በአማራ ክልል ላለፉት ሁለት ቀናት ለመጀመሪያ ጊዜ የተሰጠው የ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ተጠናቋል፡፡
በክልሉ ሰኔ 13 እና 14/2016 ዓ.ም የተሰጠው የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና መጠናቀቁን የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ገልጿል።
የቢሮው ኃላፊ ሙሉነሽ ደሴ (ዶ/ር) ፈተናው በሰላም እንዲጠናቀቅ አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት ምስጋና አቅርበዋል፡፡
ከ170 ሺህ በላይ ተፈታኞች ፈተናውን ለመውሰድ መመዝገባቸውን ከዚህ ቀደም ያሳወቀው ቢሮው፤ ምን ያህሉ ፈተናው እንደወሰዱ አልገለፀም።
በክልሉ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች በፀጥታ ችግር ምክንያት ለፈተናው ምዝገባ አለማድረጋቸው ይታወቃል።
@tikvahuniversity
በክልሉ ሰኔ 13 እና 14/2016 ዓ.ም የተሰጠው የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና መጠናቀቁን የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ገልጿል።
የቢሮው ኃላፊ ሙሉነሽ ደሴ (ዶ/ር) ፈተናው በሰላም እንዲጠናቀቅ አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት ምስጋና አቅርበዋል፡፡
ከ170 ሺህ በላይ ተፈታኞች ፈተናውን ለመውሰድ መመዝገባቸውን ከዚህ ቀደም ያሳወቀው ቢሮው፤ ምን ያህሉ ፈተናው እንደወሰዱ አልገለፀም።
በክልሉ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች በፀጥታ ችግር ምክንያት ለፈተናው ምዝገባ አለማድረጋቸው ይታወቃል።
@tikvahuniversity
አዲስ የአጠቃላይ ትምህርት አዋጅ ወደ ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተመራ።
አዋጁ የአንደኛ እና መካከለኛ ደረጃ ትምህርትን በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች በፍትሐዊነት ለማዳረስ አስቻይ ሁኔታን የሚፈጥር እና የትምህርትን ጥራት፣ ተደራሽነት እና ፍትሀዊነት ለማረጋገጥ የሚያስችል መሆኑ ተገልጿል።
አዋጁ የትምህርት አግባብነትን፣ ስርዓተ ትምህርትን፣ የትምህርት ተቋማት አደረጃጀትን እና መምህራንን የሚመለከቱ ሙያዊ እና አስተዳደራዊ ጉዳዮችን የያዘ እንደሆነ ተጠቁሟል።
የትምህርት ተቋማት ደረጃ ማውጣትን እና ከመንግሥት ውጭ ባሉ የትምህርት ተቋማት ላይ የሚደረግ ቁጥጥርን በተመለከተ ድንጋጌዎችን አካቶ የቀረበ የሕግ ማዕቀፍ መሆኑ የሚኒስትሮች ም/ቤት የተገኘው መረጃ ያሳያል።
ምክር ቤቱ በቀረበው አዋጅ ላይ የተወያየ ሲሆን ግብዓቶችን በማከል ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መርቷል።
@tikvahuniversity
አዋጁ የአንደኛ እና መካከለኛ ደረጃ ትምህርትን በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች በፍትሐዊነት ለማዳረስ አስቻይ ሁኔታን የሚፈጥር እና የትምህርትን ጥራት፣ ተደራሽነት እና ፍትሀዊነት ለማረጋገጥ የሚያስችል መሆኑ ተገልጿል።
አዋጁ የትምህርት አግባብነትን፣ ስርዓተ ትምህርትን፣ የትምህርት ተቋማት አደረጃጀትን እና መምህራንን የሚመለከቱ ሙያዊ እና አስተዳደራዊ ጉዳዮችን የያዘ እንደሆነ ተጠቁሟል።
የትምህርት ተቋማት ደረጃ ማውጣትን እና ከመንግሥት ውጭ ባሉ የትምህርት ተቋማት ላይ የሚደረግ ቁጥጥርን በተመለከተ ድንጋጌዎችን አካቶ የቀረበ የሕግ ማዕቀፍ መሆኑ የሚኒስትሮች ም/ቤት የተገኘው መረጃ ያሳያል።
ምክር ቤቱ በቀረበው አዋጅ ላይ የተወያየ ሲሆን ግብዓቶችን በማከል ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መርቷል።
@tikvahuniversity
የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ 5ኛ አመት ተመራቂ ተማሪዎች " ከሁለት አመት በፊት Add አድርገን መጨረስ የምንችላቸውን ኮርሶች በዩኒቨርሲቲው ምክንያት ባለመውሰዳችን የመውጫ ፈተና ላይም መቀመጥም ሆነ የመመረቂያ አዳራሽ ውስጥ እንዳንገኝ ዩኒቨርሲቲው ወስኖብናል " በማለት ቅሬታቸውን ለቲክቫህ አቅርበዋል።
" ከሁለት አመት በፊት ከ በግዜው በኮቪድ ምክንያት በክረምት ትምህርታቸውን ሲከታተሉ ከነበሩ ተማሪዎች ጋር አድ አድርገን መጨረስ እንችል ነበር " ያሉት ተማሪዎቹ ዩኒቨርሲቲው ከመደበኛ ተማሪዎቹ ጋር መማር አትችሉም የሚል ህግ አውጥቶ እንዳይማሩ እንዳገዳቸው አሳውቀዋል።
በክረምት መማር አትችሉም የተባሉት ተማሪዎች በቀጣዩ አመት ነገሮች እንዲመቻች ይደረግላችሁኋል በማለት የዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ ምክትል ፕ/ት ቃል ገብተውላቸው እንደነበር አስረድተዋል።
ከዛ በኋላ መስከረም ላይ የዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ ምክትል ፕ/ት ሂዱና የትምህርት ክፍላችሁን አናግሩ በማለት መፍትሄ እንዳልሰጧቸው እና በድጋሚ የቀሩትን ኮርሶች በቀጣዩ ክረምት ትወስዳላችሁ ተብሎ ቃል ቢገባላቸውም ቃሉ እንዳልተጠበቀላቸው ተናግረዋል።
ይህንን ተከትሎም ኮርሶቹን ባለመጨረሳቸው ለመውጫ ፈተናም መቀመጥ እንዳይችሉ እንደተደረጉ የገለፁት ተማሪዎቹ በተጨማሪም የምረቃ ስነስርዓት ላይ እንዳይገኙ እንደተወሰነ ጠቁመዋል።
ተማሪዎች የመውጫ ፈተና መፈተን እንዳይችሉ ከመደረጋቸው ባሻገር "ቤተሰብ ይመረቃሉ ብሎ ቢጠብቀንም መመረቂያ አዳራሽ ውስጥ እንኳን እንዳንገባ ወስነውብናል" የሚል ቅሬታቸውን በማቅረብ ዩኒቨርሲቲው ይህንን እንዲያደርግላቸው ጠይቀዋል።
ቲክቫህ ጉዳዩን በተመለከተ ከሚመለከታቸው አካላት ምላሽ ለማግኘት ጥረት ያደርጋል።
@tikvahuniversity
" ከሁለት አመት በፊት ከ በግዜው በኮቪድ ምክንያት በክረምት ትምህርታቸውን ሲከታተሉ ከነበሩ ተማሪዎች ጋር አድ አድርገን መጨረስ እንችል ነበር " ያሉት ተማሪዎቹ ዩኒቨርሲቲው ከመደበኛ ተማሪዎቹ ጋር መማር አትችሉም የሚል ህግ አውጥቶ እንዳይማሩ እንዳገዳቸው አሳውቀዋል።
በክረምት መማር አትችሉም የተባሉት ተማሪዎች በቀጣዩ አመት ነገሮች እንዲመቻች ይደረግላችሁኋል በማለት የዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ ምክትል ፕ/ት ቃል ገብተውላቸው እንደነበር አስረድተዋል።
ከዛ በኋላ መስከረም ላይ የዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ ምክትል ፕ/ት ሂዱና የትምህርት ክፍላችሁን አናግሩ በማለት መፍትሄ እንዳልሰጧቸው እና በድጋሚ የቀሩትን ኮርሶች በቀጣዩ ክረምት ትወስዳላችሁ ተብሎ ቃል ቢገባላቸውም ቃሉ እንዳልተጠበቀላቸው ተናግረዋል።
ይህንን ተከትሎም ኮርሶቹን ባለመጨረሳቸው ለመውጫ ፈተናም መቀመጥ እንዳይችሉ እንደተደረጉ የገለፁት ተማሪዎቹ በተጨማሪም የምረቃ ስነስርዓት ላይ እንዳይገኙ እንደተወሰነ ጠቁመዋል።
ተማሪዎች የመውጫ ፈተና መፈተን እንዳይችሉ ከመደረጋቸው ባሻገር "ቤተሰብ ይመረቃሉ ብሎ ቢጠብቀንም መመረቂያ አዳራሽ ውስጥ እንኳን እንዳንገባ ወስነውብናል" የሚል ቅሬታቸውን በማቅረብ ዩኒቨርሲቲው ይህንን እንዲያደርግላቸው ጠይቀዋል።
ቲክቫህ ጉዳዩን በተመለከተ ከሚመለከታቸው አካላት ምላሽ ለማግኘት ጥረት ያደርጋል።
@tikvahuniversity
በአዲስ አበባ ለተከታታይ ሦስት ቀናት የተሰጠው የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ተጠናቋል፡፡
በአዲስ አበባ በሚገኙ 183 የመፈተኛ ጣቢያዎች ከሰኔ 12-14/2016 ዓ.ም ለተከታታይ ሦስት ቀናት የተሰጠው ፈተና በሰላም መጠናቀቁን የከተማ አስተዳደሩ ትምህርት ቢሮ አሳውቋል፡፡
ፈተናውን ለመውሰድ ከተመዘገቡ ተማሪዎች መካከል ከአቅም በላይ በሆነ ችግር ምክንያት ፈተናውን መውሰድ ካልቻሉ ጥቂት ተማሪዎች በስተቀር አብዛኞቹ ተማሪዎች መፈተናቸውን በቢሮው የፈተና ዝግጅትና አስተዳደር ዳይሬክተር ዲናኦል ጫላ ገልፀዋል፡፡
በአማርኛ ስርዓተ ትምህርት ለሚማሩ ተማሪዎች በአምስት እንዲሁም በአፋን ኦሮሞ ስርዓተ ትምህርት የሚማሩ ተማሪዎች ደግሞ በስድስት የትምህርት አይነቶች ፈተናውን መውሰዳቸውን ጠቁመዋል።
@tikvahuniversity
በአዲስ አበባ በሚገኙ 183 የመፈተኛ ጣቢያዎች ከሰኔ 12-14/2016 ዓ.ም ለተከታታይ ሦስት ቀናት የተሰጠው ፈተና በሰላም መጠናቀቁን የከተማ አስተዳደሩ ትምህርት ቢሮ አሳውቋል፡፡
ፈተናውን ለመውሰድ ከተመዘገቡ ተማሪዎች መካከል ከአቅም በላይ በሆነ ችግር ምክንያት ፈተናውን መውሰድ ካልቻሉ ጥቂት ተማሪዎች በስተቀር አብዛኞቹ ተማሪዎች መፈተናቸውን በቢሮው የፈተና ዝግጅትና አስተዳደር ዳይሬክተር ዲናኦል ጫላ ገልፀዋል፡፡
በአማርኛ ስርዓተ ትምህርት ለሚማሩ ተማሪዎች በአምስት እንዲሁም በአፋን ኦሮሞ ስርዓተ ትምህርት የሚማሩ ተማሪዎች ደግሞ በስድስት የትምህርት አይነቶች ፈተናውን መውሰዳቸውን ጠቁመዋል።
@tikvahuniversity
#ማስታወሻ
ትናንት የተሰጡትን የ Management, Business Administration, Business Management እና Business Management and Entrepreneurship የመውጫ ፈተና በተለያየ ምክንያት ያልወሰዳችሁ ተፈታኞች ዛሬ ቅዳሜ ሰኔ 15 /2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 5፡30 ጀምሮ ፈተናው ስለሚሰጥ ወደየተመደባችሁበት ተቋም በመሔድ መፈተን የምትችሉ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል።
ተፈታኞች User Name Password በመያዝ ፈተናው ከመጀመሩ ከ30 ደቂቃ በፊት የፈተና ጣቢያ መገኘት አለባችሁ ተብሏል።
@tikvahuniversity
ትናንት የተሰጡትን የ Management, Business Administration, Business Management እና Business Management and Entrepreneurship የመውጫ ፈተና በተለያየ ምክንያት ያልወሰዳችሁ ተፈታኞች ዛሬ ቅዳሜ ሰኔ 15 /2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 5፡30 ጀምሮ ፈተናው ስለሚሰጥ ወደየተመደባችሁበት ተቋም በመሔድ መፈተን የምትችሉ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል።
ተፈታኞች User Name Password በመያዝ ፈተናው ከመጀመሩ ከ30 ደቂቃ በፊት የፈተና ጣቢያ መገኘት አለባችሁ ተብሏል።
@tikvahuniversity
#ጥቆማ
የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የፈረንሳይኛ ቋንቋ ማሰልጠኛ ማዕከል የመጀመሪያ ዙር 60 ሰልጣኞችን መቀበል ጀምሯል።
ምዝገባው የሚያበቃው፦
ሰኔ 19/2016 ዓ.ም
የምዝገባ ቦታ፦
CSSH ህንጻ 1ኛ ፍሉር R-10
ለተጨማሪ መረጃ፦
0977945129 / 0916159720
Email: [email protected]
@tikvahuniversity
የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የፈረንሳይኛ ቋንቋ ማሰልጠኛ ማዕከል የመጀመሪያ ዙር 60 ሰልጣኞችን መቀበል ጀምሯል።
ምዝገባው የሚያበቃው፦
ሰኔ 19/2016 ዓ.ም
የምዝገባ ቦታ፦
CSSH ህንጻ 1ኛ ፍሉር R-10
ለተጨማሪ መረጃ፦
0977945129 / 0916159720
Email: [email protected]
@tikvahuniversity
#ExitExam
ሀገር አቀፍ የመውጫ ፈተና የሁለተኛ ቀን ፈተናዎች እየተሰጡ ነው፡፡
የ2016 ዓ.ም ዕጩ ተመራቂዎች እና በድጋሜ ተፈታኞች ለሦስተኛ ጊዜ እየተሰጠ የሚገኘውን ፈተና እየወሰዱ ይገኛሉ፡፡
የአካውንቲንግ እና ሕግ ፈተናዎችን ጨምሮ የሰባት ትምህርት አይነት ፈተናዎች ዛሬ ሙሉ ቀን እየተሰጡ ነው፡፡ ሀገር አቀፍ የመውጫ ፈተናው እስከ ሰኔ 19/2016 ዓ.ም ይሰጣል፡፡
ምስል፦ ቦረና፣ አዲግራት እና ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲዎች
@tikvahuniversity
ሀገር አቀፍ የመውጫ ፈተና የሁለተኛ ቀን ፈተናዎች እየተሰጡ ነው፡፡
የ2016 ዓ.ም ዕጩ ተመራቂዎች እና በድጋሜ ተፈታኞች ለሦስተኛ ጊዜ እየተሰጠ የሚገኘውን ፈተና እየወሰዱ ይገኛሉ፡፡
የአካውንቲንግ እና ሕግ ፈተናዎችን ጨምሮ የሰባት ትምህርት አይነት ፈተናዎች ዛሬ ሙሉ ቀን እየተሰጡ ነው፡፡ ሀገር አቀፍ የመውጫ ፈተናው እስከ ሰኔ 19/2016 ዓ.ም ይሰጣል፡፡
ምስል፦ ቦረና፣ አዲግራት እና ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲዎች
@tikvahuniversity
በመቐለ ዩኒቨርሲቲ የሚያስተምሩ የተወሰኑ መምህራን “ቤት ተከራይቶ መኖር እንደከበዳቸው” ለተቋሙ ማመልከታቸውን ተከትሎ፤ በተማሪዎች ማደሪያ ዶርም “በጊዜያዊነት” እንዲኖሩ ተፈቅዶላቸው እየኖሩ መሆኑ ተሠማ።
የዩኒቨርስቲው መምህራን በትግራይ ክልል በነበረው ጦርነት ምክንያት የ17 ወር ደመወዝ ያልተከፈላቸው መሆኑ፤ በአስር ሺህዎች የሚቆጠር ውዝፍ የቤት ኪራይ እንዲከማችባችው አድርጓል።
ለመምህራን ሳይከፈል የቀረው የ17 ወር ደመወዝ ዘንድሮ “ይከፈላል ተብሎ እየተጠበቀ” መሆኑን ጨምረው ገልጸዋል። ውዝፍ ክፍያው ከተፈጸመ በኋላ ወደ ተማሪዎች መኖሪያ እንዲገቡ የተደረጉት መምህራን፤ ዶርሞቹን ሊለቁ እንደሚችሉ ተገልጿል።
የኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዝርዝር ዘገባን ያንብቡ፦
https://ethiopiainsider.com/2024/13369/
@tikvahuniversity
የዩኒቨርስቲው መምህራን በትግራይ ክልል በነበረው ጦርነት ምክንያት የ17 ወር ደመወዝ ያልተከፈላቸው መሆኑ፤ በአስር ሺህዎች የሚቆጠር ውዝፍ የቤት ኪራይ እንዲከማችባችው አድርጓል።
ለመምህራን ሳይከፈል የቀረው የ17 ወር ደመወዝ ዘንድሮ “ይከፈላል ተብሎ እየተጠበቀ” መሆኑን ጨምረው ገልጸዋል። ውዝፍ ክፍያው ከተፈጸመ በኋላ ወደ ተማሪዎች መኖሪያ እንዲገቡ የተደረጉት መምህራን፤ ዶርሞቹን ሊለቁ እንደሚችሉ ተገልጿል።
የኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዝርዝር ዘገባን ያንብቡ፦
https://ethiopiainsider.com/2024/13369/
@tikvahuniversity
#ጥቆማ
ለ Fulbright African Research Scholars Program (FARSP) ያመልክቱ!
የዩኒቨርሲቲ መምህር ነዎት? ምርምርዎትን በዩናይትድ ስቴትስ ማከናወን ይፈልጋሉ?
ዓመታዊው የፉልብራይት አፍሪካ የምርምር ምሁራን ፕሮግራም (FARSP) 2025/26 ለአመልካቾች ክፍት ነው፡፡
የማመልከቻ ጊዜው የሚያበቃው 👇
ሐምሌ 8/2016 ዓ.ም
ለማመልከት 👇
https://apply.iie.org/fvsp2025
ለማንኛውም አይነት ጥያቄ እንዲሁም ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት 👇 [email protected]
(ተጨማሪ መረጃ ከላይ ተያይዟል።)
@tikvahuniversity
ለ Fulbright African Research Scholars Program (FARSP) ያመልክቱ!
የዩኒቨርሲቲ መምህር ነዎት? ምርምርዎትን በዩናይትድ ስቴትስ ማከናወን ይፈልጋሉ?
ዓመታዊው የፉልብራይት አፍሪካ የምርምር ምሁራን ፕሮግራም (FARSP) 2025/26 ለአመልካቾች ክፍት ነው፡፡
የማመልከቻ ጊዜው የሚያበቃው 👇
ሐምሌ 8/2016 ዓ.ም
ለማመልከት 👇
https://apply.iie.org/fvsp2025
ለማንኛውም አይነት ጥያቄ እንዲሁም ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት 👇 [email protected]
(ተጨማሪ መረጃ ከላይ ተያይዟል።)
@tikvahuniversity
Tikvah-University
Photo
#ETQRA
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ለ2017 የትምህርት ዘመን በከተማዋ ምዝገባ ማከናወን የተፈቀደላቸው አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን ዝርዝር ይፋ አድርጓል።
በአዲስ አበባ ለ2017 የትምህርት ዘመን የተቀመጡ መስፈርቶችን አሟልተው ምዝገባ ማከናወን የተፈቀደላቸው 125 የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መሆናቸውን ባለስልጣኑ ገልጿል።
(የትምህርት ቤቶቹ ዝርዝር ከላይ ተያይዟል።)
@tikvahuniversity
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ለ2017 የትምህርት ዘመን በከተማዋ ምዝገባ ማከናወን የተፈቀደላቸው አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን ዝርዝር ይፋ አድርጓል።
በአዲስ አበባ ለ2017 የትምህርት ዘመን የተቀመጡ መስፈርቶችን አሟልተው ምዝገባ ማከናወን የተፈቀደላቸው 125 የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መሆናቸውን ባለስልጣኑ ገልጿል።
(የትምህርት ቤቶቹ ዝርዝር ከላይ ተያይዟል።)
@tikvahuniversity
#ጥቆማ
#EthiopianAviationUniversity
የኢትዮጵያ አቪዬሽን ዩኒቨርሲቲ በማርኬቲንግ ዘርፍ የአቪዬሺን መስክ ስልጠና ለግል አመልካቾች ይሰጣል።
ለግል አመልካቾች የሚሰጡ ስልጠናዎች፦
➧ የኤርፖርት መንገደኞች አገልግሎት የኤጀንትነት ስልጠና
➧ የአየር መንገድ የስልክ ማዕከልና የቲኬት አገልግሎት የኤጀንትነት ስልጠና
➧ የካርጎ አገልግሎት የኤጀንትነት ስልጠና
ስልጠናዎቹ ዕውቅና ያላቸው፣ እጅግ ዘመናዊ በሆነ የተግባር መለማመጃ እና ልምድ ባላቸው የዘርፉ ባለሙያዎች የሚሰጡ መሆኑ ተገልጿል።
ለማመልከት 👇
https://eau.edu.et/admission/applyonline
ለበለጠ መረጃ 👇
- [email protected]
- [email protected]
- ስልክ ቁ. 0115174600 / 0115178598
@tikvahuniversity
#EthiopianAviationUniversity
የኢትዮጵያ አቪዬሽን ዩኒቨርሲቲ በማርኬቲንግ ዘርፍ የአቪዬሺን መስክ ስልጠና ለግል አመልካቾች ይሰጣል።
ለግል አመልካቾች የሚሰጡ ስልጠናዎች፦
➧ የኤርፖርት መንገደኞች አገልግሎት የኤጀንትነት ስልጠና
➧ የአየር መንገድ የስልክ ማዕከልና የቲኬት አገልግሎት የኤጀንትነት ስልጠና
➧ የካርጎ አገልግሎት የኤጀንትነት ስልጠና
ስልጠናዎቹ ዕውቅና ያላቸው፣ እጅግ ዘመናዊ በሆነ የተግባር መለማመጃ እና ልምድ ባላቸው የዘርፉ ባለሙያዎች የሚሰጡ መሆኑ ተገልጿል።
ለማመልከት 👇
https://eau.edu.et/admission/applyonline
ለበለጠ መረጃ 👇
- [email protected]
- [email protected]
- ስልክ ቁ. 0115174600 / 0115178598
@tikvahuniversity
በሀረሪ ክልል የ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና መሰጠት ጀምሯል።
ከ76 ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ 5,350 ተማሪዎች ለፈተናው መቀመጣቸውን የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ጌቱ ነገዎ ገልፀዋል።
ፈተናው በ29 የፈተና ጣቢያዎች ዛሬን ጨምሮ ለሦስት ተከታታይ ቀናት እንደሚሰጥ ከክልሉ ትምህርት ቢሮ የተገኘ መረጃ ያሳያል።
@tikvahuniversity
ከ76 ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ 5,350 ተማሪዎች ለፈተናው መቀመጣቸውን የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ጌቱ ነገዎ ገልፀዋል።
ፈተናው በ29 የፈተና ጣቢያዎች ዛሬን ጨምሮ ለሦስት ተከታታይ ቀናት እንደሚሰጥ ከክልሉ ትምህርት ቢሮ የተገኘ መረጃ ያሳያል።
@tikvahuniversity