Telegram Web Link
#NATIONAL_EXAM

ሁለተኛ ዙር የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና ተፈታኞች ወደየተመደቡበት ዩኒቨርሲቲዎች ከትናንት ጀምሮ በመግባት ላይ ይገኛሉ።

የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከማክሰኞ ሐምሌ 9/ 2016 ዓ.ም ጀምሮ ለሦስት ተከታታይ ቀናት በወረቀት እና በኦንላይን ይሰጣል።

በትግራይ ክልል ሁለተኛው ዙር የ12ኛ ክፍል ፈተና ከሐምሌ 9-12/2016 ዓ.ም በክልሉ በሚገኙ አራት ዩኒቨርሲቲዎች ይሰጣል፡፡

@tikvahuniversity
ወልድያ ዩኒቨርሲቲ የነባር የሁለተኛ ዲግሪ የክረምት ተማሪዎች ምዝገባ ሐምሌ 15 እና 16/2016 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል።

(ተጨማሪ መረጃ ከላይ ተያይዟል።)

@tikvahuniversity
ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ለነባር የክረምት ተማሪዎች እና ለአዲስ ሰልጣኝ መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች ጥሪ አድርጓል።

በዚህም በዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ነባር የክረምት መርሐግብር የቅድመ ምረቃ ተማሪዎች የነበራችሁ እንዲሁም በትምህርት ሚኒስቴር ወደ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ የተመደባቹ አዲስ ሰልጣኝ መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች ምዝገባ ሐምሌ 22/2016 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

@tikvahuniversity
ከጥቂት ቀናት በፊት አጋሮ እና ጅማ ከተሞች አካባቢ 'ከሰማይ ወደቁ ስለተባሉት ድንጋይ/አለት' ጥናት የሚያደርግ የባለሙያዎች ቡድን ማቋቋሙን ጅማ ዩኒቨርሲቲ አሳውቋል፡፡

በማኅበራዊ ትስስር ገጾች ሲዘዋወሩ የታዩት ምስሎች የወደቁት ነገሮች የአስትሮይድ ወይም ሚቲዮራይት ስብርባሪ ሊሆኑ እንደሚችሉ የገለፀው ዩኒቨርሲቲው፤ ይሁን እንጂ ተገቢው ምርምር እና የላቦራቶሪ ፍተሻ መደረግ እንዳለበት ገልጿል፡፡

በመሆኑም የጅማ ዩኒቨርሲቲ የፕሬዝዳንት ጽ/ቤት የሥነ ፈለክ ተመራማሪዎች፣ ኬሚስቶች እና የማቴርያል ሳይንቲስቶችን ያቀፈ የባለሙያዎች ቡድን አቋቁሟል፡፡

ቡድኑ ከኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ እና ጂኦስፓሺያል ኢንስቲትዩት እንዲሁም ሌሎች ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በትብብር እንደሚሰራ ገልፀዋል፡፡

የወደቁትን ቁሶች ወደ ጅማ ዩኒቨርሲቲ ላቦራቶሪ ለመውሰድ ከአካባቢው አመራሮች ጋር ንግግር መጀመሩን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡

@tikvahuniversity
#NATIONAL_EXAM

ለሁለተኛ ዙር የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና ተፈታኞች ዛሬ ዩኒቨርሲቲዎች አጠቃላይ ገለፃ ይሰጣሉ፡፡

የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል ፈተና ከነገ ሐምሌ 9/ 2016 ዓ.ም ጀምሮ ለሦስት ተከታታይ ቀናት በወረቀት እና በኦንላይን እንደሚሰጥ ይታወቃል።

ተፈታኞች ወደየተመደቡበት ዩኒቨርሲቲ የገቡ ሲሆን፤ በዛሬው ዕለት በፈተናው ዲሲፕሊን ዙሪያ አጠቃላይ ገለፃ እየተደረገላቸው ነው፡፡

ምስል፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ

@tikvahuniversity
ወሎ ዩኒቨርሲቲ በክረምት መርሐግብር ትምህርታችሁን ስትከታተሉ የነባራችሁ ሁሉም ነባር የክረምት የመጀመሪያ እና የሁለተኛ ዲግሪ ተማሪዎች የምዝገባ ጊዜ ሐምሌ 16 እና 17/2016 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡

በቅጣት ለመመዝገብ፦ ሐምሌ 18 እና 19/2016 ዓ.ም

የምዝገባ ቦታ፦ በደሴ እና በኮምቦልቻ ግቢዎች

(ተጨማሪ መረጃ ከላይ ተያይዟል።)

@tikvahuniversity
2024/10/01 13:32:09
Back to Top
HTML Embed Code: