Telegram Web Link
#ውጤት

የ2016 የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤትን አስመልክቶ የትምህርት ሚኒስቴር የሰጠው ሙሉ መግለጫ #1

#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
👆የቀጠለ

የ2016 የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤትን አስመልክቶ የትምህርት ሚኒስቴር የሰጠው ሙሉ መግለጫ #2

#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
👆የቀጠለ የ2016 የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤትን አስመልክቶ የትምህርት ሚኒስቴር የሰጠው ሙሉ መግለጫ #2 #TikvahEthiopia @tikvahethiopia
የ12ኛ ክፍል ውጤት እንዴት ማየት ይቻላል ?

የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ተፈታኞች ውጤታቸውን ከዛሬ ጳጉሜን 4/2016 ዓ.ም ለሊት 6:00 ጀምሮ ማየት እንደሚችሉ መገለፁ ይታወቃል።

ውጤት እንዴት ማየት እንደሚቻል በርካታ ጥያቄዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ደርሰዋል።

እኛም ተፈታኞች እንዴት ነው ውጤታቸውን ማየት የሚችሉት ? ስንል የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ከፍተኛ አመራርን ጠይቀናል፡፡

" ተማሪዎች ውጤታቸውን በኦንላይን የሚያዩበትን አማራጭ አድራሻዎች ማምሻውን አገልገሎቱ ይፋ ያደርጋል " ሲሉ ከፍተኛ አመራሩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጠዋል።

በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ውጤት በድረ-ገፅ፣ በአጭር የፅሑፍ መልዕክት እና በቴሌግራም ቦት ይፋ ተደርጎ እንደነበር ይታወሳል።

አገልግሎቱ አማራጭ አድራሻዎቹን ይፋ እንዳደረገ ወደናንተ እናደርሳለን።

Via @tikvahuniversity
TIKVAH-ETHIOPIA
የ12ኛ ክፍል ውጤት እንዴት ማየት ይቻላል ? የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ተፈታኞች ውጤታቸውን ከዛሬ ጳጉሜን 4/2016 ዓ.ም ለሊት 6:00 ጀምሮ ማየት እንደሚችሉ መገለፁ ይታወቃል። ውጤት እንዴት ማየት እንደሚቻል በርካታ ጥያቄዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ደርሰዋል። እኛም ተፈታኞች እንዴት ነው ውጤታቸውን ማየት የሚችሉት ? ስንል የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ከፍተኛ አመራርን…
#ውጤት : የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ተፈታኞች ውጤታቸውን ከዛሬ ጳጉሜን 4/2016 ዓ.ም ለሊት 6:00 ጀምሮ ማየት እንደሚችሉ መገለፁ ይታወቃል።

በሚከተሉት አማራጮች ውጤታችሁን ተመልከቱ፦

በፖርታል 👉 https://result.eaes.et

በአጭር የፅሑፍ መልዕክት 👉 6284

በቴሌግራም ቦት 👉 https://www.tg-me.com/EAESbot

ከውጤት መግለጫ ፖርታል እና ቴሌግራም ቦት ላይ ጊዜያዊ ሰርቲፊኬት ማውረድና ማተም እንደምትችሉ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።

ተፈታኞች በውጤት እና ተያያዥ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ቅሬታ ካላቸው ወደ አገልግሎቱ ቢሮ በአካል መሔድ ሳያስፈልጋችሁ ከSMS በስተቀር በውጤት መግለጫ አማራጮቹ ላይ Compliant የሚለውን በመጫን የቅሬታቸውን ዓይነት በተዘጋጀ የቅሬታ ፎርም ላይ በትክክል በመሙላት ማቅረብ ትችላላችሁ።

አገልግሎቱ በቅሬታችሁ ላይ ምላሽ ቅሬታቸውን ባቀረቡበት ተመሳሳይ አድራሻ የሚያሳውቅ መሆኑን ገልጿል።

Via @tikvahuniversity
#Tigray

" እየተደረገ ያለውን እንቅስቃሴና መሳሳብ ህዝብ ስላልወደደው አሁኑኑ መቆም አለበት !! " - ሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ

የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ም/ ፕሬዚደንትና የሰላምና ፀጥታ ሴክሬታሪያት ካቢኔ ሃላፊ ሌተናል ጀነራል ታደሰ ወረደ ዛሬ መግለጫ ሰጥተው ነበር።

በዚሁ ጋዜጣዊ መግለጫ ፥ " በአሁኑ ወቅት ለሁለት በተከፈለው ህወሓት መካከል እየተደረገ ያለው እንቅስቃሴና መሳሳብ ህዝብ ስላልወደደው መቆም አለበት " ብለዋል።

ሌ/ጄነራሉ " በተቃውሞ ሆነ በድጋፍ የህዝብ ማእበል ለመፍጠር የሚደረገው ጥረት ህዝቡ ስጋት ውስጥ እየከተተ ስለሆነ ከአሁን ጀምሮ መቆም አለበት " ሲሉ አሳስበዋል።

" ሰላማዊ የአዳራሽ ውስጥ ሰብሰባ ማድረግ ይፈቀዳል " ሲሉ አክለዋል።

ሌ/ጄነራል ታደሰ " አዳዲስ የመንግስት የስራ ምደባዎች እየታዩ ነው ምደባዎች እንዲቆሙ ሁሉም ነገሮች በስከነ አካሄድ እንዲፈፀሙ እንጠይቃለን " ብለዋል።

" የማስማማት ጥረት እየተደረገ ነው (ለሁለት የተከፈሉትን የህወሓት አመራሮች) ፤ ከተቻለ አንድ እንዲሆኑ ካልተቻለ ልዩነታቸው አክብረው በህግ እንዲጓዙ ከዚህ ውጭ ያለው አካሄድ ግን ቀይ መስመር አለው የሚባል ስላልሆነ መገታት አለበት " ሲሉ አስጠንቅቀዋል።

በሌላ በኩል ሌ/ጄነራሉ " የትግራይ እና የአማራ ህዝቦች ዘላቂ ግንኙነት የሚጎዳ ማንኛውም እንቅስቃሴ መቆም አለበት " ብለዋል።

ተመላሽ ተፈናቃዮች ላይ ሰላምን የሚረብሽ እንቅስቃሴ እንዳለ በመጠቆም " ይሄ መቆም አለበት " ሲሉ አስገንዝበዋል።

" ይህንን ዓይነት እንቅስቃሴ ፍሬ ያለው ትርጉም የሌለው መሆኑ ካለፈው እንማር " ሲሉ ገልጸዋል።

" በጠብመንጃ የሚወሰድ መሬትም ሆኖ የሚቀየር ድንበር የለም ስለሆነም በአማራ ክልል በኩል ያሉ ታጣቂዎች ከድርጊታቸው በመቆጠብ ወደ ቀልባቸው ይመለሱ " ሲሉ ማሳሰባቸውን የመቐለ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ዘግቧል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በመግለጫው የአማራ ክልል ስም በመነሳቱ በክልሉ በኩል የሚሰጥ ምላሽ ጠይቆ ያቀርባል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia
2024/09/30 18:12:30
Back to Top
HTML Embed Code: