Telegram Web Link
🎯 ትክክለኞቹን የሳፋሪኮም ገጾች እንከተል! ከሳፋሪኮም ጋር አንድ ወደፊት! ⚡️

🔗 የM-PESAን ሳፋሪኮም መተግበሪያ በዚህ ሊንክ እናውርድ፦ https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle

የቴሌግራም ቻናላችንን እዚህ እንቀላቀል 👉 https://www.tg-me.com/Safaricom_Ethiopia_PLC

የፌስቡክ ገጻችንን እዚህ እንቀላቀል 👉 https://www.facebook.com/SafaricomET

የኢንስታግራም አካውንታችንን እዚህ እንቀላቀል 👉 https://www.instagram.com/safaricomet/

ስለ አገልግሎታችን ማንኛውንም ጥያቄ ወይም መረጃ በቴሌግራም ቻናላችን https://www.tg-me.com/Safaricom_Ethiopia_PLC 24/7 ማግኘት ይቻላል!

#SafaricomEthiopia
#MPESASafaricom #FurtherAheadTogether
ተመዝግበዋል?

አምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያውያንን ለሚያሳትፈው የኮዲንግ ስልጠና የኦንላይን ምዝገባ ተጀምሯል።

ከክፍያ ነፃ የሚሰጠውን ስልጠና ለመከታተል ይመዝገቡ 👇
www.ethiocoders.et/

(ምዝገባውን ለማድረግ መፈፀም ያለበዎት steps ከላይ በምስሎቹ ተያይዟል፡፡)

@tikvahuniversity
ወልድያ ዩኒቨርሲቲ በ2016 ዓ.ም የክረምት አዲስ የ "PGDT" ሰልጣኖች የማመልከቻ ጊዜን እስከ ሐምሌ 25/2016 ዓ.ም አራዝሟል፡፡

በሌላ በኩል የዩኒቨርሲቲው የማታ መርሐግብር ነባር የመጀመሪያ እና የሁለተኛ ዲግሪ ተማሪዎች የክረምት ሴሚስተር ምዝገባ ከሐምሌ 24-26/2016 ዓ.ም መሆኑ ተገልጿል፡፡ ትምህርት ሐምሌ 27/2016 ዓ.ም ይጀምራል ተብሏል፡፡

@tikvahuniversity
Tikvah-University
የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት የ2016 ዓ.ም ዕጩ ተመራቂዎች እንዲሁም ዳግም ተፈታኞች ሰኔ 24/2016 ዓ.ም የመውጫ ፈተና መውሰዳቸው ይታወቃል። በርካታ ተፈታኞች የመውጫ ፈተና ውጤት ሳይገለፅ ዘገየ ሲሉ ቅሬታቸውን ለቲክቫህ አድርሰዋል። በጉዳዩ ላይ የኢንስቲትዩቱን የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ጠይቀናል። "ኢንስቲትዩቱ ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመውጫ ፈተናው ላይ እየተወያየ መሆኑን"…
የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት የ2016 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ውጤት ይፋ ያደርጋል።

የኢንስቲትዩቱ የ2016 ዓ.ም ዕጩ ተመራቂዎች እንዲሁም ዳግም ተፈታኞች የዛሬ ወር የመውጫ ፈተና መውሰዳቸው ይታወቃል።

"ኢንስቲትዩቱ ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመውጫ ፈተናው ላይ እየተወያየ መሆኑንና ውይይቱ ሲጠናቀቅ የተፈታኞች ውጤት እንደሚገለፅ" ነግረናችሁ ነበር።

ተቋሙ ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር የነበረው ውይይት ትናንት ተጠናቋል። በመሆኑም የተፈታኞች ውጤት ዛሬ ወይም ነገ ይፋ እንደሚደረግ ከኢንስቲትዩቱ የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ሰምተናል።

@tikvahuniversity
#MoE

የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለሚያስመርቋቸው ተማሪዎች የሚሰጡት ዲግሪ የህትመት ሥራ በመንግሥት ሊከናወን ነው፡፡

የዲግሪ ህትመት ሥራው በሀገር ውስጥ እነደሚከናወንና አሰራሩም ከቀጣይ ዓመት ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚሆን የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ተናግረዋል፡፡

ሚኒስትሩ ይህን ያሉት የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን ትናንት ባዘጋጀው የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ዳግም ምዝገባ የውይይት መድረክ ላይ ነው፡፡

"ከሚቀጥለው ዓመት ጀምሮ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ዲግሪ በማሳተም ለተማሪዎቻቸው መስጠት አይችሉም" ያሉት ሚኒስትሩ፤ ዲግሪ የሚታተመው በትምህርት ሚኒስቴር በኩል እንደሚሆንና ለዚህም ተቋማቱ ክፍያ ለሚኒስቴሩ እንደሚፈፅሙ ገልፀዋል፡፡

ትምህርት ሚኒስቴር የተማሪዎቹን ዲግሪ የሚያትመው ተቋማቱ በሚልኩት መረጃ እና የተማሪዎቹ የሀገር አቀፍ የመውጫ ፈተና ውጤትን መሰረት በማድረግ እንደሚሆንም ጠቁመዋል፡፡

አሰራሩ ተግባራዊ ሲደረግ በሀገሪቱ የሚታየውን የሐሰተኛ ዲግሪ ህትመት ለማስቆም እንደሚያስችል ሚኒስትሩ አስረድተዋል፡፡

መንግሥት የ Security Printing ሥራ በሀገር ውስጥ በ2017 ዓ.ም መጨረሻ አካባቢ እንደሚጀምር ሚኒስትሩ ተናግረዋል፡፡

@tikvahUniversity
የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ስቴም (STEM) ማዕከል ለ2016 ዓ.ም ከ200 በላይ የክረምት ሰልጣኝ ተማሪዎች ቅበላ አድርጓል።

ሰልጣኝ ተማሪዎቹ በጉራጌ ዞን ከሚገኙ ትምህርት ቤቶች የተውጣጡና ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ከ7-12ኛ ክፍል ተማሪዎች መሆናቸው ተገልጿል፡፡ በተጨማሪም የፈጠራ ፕሮጀክቶች ያሏቸው 30 ተማሪዎችም ወደ ማዕከሉ ገብተዋል።

ዩኒቨርሲቲው በድምሩ 236 ሰልጣኝ ተማሪዎችን ለአንድ ወር ያህል የምግብ እና የመኝታ አገልግሎት በማቅረብ እንደሚያሰለጥን ተገልጿል፡፡

@tikvahuniversity
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በቅርቡ የመሬት መንሸራተት አደጋ በደረሰበት በጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ጥናት ማድረግ ጀምሯል።

ዩኒቨርሲቲው ስምንት አባላት ያሉት የተመራማሪዎች ቡድን ወደስፍራው በመላክ የአደጋውን መንስኤና ቀጣይ የአደጋ ስጋቶችን ለማወቅ ጥናት እየተደረገ መሆኑ ገልጿል።

ቡድኑ ፈጣንና ሳይንሳዊ ቅኝትና ጥናት በማድረግ፤ በቀጣይ መሰል አደጋዎች እንዳይከሰቱ የአደጋ ስጋት ቦታዎችን የመለየት ሥራ ያከናውናል ተብሏል።

"ከዚህ በኋላ በአካባቢው መሰል አደጋ ሊኖር ይችላል ወይ?" ለሚለው ጥያቄ ምላሽ ማግኘት እንዲሁም "የአካባቢውን ነዋሪ እዛው ለማቆየት ወይም ወደሌላ ቦታ ለማዛወር' የሚረዱ ሳይንሳዊ ምክረ ሃሳቦችን ማቅረብ የጥናት ቡድኑ ትኩረት መሆኑ ተገልጿል።

አደጋው ያስከተለውን ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ስነ-ልቦናዊ ችግሮች መለየትና መፍትሔዎችን ማመላከት ሌላኛው የጥናቱ ዓላማ መሆኑን ተጠቁሟል።

ከጂኦሎጂ፣ ከሲቪልና ከጂኦሎጂካል ምኅንድስና፣ ከጂኦግራፊ፣ ከግብርና እና ከሌሎች ዘርፎች የተወጣጡ ተመራማሪዎች፤ የጂአይኤስና ሪሞት ሴንሲንግ መሳሪያዎች በመጠቀም ጥናት እያደረጉ መሆኑ ተመልክቷል።

የቡድኑ የጥናት ውጤት በቅርቡ የሚመለከታቸው አካላት በተገኙበት ይፋ ይሆናል ተብሏል፡፡

@tikvahuniversity
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከ Dereja.com ፣ ማስተር ካርድ ፋውንዴሽን እና ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ለዕጩ ምሩቃን የሥራ አውደ ርዕይ አካሒዷል።

አውደ ርዕዩ ተመራቂ ተማሪዎችን ከቀጣሪ ተቋማት እና ባለሃብቶች ጋር ለማገናኘት ያለመ ነበር ተብሏል።

@tikvahuniversity
Tikvah-University
#MoE የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለሚያስመርቋቸው ተማሪዎች የሚሰጡት ዲግሪ የህትመት ሥራ በመንግሥት ሊከናወን ነው፡፡ የዲግሪ ህትመት ሥራው በሀገር ውስጥ እነደሚከናወንና አሰራሩም ከቀጣይ ዓመት ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚሆን የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ተናግረዋል፡፡ ሚኒስትሩ ይህን ያሉት የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን ትናንት ባዘጋጀው የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ዳግም ምዝገባ…
ትምህርት ሚኒስቴር የመንግሥት እንዲሁም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን የዲግሪ እና የዲፕሎማ ስርተፊኬቶች ከመጪው ዓመት ጀምሮ በአገር ውስጥ ለማሳትም ዝግጅት አጠናቋል።

ይህም በትምህርት ዘርፍ በአገር አቀፍ ደረጃ የሚታየውን የሐሰተኛ ትምህርት ሰነድ ህትመት ለማስቀረት እንደሚያስችል የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ተናግረዋል፡፡

ሁሉም የትምህርት ተቋማት የተመራቂ ተማሪዎቻቸውን ዝርዝር መረጃ ለትምህርት ሚኒስቴር በመላክና ለዚህም ክፍያ በመፈፀም ለተማሪዎቻቸው የዲግሪ እና የዲፕሎማ ሰርተፊኬቶች የሚያገኙበት አሰራር ከመጪው ዓመት ጀምሮ ተግባራዊ ይደረጋል ብለዋል።

@tikvahuniversity
የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመማር ማስተማር ሥራቸውን ለማስቀጠል የሚያስችላቸውን ፈቃድ ለማግኘት እስከ ታኅሳስ 30/2017 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ እንደገና ምዝገባ ማከናወን እንዳለባቸው የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን አሳውቋል።

ዳግም ምዝገባው ያስፈለገው እንደ  ሀገር ወጥነት ያለው የፈቃድ አሰጣጥ ስርዓት ተግባራዊ ለማድረግ መሆኑን ባለሥልጣኑ ገልጿል።

በዚህም በመንግሥት እና በግል ተቋማት መካከል ያለው የፈቃድ አሰጣጥ የአሰራር ስርዓት ልዩነት እንደሚቀር የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ሽፈራው ሽጉጤ ተናግረዋል።

@tikvahuniversity
Tikvah-University
በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የህክምናና ጤና ሳይንስ ተማሪዎች ወደትምህርታቸው ተመልሰዋል።

ተማሪዎቹ ለሰባት ወራት ከትምህርት ገበታቸው መራቃቸውን በመግለፅ ቅሬታቸውን ለቲክቫህ አቅርበው ነበር፡፡

የዩኒቨርሲቲው የህዝብና ኮሚዩኒኬሽን ግንኙነት ዳይሬክቶሬት "የክረምት ተማሪዎች እና ልዩ ሰልጣኝ መምህራን ከገቡ በኋላ ለጤና ተማሪዎቹ ጥሪ እንደሚደረግ" ለቲክቫህ ማሳወቁ ይታወሳል፡፡

በዚህም የህክምናና ጤና ሳይንስ ተማሪዎቹ ከሰኞ ሐምሌ 22/2016 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ዩኒቨርሲቲው እየገቡ እንደሚገኙ ቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ አረጋግጧል፡፡

@tikvahuniversity
#National_GAT

የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ምዝገባ የሚካሔደው ከሐምሌ 24/2016 ዓ.ም እስከ ነሐሴ 05/2016 ዓ.ም መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።

በመሆኑም በ2017 የትምህርት ዘመን በድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች ለመማር ፍላጎት ያላችሁ አመልካቾች የመመዝገቢያው ቅጽ ላይ የተዘረዘሩት መስፈርቶችን በሟሟላት በተጠቀሰው ጊዜ መመዝገብ ትችላላችሁ ተብሏል።

ለመመዝገብ 👇
https://NGAT.ethernet.edu.et

@tikvahuniversity
2024/10/02 10:31:47
Back to Top
HTML Embed Code: