Telegram Web Link
TIKVAH-ETHIOPIA
#ውጤት : የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ተፈታኞች ውጤታቸውን ከዛሬ ጳጉሜን 4/2016 ዓ.ም ለሊት 6:00 ጀምሮ ማየት እንደሚችሉ መገለፁ ይታወቃል። በሚከተሉት አማራጮች ውጤታችሁን ተመልከቱ፦ ► በፖርታል 👉 https://result.eaes.et ► በአጭር የፅሑፍ መልዕክት 👉 6284 ► በቴሌግራም ቦት 👉 https://www.tg-me.com/EAESbot ከውጤት መግለጫ ፖርታል እና ቴሌግራም…
የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ።

ተማሪዎች እና ወላጆች የፈተናውን ውጤት ከዚህ ሰዓት ጀምሮ ማየት ይችላሉ።

ውጤት የሚታየው ፦

► በፖርታል 👉 https://result.eaes.et

► በአጭር የፅሑፍ መልዕክት 👉 6284

► በቴሌግራም ቦት 👉 https://www.tg-me.com/EAESbot ላይ ነው።

ከፍተኛ የኔትዎርክ መጨናነቅ ስለሚኖር በትዕግስት ይሞክሩት።

በ2016 ዓ / ም ለፈተናው ከተቀመጡት ከ684 ሺህ በላይ ተማሪዎች 36,409 ተማሪዎች (5.4 በመቶ) ናቸው በቀጥታ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚያስገባቸውን 50% እና ከዛ በላይ ውጤት ያመጡት።

ምንም እንኳን በተማሪ ቁጥር ደረጃ ከአምናው የቀነሰ ቢሆንም በቀጣይ የትምህርት ዘመንም የሬሜዲያል ፕሮግራም ይኖራል።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia @tikvahuniversity
#የቴክኖ የአዲስ ዓመት ልዩ የበዓል ስጦታ!

የአዲስ አመት ልዪ ስጦታ ከቴክኖ ሞባይል ኢትዮጵያ፣ ከየትኛውም የቴክኖ ሱቅ የቴክኖ ስማርት ስልክን ሲገዙ አብሮት ካለ ወዳጅ ዘመድ ወይም ጓደኛ ጋር ፎቶ በመነሳት የማህበራዊ ገጾት ላይ በመለጠፍ እና ብዙ ላይክ በማግኘት የዱባይ ደርሶ መልስ የቢዝነስ ክላስ የአውሮፕላን ትኬት፣ ላፕቶፖች፣ የቴክኖ ስማርት ስልኮችን እና ገደብ አልባ የኢንተርኔት ፓኬጆችን ይሸለሙ፡፡

የውድድሩ መመሪያ
1. የቴክኖ ኢትዮጵያን ፌስ ቡክ ፣ ኢንስታግራም እና ቲክቶክ ገጾችን ፎሎው ያድርጉ፡፡
2. የተነሱትን ፎቶ በመረጡት ማህበራዊ ሚዲያ ሲለጥፉ የቴክኖ ኢትዮጵያን ገፅ ከፖስቶት ጋር ታግ ያድርጉ፡፡ ብዙ ላይክ እና ኢንጌጅመንት ያገኘው ተሸላሚ ይሆናል፡፡
- Tag ሲያደርጉን ለ Facebook @ TecnoEt ፣ ለ Instagram @ TecnoMobileEthiopia እና ለ TikTok @ TecnoEt ን  ሜንሽን ማድረግ እንዳይረሱ።)
- በተጨማሪም #TecnoEt2017 ን keyword መጠቀም እንዳይረሱ)
#SamiTech

አዳዲስ ላፕቶፕች ከአንድ ዓመት ዋስትና ጋር!!
@samcomptech

ለቢሮዎች፣ ለተማሪዎች ፣ ለዲዛይን ባለሙያዎች ፣ ለጌመሮች  ወ.ዘ.ተ
አቅምን ካገናዘቡ እስከ ቅንጡ ላፕቶፖች ይህ ቀረ ሳይሉ የሚያገኙበትን ሱቃችንን ይጎብኙ።

የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ ባሉበት ሆነው ይዘዙን እናደርሳለን።
የዕቃዎች ዋጋ፣ ዓይነት እና አድራሻ ለማግኘት ይሄን 👉 @samcomptech ተጭነው በቴሌግራምው ማየት ይችላሉ።

@sww2844 0928442662 / 0940141114

https://maps.app.goo.gl/H3PM1NrTcQ4SWkK17
🔈#የዜጎችድምፅ

🔵 “ በጸጥታው ችግር  ታካሚዎች በሰው ጫንቃ ታዝለው ነው ሆስፒታል የሚሄዱት፡፡ ተሂዶም መድኃኒት የማይገኝበት ጊዜ አለ ” - ነዋሪዎች

⚫️ “ አቅራቢዎች በቂ የመድኃኒት አቅርቦት እያመጡ አይደለም ” - የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል

በአማራ ክልል፣ ባሕር ዳር ከተማ የሚገኙ ነዋሪዎች ከሆስፒታል ውስጥ መድኃኒት ስለማይገኝ ከግል ፋርማሲዎች በከፍተኛ ዋጋ ለመግዛት እየተገደዱ መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

ችግሩ የሚገጥማቸው በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል ለህክምና ሲሄዱ መሆኑን ለአብነት ገልጸዋክ።

አንዳንዴም በጸጥታ ችግር መንገዶች ስለሚዘጋጉ ተመላላሽ ህክምና በወቅቱ መታከም እንዳልቻሉ አስረድተዋል፡፡

ከፍተኛ የሆነ ችግር ውስጥ ከገቡ ከዓመት በላይ እንዳስቆጠሩ ተናግረዋል።

በከተማዋ ተቋማት እንኳ ከሚከፈቱበት የሚዘጉበት ጊዜ እንደሚበዛ አስረድተዋል፡፡

በተለይ ደግሞ የጸጥታ ችግር በሚፋፋምበት ወቅት የትራንስፖርት እንቅስቃሴ ሲለሚገደብ ታካሚዎች በሰው ጫንቃ ታዝለው ወደ ሆስፒታል እንደሚወሰዱ ጠቁመዋል።

በሸክም ተወስደው መድኃኒትና ሠራተኛ በሆስፒታሉ የማይገኝበት ወቅት እንዳል አስረድተዋል፡፡

በዚህም በተለይ ተመላላሽ ታካሚዎች መዳን እየቻሉ የመሞት እድላቸው እየሰፋ ነውና የሰላም ያለህ! ሲሉ ተማጽነዋል፡፡

ስማቸው እንዲነገር ያልፈቀዱ በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል ውስጥ የሚሰሩ አንድ ሀኪም፣ ታካሚዎች ሆስፒታሉ ውስጥ ‘ግላቭ ብቻ ነው ያለው ሌላውን ውጪ ነው የምንገዘው’ እንዳሏቸው ገልጸዋል።

“Ampicillin፣ Gentamicin፣ Vancomicin፣ Cefepime፣ Tretionin” የሚባሉ መድኃኒቶች በሆስፒታሉ ውስጥ እንደሌሉ፣ የ“Laboratory፣ CBC፣ Serum electrolyte፣Liver function test፣ CSF analysis፣ Echo፣ CT scan” አገልግሎቶች በተሟላ ሁኔታ እየተሰጡ እንዳልሆነም ገልጸዋል፡፡

በተለይ ከሳምንታት በፊት ትራንስፖርት ተቋርጦ ስለነበር ሠራተኞቹ ሥራ ለመግባት ተቸግረው እንደነበር፣ በዚህም ታካሚዎቹ ሰርጀሪ የሚሰራላቸው ቀኑ እየተራዘመ መሆኑን አልደበቁም፡፡

ለጉዳዩን ምላሽ የጠየቅነው የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል፣ “አቅራቢዎች በቂ የመድኃኒት አቅርቦት እያመጡ አይደለም፡፡ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ከጸጥታውም ይሁን ካለው የገበያ ሁኔታ ጋር ተያይዞ ማለት ነው” ብሏል፡፡

“ከዚያ በሻገር ግን ዛሬ ላይ መደበኛ ሥራችንን ለማስኬድ የሚያስችል ሰቶክም አለን፡፡ ችግሮችም ይኖራሉ ከአቅማችን በላይ በሆኑ ምክንያቶች” ነው ያለው፡፡

“በቂ ስቶኮች አንይዝም፡፡ ልናገኝ አንችልም፡፡ የ3፣ የ6 ወራት ብለን ልንገዛ አንችልም፡፡ እንገዛ ብንል በጀትም አይኖረንም አቅራቢም አናገኝም” ሲል አስረድቷል፡፡

ከጸጥታው ሁኔታ ጋር ተይይዞ ሠራተኞች አይገቡም ተብሎ ለቀረበው ቅሬታ ሆስፒታሉ ፥ “ ሠራተኞች ይገባሉ፡፡ መንገድ በተዘጋ ጊዜ በአምቡላንስ ነው የምናመጣቸው፡፡ ጦርነት በሚኖርበት ጊዜ ግን አስቸጋሪ ነው ” ሲል ገልጿል፡፡

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#NewsAlert🚨

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን የጭነት ተሽከርካሪዎችን እንቅስቃሴን ለመወሰን የወጣ መመሪያ ቁጥር 149/2016 አስመልክቶ ዛሬ መግለጫ ሰጥቷል።

ምን አለ ?

- መመሪያው የሚመለከታቸው የጭነት ተሽከርካሪዎች / የጭነት አቅማቸው ከ1 ቶን ወይም 10 ኩንታል በላይ የሆኑ ተሽከርካሪዎችን ነው።

- እነዚህ ተሽከርካሪዎች ጠዋት ከ1:00 ሰዓት እስከ 3:00 ሰዓት ድረስ እንዲሁም ከሰዓት 10:30 እስከ ምሽት 1:00 ሰዓት ድረስ መንቀሳቀስ እንዳይችሉ ገደብ ተጥሎባቸዋል።

- በዋና መንገዶች ላይ ማቆም፤ ጭነት ማውረድና መጫን እንዲሁም መንቀሳቀስ በክልከላው የተካተቱ ናቸው።

- አዲሱ መመሪያ ከዚህ በፊት ከነበረው የሰዓት ገደብ ላይ በቀረቡ ቅሬታዎች ላይ ማሻሻያ ለማድረግ ታስቦ የወጣ እንደሆነ ተመላክቷል።

- አዲሱ መመሪያ ከመስከረም 2/2017 ጀምሮ ተግባራዊ የሚሆን ሲሆን እሁድ እንዲሁም የበዓል ቀናትን አይመለከትም።

የተቀመጡ የቅጣት እርከኖች ምንድናቸው ?

➡️ በተከለከለ ሰዓት በዋና ዋና መንገዶች ላይ የቆሙ የ10ሺ ብር ቅጣት፤

➡️ በተከለከለው የሰዓት ገደብ የተንቀሳቀሰ 20ሺ ብር የገንዘብ ቅጣት፤

➡️ በቅጣት ሂደቱ በድጋሜ የተቀጣ አሽከርካሪ የቅጣት እርከኑን በእጥፍ የሚቀጣ ይሆናል።

➡️ በተጨማሪ የቅጣት ወረቀት በመያዝ በዋና ዋና መንገዶች ላይ የሚንቀሳቀስ ትዕዛዝ ባለማክበር ተጨማሪ ቅጣት የሚተላለፍባቸው ይሆናል ተብሏል።

ቅሬታ ያላቸው በጹሑፍ ቅሬታቸውን ለባለሥልጣኑ በማመልከቻ ማቅረብ የሚችሉ ሲሆን የባለሥልጣኑ ውሳኔ የመጨረሻ ውሳኔ ይሆናል።

ይህ መመሪያ ቁጥር 149/2016 ከዚህ ቀደም የነበረውን መመሪያ ቁጥር 38/2013 እንዲሁም ሰርኩላሮች፣ ልማዳዊ አሰራሮች የሚሽር ነው።

ይህ መመሪያ ተግባራዊ የማይደረግባቸው የትኞቹ ተሽከርካሪዎች ላይ ነው ?

1ኛ. የሀገር መከላከያ፤ የፖሊስ እንዲሁም በጸጥታ አካላት ስም የተመዘገቡ ተሽከርካሪዎች፤

2ኛ. የድንገተኛ አደጋ ተሽከርካሪዎች፤

3ኛ. ነዳጅ የሚያመላልሱ ቦቴዎችን አይመለከትም።

ከዚህ ቀደም ወጥ አተገባበር ባልተስተዋለባቸው የውሃ አመላላሽ ቦቴዎች ላይ አዲሱ መመሪያ እንዴት ይመለከተዋል ? በሚል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ላነሳው ጥያቄ ፥ በአዲሱ መመሪያ እንደሌሎች ከባድ ተሽከርካሪዎች እንደሚስተናገዱ ተገልጿል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
" በይቅርታ ከእስር እንዲለቀቁ ተወስኗል " - ሀገር መከላከያ ሰራዊት

ሀገር መከላከያ ሠራዊት " 178 የትግራይ ተወላጅ የሠራዊት አባላት ከዛሬ ጳጉሜን 5/2016 ጀምሮ ከእስር በይቅርታ እንዲለቀቁ ተወስኗል " ሲል አሳወቀ።

መከላከያ በአዲስ ዓመት ይቅርታ የተደረገላቸው የህወሓት ታጣቂ ሃይሎች ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ/ም የሰሜን ዕዝ ላይ ጥቃት መከፈታቸውን ተከትሎ የተሰጣቸውን ህገ-መንግስታዊ ተልዕኮ ወደ ጎን በመተው በሰራዊቱ እና በህዝብ ጥቅሞች ላይ ወንጀል የፈጸሙ ናቸው ብሏል።

" ጉዳያቸው በወታደራዊ ፍትህ ስርዓቱ አማካኝነት ክስ ተመስርቶባቸው በተከሰሱበት ወንጀል ጥፋተኛ ሆነው በመገኘታቸው ምክንያት በወታደራዊ ፍርድ ቤቶች እስከ ሞት ቅጣት ተወስኖባቸው በማረሚያ ቤት ይገኙ ነበር " ሲል አስረድቷል።

ሀገር መከላከያ " እኚሁ የሠራዊት አባላት በፈፀሙት ወንጀል ተፀፅተው የይቅርታ ጥያቄአቸውን ለመንግስት እና ለመከላከያ ሚኒስቴር አሥገብተዋል " ሲልም አክሏል።

በዚህም በአዲሱ ዓመት በይቅርታ 178ቱ የትግራይ ተወላጅ የሠራዊት አባላት ከዛሬ ጀምሮ ከእስር እንዲለቀቁ መወሰኑን ይፋ አድርጓል።

#FDREDefenseForce

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#እንድታውቁት🚨

በአዲስ አበባ የጭነት ፣ ማሽነሪዎችን እና መሰል ተሸከርካሪዎችን እንቅስቃሴ ለመወሰን የወጣ መመሪያ ቁጥር 149/2016 ምን ይላል ?

- መመሪያው ወደ አዲስ አበባ ከተማ ክልል በሚገቡና በከተማ ውስጥ በሚንቀሳቀሱ እንዲሁም ከተማዋን አቋርጠው በሚያልፉ የመጫን አቅማቸው ከ1 ቶን ወይም ከ1ዐ ኩንታል በላይ የሆኑ የተለያዩ የፈሳሽና የደረቅ ጭነት ተሽከርካሪዎች እና የኮንስትራክሽን ማሽነሪዎች ላይ ተፈፃሚ ይሆናል፡፡

- ማንኛውም የጭነት ማመላለሻ ተሽከርካሪ እና የኮንስትራክሽን ማሽነሪ ከጠዋቱ 1፡00 እስከ 3፡00 ሰዓት ከሰዓት በኃላ ከቀኑ 10፡30 እስከ ምሽቱ 1፡ዐዐ ሰዓት ወደ ከተማ ውስጥ መግባትም ሆነ በከተማ ውስጥ መንቀሳቀስ፣ ጭነት መጫንም ሆነ ማራገፍ እንዲሁም በዋና ዋና የትራፊክ ፍሰት በሚበዛባቸው መንገዶች ላይ መቆም የተከለከለ ነው፡፡

- በዚህ መመሪያ መሠረት ወደ ከተማ መግባትም ሆነ በከተማ ውስጥ መንቀሳቀስ የተከለከለ የጭነት ተሽከርካሪ ወይም የኮንስትራክሽን ማሽነሪ ወደ ከተማ ለመግባት በእንቅስቃሴ ላይ እያለ የሰዓት ገደቡ ቢደርስበት በከተማዋ መግቢያ በሮች ላይ ከዋና መንገድ ወጣ ብሎ በሚገኝ ቦታ ላይ የአካባቢውን የትራፊክ እንቅስቃሴ በማያውክ መልኩ በመቆም የሰዓት ገደቡ እስኪያልፍ መጠበቅ አለበት።

- ማንኛውም የጭነት ተሽከርካሪ ወይም የኮንስትራክሽን ማሽነሪ በከተማ ውስጥ በእንቅስቃሴ ላይ እያለ በዚህ መመሪያ የተደነገገው የጊዜ ገደብ ቢደርስበት የአካባቢውን የትራፊክ እንቅስቃሴ በማያውክ መልኩ ከመንገድ በመውጣት መቆም አለበት።

- በዚህ መመሪያ የተደነገገው የሰዓት ገደብ #እሁድ እና #የበዓል_ቀናት ላይ ተግባራዊ የማይደረግ በመሆኑ ማናቸውም የጭነት ተሸከርካሪ ወይም የኮንስትራክሽን ማሽነሪ ወደ ከተማ ውስጥ መግባትም ሆነ በከተማ ውስጥ መንቀሳቀስ፣ ጭነት መጫን ሆነ ማራገፍ ይችላል፡፡

የሰዓት ገደብ የማይመለከታቸው ተሽከርካሪዎች የትኞቹ ናቸው ?

1. ሰሌዳቸው በሀገር መከላከያ ወይም በፖሊስ የተመዘገቡ የሀገር መከላከያ እና ሌሎች የፀጥታ ስራዎችን የሚያከናወኑ ከባድና ቀላል የጭነት ተሽከርካሪዎች፤

2. በህግ መሠረት የድንገተኛ አደጋ ተሸከርካሪዎች ተብለው የተለዩ የድንገተኛ አደጋ የሚሰሩ ቀላልና ከባድ የጭነት ተሽከርካሪዎች፤

3. ነዳጅ የሚያመላልሱ ቦቴዎች

አስተዳደራዊ ቅጣቱ ምን ይመስላል ?

🔵 በተከለከለ ሰዓት ወደ ከተማ ውስጥ በመግባትና በዋና ዋና መንገዶች ላይ የቆመ ብር 10,000 (አስር ሺህ ) ይቀጣል፡፡

🔵 በዋና ዋና መንገድ ላይ የተንቀሳቀሰም ሆነ የጭነት መጫንና ማውረድ ተግባር የፈፀመ ወይም የኮንስትራክሽን ስራ የሰራ ብር 20,000 (ሃያ ሺህ) ይቀጣል፡፡

🔵 በመመሪያው ላይ የተደነገገወን የሰዓት ገደብ በመተላለፍ ከተቀጣ በኃላ ለሁለተኛ ጊዜ ጥፋቱን በመድገም የተገኘ ማንኛውም ሰው ከላይ የተገለፀውን ቅጣት በእጥፍ ይከፍላል፡፡

NB. በተከለከለው ሰዓት በከተማው ውስጥ ሲንቀሳቃስ በመገኘቱ ቅጣት የተጣለበት አሸከርካሪ ሰዓቱ ሳይደርስ የቅጣት ወረቀት ይዞ በተከለከለው ሰዓት እንዲንቀሳቀስ አይፈቀድለትም። የትራፊክ ተቆጣጣሪው ፍሰት በማያሰናክል ቦታ ላይ ተሸከርካሪው እንዲቆም በማድረግ ቅጣቱን እንዲከፍል ማድረግ አለበት፡፡

🗓 ይህ መመሪያ ከመስከረም 2 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮ ተግባራዊ መሆን ይጀምራል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
TIKVAH-ETHIOPIA
የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ። ተማሪዎች እና ወላጆች የፈተናውን ውጤት ከዚህ ሰዓት ጀምሮ ማየት ይችላሉ። ውጤት የሚታየው ፦ ► በፖርታል 👉 https://result.eaes.et ► በአጭር የፅሑፍ መልዕክት 👉 6284 ► በቴሌግራም ቦት 👉 https://www.tg-me.com/EAESbot ላይ ነው። ከፍተኛ የኔትዎርክ መጨናነቅ ስለሚኖር በትዕግስት ይሞክሩት። በ2016 ዓ / ም ለፈተናው ከተቀመጡት…
#ዮናስንጉሰ #ሔለንበርኸ👏

በ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከሀገሪቱ ከፍተኛውን ውጤት ያመጣው የትግራይ ፣ የቓላሚኖ ልዩ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪው ዮናስ ንጉሰ ነው።

በትግራይ ሀገር አቀፉ ፈተና ከ700 መሰጠቱ ይታወሳል።

ተማሪ ዮናስ ንጉሰ ከ700ው 675 በማምጣት በሀገር ደረጃ ታሪካዊ ነው የተባለውን ውጤት አስመዝግቧል።

ከዚህ ቀደም ከ700 በተሰጠ ፈተና ይሄን ያህል ከፍተኛ ውጤት (675) በሀገር ደረጃ ሲመዘገብ የመጀመሪያ ነው ተብሏል።

ሌላኛዋ የቓላሚኖ ተማሪ ሔለን በርኸ 662 በማምጣት ከፍተኛ ውጤት አስመዝግባለች።

ሌሎችም የቓላሚኖ ተማሪዎች ከፍተኛ ውጤት ማምጣታቸው ተሰምቷል።

የትግራይ ልማት ማህበር በተመዘገው ውጤት መደሰቱን ገልጿል።

ትምህርት ቤቱ እጅግ ጎበዝ የሚባሉ ተማሪዎች የሚማሩበት ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ዮናስንጉሰ #ሔለንበርኸ👏 በ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከሀገሪቱ ከፍተኛውን ውጤት ያመጣው የትግራይ ፣ የቓላሚኖ ልዩ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪው ዮናስ ንጉሰ ነው። በትግራይ ሀገር አቀፉ ፈተና ከ700 መሰጠቱ ይታወሳል። ተማሪ ዮናስ ንጉሰ ከ700ው 675 በማምጣት በሀገር ደረጃ ታሪካዊ ነው የተባለውን ውጤት አስመዝግቧል። ከዚህ ቀደም ከ700 በተሰጠ ፈተና ይሄን ያህል ከፍተኛ ውጤት (675)…
👏 #ሲፈን_ተክሉ

የአዲስ አበባዋ ተማሪ ሲፈን ተክሉ በዘንድሮ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በተፈጥሮ ሳይንስ ከ600ው 575 በማምጣት ከፍተኛ ውጤት አስመዝግባለች።

ሲፈን የኦግዝሌየም ካቶሊክ ትምህርት ቤት ተማሪ ናት።

ተማሪዋ " ጌዜን ትምህርት ላይ ማሳለፌ ፣በቡድን ማጥናቴ ፣ የቤተሰብና የመምህራኖቼ ድጋፍ ለዚህ ስኬት አብቅቶኛል " ብላለች።

ለቤተሰቦቿ 2ኛ ልጅ የሆነችው ሲፈን የስርዓተ ምግብ ባለሙያ የመሆኑ ዝንባሌ እንዳላትም ተናግራለች። #AMN

@tikvahethiopia
ከዘመን ዘመን ስንሻገር፣ መስኩ በአደይ ሲንቆጠቆጥ
በአደይ አበባ ጥቅል፣ በአዲስ ዓመት ስጦታ እናሸብርቅ!


🤩 ተናፋቂዋን አደይ አበባ ጥቅል እስከ 20% ከሚደርስ ቅናሽ ጋር በቴሌብር ይግዙ፤ የበዓል ስጦታ ለወዳጅ ቤተሰብ ያበርክቱ!

🔗 ቴሌብር ሱፐርአፕን https://onelink.to/uecbbr ወይም *127# ይጠቀሙ

🌼 መልካም አዲስ ዓመት 🌼

#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
#አቢሲንያ_ባንክ

እንኳን አደረሳችሁ !

በካሽ ጎ ከውጭ ሀገር የተላከልዎትን ገንዘብ በአቢሲንያ ባንክ ሲቀበሉ ከዕለታዊ ተመን በተጨማሪ 16% ጉርሻ ያገኛሉ። ከነሐሴ 30 ቀን 2016 ዓ.ም እስከ መስከረም 24 ቀን 2017 ዓ.ም የሚቆይ።

የሞባይል መተግበሪያውን ከ Play Store ወይም App Store በማውረድ ይጠቀሙ።

ለአንድሮይድ ስልኮች
https://play.google.com/store/apps/details?id=com.bankofabyssinia.cashgo&hl=en&gl=US

ለአፕል ስልኮች
https://apps.apple.com/us/app/cashgo/id1559346306

አቢሲንያ የሁሉም ምርጫ!
#cashogo #newyear #BankofAbyssinia #የሁሉም_ምርጫ #The_Choice_For_all
2024/09/30 16:31:11
Back to Top
HTML Embed Code: