Telegram Web Link
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
ሌ/ጄነራል ፃድቃን ገ/ትንሳኤ ምን አሉ ?

የትግራይ ጊዜዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የሚመሩትና ም/ፕሬዜዳንት ሌ/ጄነራል ፃድቃን ገ/ትንሳኤ የሚገኙበት የአመራሮች ቡድን ከሰሞኑን ህዝባዊ ውይይቶችን እያደረገ ነው።

ትላንት ማይጨው ላይ በነበረ ውይይት ጀነራል ፃድቃን ስለ ፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ዙሪያ ሃሳቦች ሰጥተዋል።

" የሚታየውን ዋናው የልዩነት ነጥብ በፕሪቶሪያ ውል ላይ ያለ የአመለካለት ልዩነት ነው " ብለዋል።

" ስምምነቱ ዓለም አቀፍ ውል ነው መከበር አለበት " ሲሉም በቅርቡ እኔ ነኝ ህጋዊ ህወሓት የሚለው የእነ ዶ/ር ደብረፅዮን ሃይል ሲሸነቆጥ አድርገዋል።

ፕሬዜዳንቱ ጌታቸው ረዳ ደግሞ ሃሳቡ አጠናክረዋል።

"  የፕሪቶሪያ ውል ለማፍረስ የሚደረግ ማንኛውም እንቅስቃሴ ጦርነትን መጥራት መሆኑ ሊታወቅ ይገባል " በማለት አስጠንቅቀዋል።

የጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜዳንትና ምክትላቸው በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነትና አመለካከትና አተገባበር  ዙሪያ የሰነዙሩዋቸው ጥንካራ ትችቶች ተከተሎ የእነ ዶ/ር ደብረፅዮን ሃይል መልስ ሰጥቷል።

የእነ ዶ/ር ደብረፅዮን ሃይል በመወከል መልስ የሰጡት የኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድና በህወሓት ምክትል ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ የሚመሩ በርካታ የማእከላዊ ኮሚቴ አባላት " ህጋዊ ጉባኤ አይደለም " ባሉት 14ኛው ጉባኤ የስራ አስፈፃሚ አባል ሆነው የተመረጡና በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ህወሓት ወክለው ከተደራደሩትና ውሉ ከፈረሙት አንዱ ፍስሃ ሃፍተፅዮን (ዶ/ር) ናቸው ። 

ፍስሃ (ዶ/ር) " ህወሓት የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት እንደማይደግፍ ተደርጎ እየቀረበ ያለው ሃሳብ ስም ማጥፋት ነው " ሲሉ ኮንነዋብ።

" ህወሓት በፕሪቶሪያ ስምምነትና አተገባበር የፀና አቋም አለው " ሲሉ ተናግዋል።

የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በደቡብ አፍሪካ በሚፈፀምበት ወቅት ትግራይን ወክለው በተሳተፉ ተደራዳሪዎች መካከል ልዩነት ተፈጥሮ እንደነበረ አስታውሰዋል።

ጊዚያዊ መንግስት ማቋቋም አለመቋቋም በተደራዳሪዎች መካከል ከነበሩት የሃሳብ ልዩነት እንድ አንድ ነጥብ ጠቅሰውታል።   

" በፕሪቶሪያ ተስማምተን መፈረማችን አንድ ፀጋ ሆኖ የቀሩት ጉድለቶች በሂደት እንፈታቸዋለን ብለን አምነን ነው የተመለስነው " ሲሉ ፍስሃ (ዶ/ር) ገልጸዋል።

ሌላው " ህወሓት ከሻዕብያ ጋር ግንኙነት አለው የሚለው ወሬ ነጭ ውሸት ነው " ሲሉ ተናግረዋል።

የፕሪቶሪያ ስምምነት ተደራዳሪና ፈራሚ ቡድን አባል የሆኑት ፍስሃ (ዶ/ር) " በውስጣችን ያሉ ግን መሬታችን ወረው ለያዙ ያግዛሉ " በማለት በፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ የሚመራውን ጊዚያዊ አስተዳደር ወቅሰዋል። 

" ወደ ጦርነት የሚያስገባ አንድም ምክንያት የለም " ያሉ ሲሆን በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት አፈፃፀምና አተገባበር እሳቸውን ያቀፈው የእነ ዶ/ር ደብረፅዮን ሃይል ትክክለኛ እንደሆነ ሞግተዋል።

የአሜሪካው የፕሪቶሪያ የሰላም አደራዳሪ ማይክ ሃመር ውሉና አተገባበሩ የሚመለከት ጉብኝት ለማድረግ ወደ ኢትዮጵያ ይመጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።

በህወሓት አመራሮች መካከል የተፈጠረው ፓለቲካዊ ልዩነት ግን አሁንም አልበረደም።

የእነ ዶ/ር ደብረፅዮን ሃይል " ህጋዊ  አይደለም " የተባለ 14ኛ ጉባኤ ካካሄደ በኋላ የእነ ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ ሃይል ፥
- ደርጅታዊ ስብሰባዎች በመንግስት የስራ ሰአት እንዳይካሄዱ የሚከለክል የስራ መመሪያ ፣
- ላልተወሰነ ጊዜ ሰላማዊ ሰልፍ የሚከለክል ማስጠንቀቅያ ፣
- የዞን አስተዳደሪዎች ሹምሹር ያካሄደ ሲሆን በክልሉ የዞኑ ትልልቅ ከተሞች በመዘዋወርም ህዝባዊ ውይይቶች በማካሄድ ላይ ይገኛል።

ባለፈው ሳምንት በተምቤን ፣ በዓዲግራትና በማይጨው ህዝባዊ ውይይቶች አካሂዷል።

በቀጣይ የጳጉሜን ቀናትም ኣክሱምና እንዳስላሰ ሽረ እንደሚያቀና እየተነገረ ነው።

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ዕለታዊ

የዶላር ምንዛሬ ዋጋ ዛሬ ጭማሪ አሳይቷል።

በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ላለፉት 2 ተከታታይ ቀናት ዶላር መግዣው  106.3684 ፤ መሸጫው ደግሞ 118.0689 ነበር።

በዛሬው የምንዛሬ ዋጋ ጭማሪ ተይቷል።

መግዣው ወደ 107 ብር ከ7565 ሳንቲም ሲጨምር ፤ መሸጫው ወደ 119 ብር ከ6097 ሳንቲም ከፍ ብሏል።

ፓውንድ መግዣው 135 ብር 6525 ፤ መሸጫው 151.2774 ገብቷል።

ዩሮም ጨምሯል። 119 ብር ከ7282 ሳንቲም መግዣው ሲሆን 132 ብር ከ8983 ሳንቲም መሸጫው ተቆርጦለታል።

አንዱ የኩዌት ዲናር 337 ብር ከ4568 ሳንቲም መግዣው ሲሆን 376 ብር ከ3261 መሸጫው ሆኗል።

የUAE ድርሃም መግዣው 29 ብር ከ3399 ሳንቲም መሸጫው ደግሞ 32 ብር ከ5672 ሳንቲም ተቆርጦለታል።

(ጳጉሜን 1 ቀን 2016 ዓ/ም)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Telegram : የቴሌግራም መስራች እና ዋናው ስራ አስኪያጅ ፓቨል ዱሮቭ ፍርድ ቤት ቀርቧል። ፍርድ ቤት በ5 ሚሊዮን ዩሮ ወይም 5.56 ሚሊዮን ዶላር ዋስ ተለቆ ጉዳዩን እንዲከታተል ወስኖለታል። ከፈረንሳይ እንዳይወጣ ግን ታግዷል። እገዳው ተጨማሪ ምርመራ ስለሚደረግ ነው የተጣለው። በሳምንት ሁለት ጊዜ ለፖሊስ ሪፖርት ማድረግ እንዳለበት ተገልጿል። ዱሮቭ ከቀናት በፊት ፓሪስ አቅራቢያ ኤርፖት ተይዞ…
#Telegram

የቴሌግራም መስራች እና ዋና ስራ አስፈጻሚ ፓቨል ድሮቭ ፓሪስ ውስጥ ታስሮ በዋስ ከተለቀቀ በኃላ ለመጀመሪያ ጊዜ ይፋዊ አስተያየት ሰጥቷል።

ዱሮቭ ምን አለ ?

አብረውት ለነበሩትና ለደገፉትና ፍቅራቸውን ላሳዩት ሁሉ ምስጋና አቅርቧል።

ባለፈው ወር ፓሪስ በደረሰ ወቅት 4 ጊዜ በፖሊስ ኢንተርቪው ተደርጎ እንደነበር ገልጿል።

በዚህ ወቅት የፈረንሳይ ባለስልጣናት ከቴሌግራም ምላሾችን ስላላገኙ ምናልባትም ለሌሎች ሰዎች ህገወጥ የቴሌግራም አጠቃቀም በግል ዱሮቭ ተጠያቂ እንደሚሆን እንደተነገረው አመልክቷል።

ይህ ግን በብዙ ምክንያቶች አስገራሚ እንደነበር አስረድቷል።

- ቴሌግራም የአውሮፓ ህብረት ጥያቄዎችን የሚቀበል እና የሚመልስ በአውሮፓ ህብረት ውስጥ ኦፊሴላዊ ተወካይ አለው። ይፋዊ ኢሜልም አለው።

- የፈረንሳይ ባለስልጣናት እርዳታ ለመጠየቅ ዱሮቭን ለማግኘት ብዙ መንገዶች ነበሯቸው። እንደ አንድ የፈረንሳይ ዜጋ በዱባይ በሚገኘው የፈረንሳይ ቆንስላ ተደጋጋሚ እንግዳም ነበር። ከጥቂት ጊዜ በፊት ደግሞ በግሉ በፈረንሳይ ያለውን የሽብርተኝነት ስጋት ለማስወገድ ከቴሌግራም ጋር የስልክ መስመር እንዲፈጥሩ ረድቷቸዋል።

- አንድ ሀገር በኢንተርኔት አገልግሎት ላይ ደስተኛ ካልሆነ በራሱ በአገልግሎቱ ላይ ህጋዊ እርምጃ መጀመር ነው። ከቅድመ ስማርት ስልክ በፊት የነበረ ህግ አምጥቶ በመተግበሪያው ላይ በሶስተኛ ወገኖች ለሚሰራ ወንጀል የድርጅት ስራ አስፈጻሚን ተጠያቂ ማደረግ ትክክለኛ አካሄድ አይደለም። ቴክኖሎጂን መገንባት በራሱ ከባድ ነገር ነው። ማንም ኢኖቬተር ሌሎች አላግባብ ለሚጠቀሙት አጠቃቀም እሱ በግሉ እንደሚጠየቅ ካወቀ አዲስ ነገር አይፈጥርም።

በግላዊ መረጃ እና በደህንነት መካከል ትክክለኛውን ሚዛን መፍጠር እንዲሁ ቀላል እንዳልሆነ ዱሮቭ ገልጿል።

አንዳንድ ጊዜ ይህን ሚዛን በመጠበቅ ጉዳይ ከሀገራት ተቆጣጣሪዎች ጋር መግባባት ሳይፈጠር ሲቀር ቴሌግራም ሀገራቱን ለቆ እንደሚወጣ አመልክቷል። ይህንን ብዙ ጊዜ እንዳደረገ ገልጿል።

ለአብነት ፦ ሩስያ ለስለላ " የኢንክሪፕሽን ቁልፎችን " መጠየቋን ተከክሎ ቴሌግራም አልሰጥም በማለቱ ሩስያ ውስጥ ቴሌግራም ታግዷል።

ኢራን የሰላማዊ ሰልፎችን ቻናሎች ብሎክ እንዲደረግላት ጠይቃ ቴሌግራም " አላደርገውም አይቻልም " በማለቱ ኢራን ውስጥ ታግዷል።

ዱሮቭ ምስራዎች የሚሰሩት ለገንዘብ ባለመሆነ ከቴሌግራም መርህ ጋር የማይሄድን ገበያ ለቆ ለመውጣት ሁሌም ዝግጁ እንደሆነ ገልጿል።

ይህ ሁሉ ማለት ግን ቴሌግራም ፍጹም ነው ማለት እንዳልሆነ ዱሮቭ አመልክቷል።

የመንግሥት አካላት / ባለስልጣናት ጥያቄያቸውን የት መላክ እንዳለባቸው ግራ ይግባሉ ይህንን ማስተካከል አለብን ብሏል።

ነገር ግን በአንዳንድ ሚዲያዎች ቴሌግራም የስርዓት አልበኞች መፈንጫ ተደርጎ የሚቀርበው ፍጹም ሀሰተኛ ነው ሲል ገልጿል።

" በየቀኑ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ጎጂ ፖስቶችን እና ቻናሎችን እናስወግዳለን " ያለው ዱሮቭ በየዕለቱ ግልጽነት መፍጠሪያ ሪፖርቶችም እንልካለን ብሏል።

መንግሥታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች (NGOs) ጋር አስቸኳይ የሞደሬሽን ጥያቄዎችን በፍጥነት ለማስተናገድም የቀጥታ ስልክ መስመሮችም አሉን ሲል አክሏል።

" ሆኖም ግን ይህ በቂ አይደለም የሚሉ ድምፆችን እንሰማለን " ያለው ዱሮቭ " የተጠቃሚዎች ብዛት ወደ 950 ሚሊዮን መድረስ ወንጀለኞች የእኛን መድረክ አላግባብ ለመጠቀም ቀላል አድርጎላቸዋል። በዚህ ረገድ ያሉ ነገሮችን በከፍተኛ ሁኔታ ማሻሻል የግል ግቤ አድርጊያለሁ " ብሏል።

ይህ ሂደት በውስጥ በኩል መጀመሩን ጠቁሞ በቀጣይ ስላለው ሁኔታ ተጨማሪ ዝርዝር ጉዳዮች በቅርቡ ይፋ እንደሚደረጉ አሳውቋል።

ያለፈው ወር ክስተት ቴሌግራም እና የማህበራዊ አውታረመረብ ኢንዱስትሪን በጠቅላላ ደህንነቱ የተጠበቀና ጠንካራ እንደሚያደርገው ተስፋ እንዳለው ዱሮቭ ገልጿል።

#TikvahEthiopia
#Telegram

@tikvahethiopia
Forwarded from Ethio telecom
🎉🌼 የአዲስ ዓመት ዕንቍጣጣሽ ጨዋታ ብዙዎችን በሽልማት እያንበሸበሸ ነው!!

🧩 ገና አልተነካም በቴሌብር ሱፐርአፕ ፊደላትን በመገጣጠም እስከ 100,000 ብር ይሸለሙ!

💡ቴሌብር ሱፐርአፕን ለወዳጅ መጋበዝ፣ ገንዘብ መላክ፣ የአየር ሰዓትና ጥቅል መግዛት፣ ግብይት መፈጸም እንዲሁም የቴሌኮም ቢል መክፈል ተጨማሪ ዕድሎችን ያስገኝልዎታል፡፡

🎁 ሙሉ ''2017 እንቁጣጣሽ’' የሚለውን ቃል ሲያገናኙ ለዕጣ ሽልማት ብቁ ይሆናሉ!

🔗 ቴሌብር ሱፐርአፕ https://onelink.to/uecbbr እስካሁን ከሌለዎት አሁኑኑ ይጫኑና ወደ ጨዋታው ይግቡ!

🗓 እስከ መስከረም 1 ቀን 2017 ዓ.ም

ቴሌብር - እጅግ ቀላል፣ ፈጣን፣ ምቹ እና አስተማማኝ!

#Ethiotelecom #telebirr #telebirrSupperApp #DigitalEthiopia #DigitalAfrica #RealizingDigitalEthiopia
#የቴክኖ የአዲስ ዓመት ልዩ የበዓል ስጦታ!

የአዲስ አመት ልዪ ስጦታ ከቴክኖ ሞባይል ኢትዮጵያ፣ ከየትኛውም የቴክኖ ሱቅ የቴክኖ ስማርት ስልክን ሲገዙ አብሮት ካለ ወዳጅ ዘመድ ወይም ጓደኛ ጋር ፎቶ በመነሳት የማህበራዊ ገጾት ላይ በመለጠፍ እና ብዙ ላይክ በማግኘት የዱባይ ደርሶ መልስ የቢዝነስ ክላስ የአውሮፕላን ትኬት፣ ላፕቶፖች፣ የቴክኖ ስማርት ስልኮችን እና ገደብ አልባ የኢንተርኔት ፓኬጆችን ይሸለሙ፡፡

የውድድሩ መመሪያ
1. የቴክኖ ኢትዮጵያን ፌስ ቡክ ፣ ኢንስታግራም እና ቲክቶክ ገጾችን ፎሎው ያድርጉ፡፡
2. የተነሱትን ፎቶ በመረጡት ማህበራዊ ሚዲያ ሲለጥፉ የቴክኖ ኢትዮጵያን ገፅ ከፖስቶት ጋር ታግ ያድርጉ፡፡ ብዙ ላይክ እና ኢንጌጅመንት ያገኘው ተሸላሚ ይሆናል፡፡
- Tag ሲያደርጉን ለ Facebook @ TecnoEt ፣ ለ Instagram @ TecnoMobileEthiopia እና ለ TikTok @ TecnoEt ን  ሜንሽን ማድረግ እንዳይረሱ።)
- በተጨማሪም #TecnoEt2017 ን keyword መጠቀም እንዳይረሱ)
TIKVAH-ETHIOPIA
#AAU #GAT አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በተቋሙ የድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (GAT) መስከረም 3/2017 ዓ.ም እንደሚሰጥ አሳውቋል፡፡  በተቋሙ የሚሰጠውን ፈተና ለመውሰድ የአመልካቾች ምዝገባ ከዛሬ ነሐሴ 30/2016 ዓ.ም እስከ መስከረም 1/2017 ዓ.ም ይከናወናል ተብሏል፡፡ Via @tikvahuniversity
#MoE

ሀገር አቀፍ የድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ለመውሰድ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲን እንደ ፈተና ማዕከል መርጣችሁ ለነበራችሁ ተፈታኞች ፈተናው ለሌላ ጊዜ መተላለፉን ትምህርት ሚኒስቴር ማሳወቁ ይታወሳል፡፡

"ዩኒቨርሲቲው በእድሳት ላይ በመሆኑ" የፈተና ማዕከል መቀየር አስፈላጊ ሆኖ መገኘቱን የገለፀው ሚኒስቴሩ፤ ፈተናው መስከረም 3 እና 4/2017 ዓ.ም በሚከተሉት ሰባት ተቋማት ውስጥ እንደሚሰጥ አሳውቋል፦

1. በኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ፣
2. በኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ፣
3. በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ፣
4. በፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኢንስቲትዩት፣
5. በኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርስቲ፣
6. በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና
7. በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ሜዲካል ኮሌጅ፡፡

የተሰጣችሁን የመፈተኛ ስም (Username) ተጠቅማችሁ በሚደርሳችሁ የመፈተኛ ማዕከል እና የፈተና ሰዓት (Exam Session) መሰረት ፈተናውን እንድትወስዱ ሚኒስቴሩ አሳስቧል፡፡

(ፈተናው የሚሰጠበት ፕሮግራም ከላይ ተያይዟል፡፡)

Via @tikvahuniversity
አንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ መጪውን የ2017 አዲስ ዓመት በዓል ምክንያት በማድረግ ልዩ ልዩ ሽልማቶችን የሚያስገኝ የጥያቄና መልስ ውድድር ይዞላችሁ መጥቷል፡፡

እርስዎም የሽልማቱ ተሳታፊ ለመሆን ከታች ያሉትን የባንኩን ይፋዊ የቴሌግራም እና የፌስቡክ ገፆች በመቀላቀል እና ጥያቄውን ቀድመው በመመለስ ሽልማቶችን የራስዎ ያድርጉ፡፡

ጥያቄው የሚካሄዳው ማክሰኞ ጳጉሜን 5 ቀን 2016 ከቀኑ 8:00 ሰዓት ሲሆን ፤ ጥያቄውን ለመለሱ 5 ተሳታፊዎች ሊሸልም ዝግጅቱን ጨርሷል።

ከአንድ እስከ አምስት ለወጡ ተወዳዳሪዎች የተለያዩ ሽልማቶችን አዘጋጅቶ ይጠብቃችኋል።

እርስዎም ለወዳጅ ዘመድዎ በማጋራት የውድድሩ ተሳታፊ ይሁኑ!!
ደንብና ሁኔታዎች ተፈፃሚ ይሆናሉ፡፡
[Telegram] [Facebook]

አንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ
የስኬትዎ አጋር!
TIKVAH-ETHIOPIA
#OLF " ለ4 ዓመታት ያህል በግፍ ታስረው የቆዩት የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) አመራሮች ከእስር መለቀቃቸውን " የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ አመራር አቶ ጃዋር መሀመድ አወደሱ። ፖለቲከኛው ፥ በአመራሮቹ መፈታት እጅጉን እንደተደሰቱ ገልጸዋል። " መንግስት የቀሩትን የፖለቲካ እስረኞች በመፍታት የትጥቅ ግጭቶችን ሁሉ በውይይት እንዲቆሙ በማድረግ ይህንን በጎ እርምጃ ማሳደግ ይኖርበታል " ብለዋል።…
#OLF #OFC

የኦፌኮ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጡሩነህ ገምታ ከእስር የተፈቱትን የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) ከፍተኛ አመራሮች በአካል በማግኘት " እንኳን በሰላም ከእስር ተፈታችሁ ! " በማለት በኦፌኮ ስም ደስታቸውን ገልፀዋል።

አቶ ጥሩነህ " በተለያዩ እስር ቤቶች በህገ ወጥ መንገድ የታሰሩ የፖለቲካ እስረኞች እንዲፈቱ ደጋግመን እየጠየቅን ነበር " ብለዋል።

" የኦሮሞ ታጋዮች አቋምና ድጋፍ እንዲሁም በኦፌኮ እና በOLF ድርጅቶች መካከል ያለው ትብብር ለአገር ድል ወሳኝ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ፕሮፌሰር እንድርያስ እሸቴ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ፕሬዝዳት ፕሮፌሰር አንድርያስ እሸቴ ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ዛሬ ነሐኔ 23 ቀን 2016 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። @tikvahethiopia
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ፕሬዝዳንት እና በጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት አማካሪ ሚኒስትር ሆነው ያገለገሉት የፕሮፌሰር አንድርያስ እሸቴ የቀብር ስንስርዓት እሁድ ጷጉሜን 3/2016 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ሰዓት በመንበረ ፀባዖት ቅድስት ስላሴ ካቴድራል ቤተክርስትያን ይፈፀማል።

በዕለቱ ከጠዋቱ 4:00-6:00 ሰዓት ባስተማሩበትና በሰሩበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ዋና ግቢ ራስ መኰንን አዳራሽ የስንበት ስነ-ስርዓትም የሚከናወን ይሆናል።

#AAU

@tikvahethiopia
2024/09/30 18:25:29
Back to Top
HTML Embed Code: