Telegram Web Link
ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ነባር የመጀመርያ ዲግሪ ተማሪዎች የ2016 ዓ.ም የክረምት ትምህርት ምዝገባ ሐምሌ 22 እና 23/2016 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል፡፡

የምዝገባ ቦታ፦ በዩኒቨርሲቲው ዋና ሬጅስትራር ህንጻ ቁ. 121

በ2016 ዓ.ም በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ እንድትሰለጥኑ የተመደባችሁ አዲስ ሰልጣኝ መምህራን እና የትምህርት ቤት አመራሮች መግቢያ ሐምሌ 22/2016 ዓ.ም መሆኑ ተገልጿል፡፡

በዩኒቨርሲቲው የጤና ኢኒስቲትዩት እና እንስሳት ህክምና ሳይንስ ተማሪዎች መግቢያ ሐምሌ 22/2016 ዓ.ም መሆኑ ተመላክቷል፡፡

ከላይ ጥሪ የተደረገላችሁ ተማሪዎች በሙሉ ወደ ተቋሙ ስትሔዱ አንሶላ፣ ብርድ ልብስ እና የትራስ ልብስ መያዝ ይኖርባችኋል፡፡

(ተጨማሪ መረጃ ከላይ ተያይዟል፡፡)

@tikvahuniversity
*400,000 ብር??* በዛ ላይ ደግሞ አስቡት የእናንተ ሙዚቃ በመላው ኢትዮጵያ ሲደመጥ ... እናንተ ችሎታው ይኑራችሁ የቀረውን በእኛ ጣሉት! አሁኑኑ የአንድ ደቂቃ ቪዲዮአችንን እንላክ!

የዲጂታል ሙዚቃ ውድድርን ለመቀላቀል፦

🎥 የአንድ ደቂቃ የራሳችን ሙዚቃ ቪዲዮ በTikTok ላይ እንፖስት
🏷 #1Wedefit እና #የምትኖሩበትን ከተማ አድራሻ ማስገባት እንዳትረሱ
📲 የTikTok ቻናል @Safaricomet ታግ እናድርግ

እንዝፈን! ፖስት እናድርግ! እናሸንፍ!

መልካም ዕድል!
እንዳያመልጣችሁ!


#SafaricomEthiopia #1Wedefit #FurtherAheadTogether #DigitalMusicChallenge
ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለክረምት ልዩ ሰልጣኝ የሁለተኛ ደረጃ መምህራን እና የትምህርት ቤት አመራሮች ጥሪ እያደረጉ ነው።

ልዩ የክረምት የአቅም ግንባታ ሰልጣኞቹ ሰኞ ሐምሌ 22/2016 ዓ.ም እስከ ቀኑ 6፡00 ብቻ ወደተመደቡበት ዩኒቨርሲቲ/ተቋም መግባት ይጠበቅባቸዋል።

ሰልጣኞች ወደየተመደባችሁበት ተቋም ስትሔዱ አንሶላ፣ ብርድ ልብስ እና የትራስ ጨርቅ መያዝ ይኖርባችኋል።

(ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ እና ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ያደረጉት ጥሪ ከላይ ተያይዟል፡፡)

@tikvahuniversity
የመምህራንና የትምህርት አመራሮች የክረምት ልዩ የአቅም ግንባታ ስልጠና የሚሰጡ የአሰልጣኞች ስልጠና (ToT) በተለያዩ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች እየተሰጠ ይገኛል።

የአሰልጣኞች ስልጠና ከሐምሌ 17-19/2016 ዓ.ም ለሦስት ተከታታይ ቀናት እንደሚሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር ያወጣው መርሐግብር ያሳያል።

የአሰልጣኞች ስልጠናው በትምህርት አመራርነት፣ በእንግሊዝኛ፣ ሒሳብ፣ ፊዚክስ፣ ኬሚስትሪ እና ባዮሎጂ የትምህርት መስኮች በማስተማር ስነ-ዘዴ ላይ ትኩረት በማድረግ እየተሰጠ እንደሚገኝ ተገልጿል።

ምስል፦ ዋቸሞ፣ ወልቂጤ እና አክሱም ዩኒቨርሲቲዎች

@tikvahuniversity
#የሥራ_ቅጥር_ጥቆማ

በመቐለ ዩኒቨርሲቲ የጤና ሳይንስ ኮሌጅ የህክምና ባለሙያዎችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡

➧ ተፈላጊ ባለሙያዎች ብዛት፦ 13
➧ የሥራ ቦታ፦ መቐለ ዩኒቨርሲቲ የጤና ሳይንስ ኮሌጅ
➧ የሥራ ልምድ፦ ከዜሮ ዓመት ጀምሮ
➧ የማመልከቻ ጊዜ፦ ከሐምሌ 12/2016 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የሥራ ቀናት

አመልካቾች የማይመለስ የትምህርት ማስረጃ እና CV እንዲሁም የሙያ ፍቃድ በመያዝ ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ከሐምሌ 12/2016 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት አስር ተከታታይ የሥራ ቀናት (እስከ ሐምሌ 25/2016 ዓ.ም ድረስ) በሰው ሃብት ልማት አስተዳደር ኮሌጅ መመዝገብ ትችላላችሁ፡፡

(ተጨማሪ መረጃ ከላይ ተያይዟል፡፡)

@tikvahuniversity
የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሕግ ትምህርት ቤት ተማሪዎች በኑረምበርግ ዓለም አቀፍ የምስለ ችሎት ውድድር እየተሳተፉ ነው።

በታዋቂው ውድድር በመጀመሪያው ዙር 600 ዩኒቨርሲቲዎች የተሳተፉ ሲሆን፤ ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ 40 ዩኒቨርሲቲዎች በጀርመን ኑረምበርግ ከተማ ለሚካሄደው የመጨረሻው ዙር ውድድር አልፈዋል።

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሕግ ትምህርት ቤት አፍሪካን በመወከል በውድድሩ ላይ ከሚሳተፉት አራት ዩኒቨርሲቲዎች መካከል አንዱ ሲሆን፤ኢትዮጵያን በመከል በውድድሩ ላይ የሚሳተፈው ብቸኛ ቡድን ነው።

መካሻው ጫኔ፣ እሱባለው ሞላ እና ትዕግስት ደርብ በውድድሩ ላይ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲን በመወከል የሚወዳደሩ ሲሆን፤ የቡድኑ አሰልጣኝ እንድሪያስ ጌታቸው እና የቡድኑ አስተባባሪ ተገኘ ዘርጋው በመሆን በውድድሩ በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።

ታሪካዊቷ ኑረምበርግ ከተማ ሁለተኛው የዓለም ጦርነት ማብቃትን ተከትሎ የናዚ የጦር ወንጀለኞች የተዳኙበት ከተማ ናት።

@tikvahuniversity
#KUE

ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ 'የአደጋ ጊዜ ትምህርት' ስርዓተ ትምህርት ቀርጿል፡፡


ስርዓተ ትምህርቱ በባለድርሻ አካላት እና በገምጋሚዎች ማረጋገጫ ተሰጥቶታል፡፡

በዚህም ዩኒቨርሲቲው በ2017 የትምህርት ዘመን በማስተርስ ደረጃ ትምህርቱን መስጠት እንደሚጀምር ይጠበቃል፡፡

የትምህርቱ መጀመር ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ በዘርፍ የሚያስፈልጉ በርካታ ሙያተኞችን ለማፍራት እንደሚያስችለው ተገልጿል፡፡

ስርዓተ ትምህርቱ በፀጥታ ችግር ምክንያት ከትምህርት የራቁ ዜጎች ወደ ትምህርት ተቋማት እንዲመለሱ እንዲሁም በመጠለያ ካምፕ ውስጥ ሆነው ትምህርት እንዲያገኙ የሚያደርግ ነው፡፡ በተጨማሪም የስነ-ልቦና ድጋፍ መስጠት በስርዓተ ትምህርቱ መካተቱም ታውቋል፡፡

@tikvahuniversity
#ነፃ_የፌሎውሺፕ_ዕድል

ከዩኒቨርሲቲ በቅርቡ ተመርቀዋል? የማኅበረሰብ ለውጥ ለማምጣት ፍላጎት አለዎት?

እንግዲያውስ ለዩናይትድ ስቴትስ ዓለም አቀፍ የልማት ተራድኦ ምላሽ የአመራር ፌሎውሺፕ ፕሮግራም ያመልክቱ።

ለሁለት ዓመት የሚቆየው ፌሎውሺፕ ፕሮግራሙ የአደጋ ተጋላጭነት አስተዳደር ክህሎትና ልምድ እንዲያጎለብቱ ያስችልዎታል።

በዘርፉ ባለሙያዎች ስልጠና የሚያገኙ ሲሆን፤ በፕሮጀክቶች ላይ በመስራት ከዘርፉ ሙያተኞች ጋር ትስስር እንዲፈጥሩ ይደረጋል።

ስለፌሎውሺፕ ፕሮግራሙ መረጃ ለማግኘት 👇
https://drive.google.com/file/d/12fK_rTrR37tfEasG7tPd4Sm--4L2jkeu/view?usp=drive_link

ኦንላይን ለማመልከት 👇
https://docs.google.com/forms/d/1QJflHITYBmP_dxSQRTWhUsGZoHRQashTNqMsIOd2zZI/edit

የማመልከቻ ጊዜው የሚያበቃው 👇
ነሐሴ 5/2016 ዓ.ም

@tikvahuniversity
ከM-PESA Safaricom app ፈጣን የኢንተርኔት ጥቅል በመግዛት እስከ 50% ተጨማሪ ጥቅል እናግኝ!

M-PESA ላይ እንመዝገብ! በM-PESA እንገበያይ!

🔗 የM-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያን በዚህ ሊንክ እናውርድ፦ https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle

የቴሌግራም ቻናላችንን እዚህ እንቀላቀል 👉 https://www.tg-me.com/Safaricom_Ethiopia_PLC

ስለ አገልግሎታችን ማንኛውንም ጥያቄ ወይም መረጃ በቴሌግራም ቻናላችን https://www.tg-me.com/Safaricom_Ethiopia_PLC 24/7 ማግኘት ይቻላል!

#MPESASafaricom #FurtherAheadTogether
Tikvah-University
#WachemoUniversity ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ተመድቦለታል። ዳዊት ሃየሶ (ዶ/ር) ከሐምሌ 12/2016 ዓ.ም ጀምሮ የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ሆነው እንደተወከሉ በትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) በቀን ሐምሌ 12/2016 ዓ.ም ተፈርሞ የወጣ ደብዳቤ ያሳያል። የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት የነበሩት ሀብታሙ አበበ (ዶ/ር) እና ምክትል ፕሬዝዳንት የነበሩት…
የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ሆነው የተመደቡት ዳዊት ሀዬሶ (ዶ/ር) ከዩኒቨርሲቲው የማኔጅመንት ካውንስል እና ሌሎች ሠራተኞች ጋር ትወውቅ አድርገዋል።

በዩኒቨርሲቲው የተጀመሩ ጠንካራ ሥራዎችን በማስቀጠል፣ ተቋሙን ተወዳዳሪ ለማድረግ እንደሚሰሩ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንቱ ገልፀዋል።

ተቋማዊ አስራሮችን በመገንባት የአካዳሚክ አካባቢ የልህቀት አቅጣጫዎችን ለማጠናከር ይሰራል ብለዋል።

@tikvahuniversity
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከ2.7 ሚሊዮን ዶላር በላይ በሆነ ወጪ የኤሌክትሮኒክስ መጽሄት፣ ኤሌክትሮኒክስ መጻሕፍት፣ የምርምር መመዘኛ እና የፕላጃሪዝም ማሳወቂያ ቴክኖሎጂ ገዝቷል።

የተገዙት የኤሌክትሮኒክስ መጽሄት፣ መጻሕፍት እና ቴክኖሎጂው የዩኒቨርሲቲውን የመማር ማስተማር እና የጥናትና ምርምር ሥራዎች በቴክኖሎጂ ለመደገፍ ያስችላል ተብሏል።

የኤሌክትሮኒክስ መጻሕፍቱ እና መጽሄቶቹ ለሚቀጥሉት ሦስት ዓመታት እንደሚያገለግሉ የዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ጀይሉ ዑመር (ዶ/ር) ተናግረዋል።

@tikvahuniversity
2024/10/04 21:12:02
Back to Top
HTML Embed Code: