥራት ማረጋገጫ ኤጀንሲ ዳይሬክተር ታደሰ ካህሳይ (ዶ/ር) ለኢዜአ ተናግረዋል፡፡ ፈተናው በሰላም መጠናቀቁን ኃላፊው ገልፀዋል።

@tikvahuniversity
#ExitExam

ሀገር አቀፍ የመውጫ ፈተና ዛሬ መሰጠት ጀምሯል፡፡

የ2016 ዓ.ም ዕጩ ተመራቂዎች እንዲሁም ለፈተናው በድጋሜ የሚቀመጡ ተማሪዎች ለሦስተኛ ጊዜ እየተሰጠ የሚገኘውን ፈተና ይወስዳሉ፡፡

ተፈታኞች የማኔጅመንት፣ የጂኦሎጂ እና የሕዝብ አስተዳደርና ዴቨሎፕመንት ማኔጅመንት ፈተናዎችን ዛሬ ሙሉ ቀን የሚወስዱ ይሆናል፡፡

ተሻሽሎ የወጣው የመውጫ ፈተና መርሐግብር፤ ሀገር አቀፍ ፈተናው እስከ ሰኔ 19/2016 ዓ.ም እንደሚሰጥ ያሳያል፡፡

ምስል፦ ደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ

@tikvahuniversity
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#MoE

በተለያየ ምክንያት ዛሬ የተሰጡትን የ Management, Business Administration, Business Management እና Business Management and Entrepreneurship ፈተና ያልወሰዳችሁ የመውጫ ፈተና ተፈታኞች ነገ ቅዳሜ ሰኔ 15 /2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 5፡30 ጀምሮ ፈተናው ስለሚሰጥ ወደየተመደባችሁበት ተቋም በመሔድ መፈተን የምትችሉ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።

ሁሉም ተፈታኞች User Name Password በመያዝ ፈተናው ከመጀመሩ ከ30 ደቂቃ በፊት የፈተና ጣቢያ መገኘት እንዳለባችሁ ተገልጿል።

@tikvahuniversity
2024/10/01 18:39:40
Back to Top
HTML Embed Code: