Telegram Web Link
#Tecno
ቴክኖ በአይነቱ አዲስ የሆነ እና ሶስት ጊዜ የሚታጠፍ PHANTOM ULTIMATE 2 የተሰኘ የስልክ ዲዛይን ንድፈ ሀሳብን ይፋ አድርጓል፡፡  ይህ የስልክ ዲዛይን ንድፈ ሃሳብ በአለም ገበያ ላይ ከሚገኙ ታጣፊ ስልኮች ቀጭን ዲዛይን ያለው ሲሆን ስልኩ ሶስት ጊዜ የመታጠፍ ብቃት ሲኖረው 11 ሚሊ ሜትር ውፍረት ብቻ  እንዲኖረው ሆኖ ዲዛይን ተደርጓል፡፡

PHANTOM ULTIMATE 2  ሲታጠፍ 6 ነጥብ 48 ኢንች ሙሉ በሙሉ ሲዘረጋ ደግሞ 10 ኢንች የስክሪን ስፋት ይኖረዋል ከዚህ ባለፈም ሁለት ስራዎችን እንደ አንድ ለመከወን እና የተለያዩ ቋንቋዎችን ለመተርጎም የሚያስችል ብቃትም አለው፡፡

ይህ የስልክ ዲዛይን ንድፈ ሃሳብ በቅርብ ለአለም ገበያ ይፋ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#AAU #GAT

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በተቋሙ የድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (GAT) መስከረም 3/2017 ዓ.ም እንደሚሰጥ አሳውቋል፡፡ 

በተቋሙ የሚሰጠውን ፈተና ለመውሰድ የአመልካቾች ምዝገባ ከዛሬ ነሐሴ 30/2016 ዓ.ም እስከ መስከረም 1/2017 ዓ.ም ይከናወናል ተብሏል፡፡

Via @tikvahuniversity
#Ethiopia ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነጻ የሚሆነውን የኤሌክትሪክ እና የውሀ ፍጆታ መጠን ለመወሰን የወጣ መመሪያ ቁጥር 1021/2016 ከላይ ተያይዟል።

#MinistryofFinance

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#OLF 🇪🇹 የፓለቲካ ፓርቲዎች ምን ይላሉ ? 🇪🇹 “ መንግስት በተለዬ መልኩ ጫና እያደረሰብን ነው ” ሲል የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ፓርቲ ወቀሰ። ፓርቲው ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጋር ቆይታ አድርጓል። በዚህም በወቅታዊ እና በአገራዊ ጉዳዮች እንደ ፓርቲ ያለውን ግምገማና የመፍትሄ ሀሳብ አጋርቷል። Q. ስለ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን የፓርቲው ግምገማ ምንድን ነው ? ኦነግ ፦ የአገራዊ ምክክር…
ፎቶ ፦ ባለፉት አራት አመታት እስር ላይ የነበሩት የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) ከፍተኛ አመራሮች ዛሬ ተለቀዋል።
➡️ አብዲ ረጋሳ፣
➡️ ሚካኤል ቦረን፣
➡️ ኬነሳ አያና፣
➡️ ለሚ ቤኛ፣
➡️ ዶክተር ገዳ ኦልጅረ፣
➡️ ገዳ ገቢሳና ዳዊት አብደታ ዛሬ ማምሻውን ከእስር ቤት በዋስ መለቀቃቸውን የግንባሩ ህዝብ ግንኙነት ሃላፊ የሆኑት አቶ ለሚ ገመቹ ለኦኤምኤንገልፀዋል።

#OMN

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ፎቶ ፦ ባለፉት አራት አመታት እስር ላይ የነበሩት የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) ከፍተኛ አመራሮች ዛሬ ተለቀዋል። ➡️ አብዲ ረጋሳ፣ ➡️ ሚካኤል ቦረን፣ ➡️ ኬነሳ አያና፣ ➡️ ለሚ ቤኛ፣ ➡️ ዶክተር ገዳ ኦልጅረ፣ ➡️ ገዳ ገቢሳና ዳዊት አብደታ ዛሬ ማምሻውን ከእስር ቤት በዋስ መለቀቃቸውን የግንባሩ ህዝብ ግንኙነት ሃላፊ የሆኑት አቶ ለሚ ገመቹ ለኦኤምኤንገልፀዋል። #OMN @tikvahethiopia
#OLF

" ለ4 ዓመታት ያህል በግፍ ታስረው የቆዩት የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) አመራሮች ከእስር መለቀቃቸውን " የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ አመራር አቶ ጃዋር መሀመድ አወደሱ።

ፖለቲከኛው ፥ በአመራሮቹ መፈታት እጅጉን እንደተደሰቱ ገልጸዋል።

" መንግስት የቀሩትን የፖለቲካ እስረኞች በመፍታት የትጥቅ ግጭቶችን ሁሉ በውይይት እንዲቆሙ በማድረግ ይህንን በጎ እርምጃ ማሳደግ ይኖርበታል " ብለዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" የተፈጠረው ልዩነት ያለ ግጭት እንዲፈታ እንሰራለን " - አቶ ጌታቸው ረዳ

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ " ያሉት ልዩነቶች ያለ ግጭት እንዲፈቱ እንሰራለን " ብለዋል።

ይህን ያሉት ዛሬ ማይጨው ከተማ ህዝባዊ ውይይት ባደረጉበት ወቅት ነው።

አቶ ጌታቸው የሚመሩትና ጄነራል ጻድቃን ገ/ትንሳኤ ያሉበት የከፍተኛ አመራሮች ቡድን ከሰሞኑን በትግራይ እየተንቀሳቀሰ ህዝባዊ ውይይት እያደረገ ነው።

ከቀናት በፊትም በዓዲግራት ውይይት አድርጎ ነበር።

ዛሬ ደግሞ በማይጨው ከተማ ህዝባዊ ውይይት አድርጓል።

አመራሮቹ ወደ ማይጨው ባደረጉት ጉዞ በየመንገዱ ህዝቡ እየወጣ ተቀብሏቸዋል ፤ ማይጨው ላይም ከፍተኛ የሰው ቁጥር በአጀብ ተቀብሏቸዋል።

ከህዝብ ጋር ባደረጉት ውይይት የተለያዩ ጉዳዮች ተነስተው ነበር።

ነዋሪዎች ምን አሉ ?

- በአመራሮች መካከል የተፈጠረው ልዩነት ህዝቡን ይከፋፍላል ስለዚህ በአስቸኳይ መቆም አለበት።
- በአመራሮች መካከል የተፈጠረው እኔ ከሞትኩ ስርዶ አይብቀል ዓይነት አካሄድ ይቁም።
- በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት መሰረት ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው ይመለሱ ፤ የተመለሱት ክትትልና ድጋፍ ይደረግላቸው።
- አመራሮች ሰላም ቀዳሚ የህዝብ ምርጫ መሆኑ ሊረዱና ሊያስቀጥሉ ይገባል።
- በዲፕሎማሲ እንጂ በአፈሙዝ አይመራም።
- የትግራይ ሉግዛት የማስከበር ጉዳይ ችላ መባል የለበትም።
- የሚታዩ የፀጥታ ስጋቶች የሚቀርፍ ቀጣይ ስራ ይሰራ።
- ፍትህ እየተጓደለ ነው ፤ በፍርድ ቤቶች ፍትህና የህግ የበላይነት እንዲረጋገጥ ከወገንተኝነት በፀዳ መልኩ ይሰራል። 
- በሴቶች የሚደርሰው ጥቃት ይቁም።
- የሰማእታት ቤተሰቦች ትኩረት ይደረግላቸው።
- አቅም ያላቸው ሰዎች ወደ አመራር ይወጡ። - ተጀምረው የተቋረጡ መሰረተ ልማቶች ይቀጥሉ።
- ህገወጥ የወጣቶች ፍልሰት የሚከላከል መንግስታዊ እንቅስቃሴ በአስቸኳይ ተግባራዊ ይሁን።
- ከአግባብ ውጭ በሙስናና ህገ-ወጥ መንገድ ለኢንቨስትመንት ማስፋፍያ ተብሎ የሚሰጥ መሬት ይቁም ... ሲሉ አሳስበዋል። 

ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ ፤ የህወሓት ህጋዊነት ለህዝብ በሚመጥንና የፕሪቶሪያ ውል በሚያስከብር መልኩ ለመመለስ እንደሚሰሩ ገልፀዋል። 

እርሳቸው በሚመሩትና በዶ/ር ደብረፀዮን በሚመራው ህወሓት መካከል የተፈጠረው ልዩነት ያለ ግጭት እንዲፈታ እንደሚሰሩ ገልጸዋል።

" ከዚህ ውጭ የፕሪቶሪያ ውል ለማፍረስ የሚደረግ ማንኛውም እንቅስቃሴ ጦርነትን መጥራት መሆኑ ሊታወቅ ይገባዋል " ሲሉ አስጠንቅቀዋል።

" የተፈጠረው ልዩነት በሰላማዊ መንገድ እንዲፈታ ከማድረግ ጎን ለጎን ተፈናቃዮች በአጭር ጊዜ ወደ ቄያቸው እንዲመለሱ እናደርጋለን " ሲሉ አክለዋል።

ፎቶ፦ ድምጺ ወያነ

@tikvahethiopia 
#አንበሳ_ኢንተርናሽናል_ባንክ

አንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ መጪውን የ2017 አዲስ ዓመት በዓል ምክንያት በማድረግ ልዩ ልዩ ሽልማቶችን የሚያስገኝ የጥያቄና መልስ ውድድር ይዞላችሁ መጥቷል፡፡

እርስዎም የሽልማቱ ተሳታፊ ለመሆን ከታች ያሉትን የባንኩን ይፋዊ የቴሌግራም እና የፌስቡክ ገፆች በመቀላቀል እና ጥያቄውን ቀድመው በመመለስ ሽልማቶችን የራስዎ ያድርጉ፡፡

ጥያቄው የሚካሄዳው ማክሰኞ ጳጉሜን 5 ቀን 2016 ከቀኑ 8:00 ሰዓት ሲሆን ፤ ጥያቄውን ለመለሱ 5 ተሳታፊዎች ሊሸልም ዝግጅቱን ጨርሷል።

ከአንድ እስከ አምስት ለወጡ ተወዳዳሪዎች የብር ሽልማቶን አዘጋጅቶ ይጠብቃችኋል።

እርስዎም ለወዳጅ ዘመድዎ በማጋራት የውድድሩ ተሳታፊ ይሁኑ!!

ደንብና ሁኔታዎች ተፈፃሚ ይሆናሉ፡፡

https://linktr.ee/anbesabank

አንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ
የስኬትዎ አጋር!
2024/09/30 20:21:21
Back to Top
HTML Embed Code: