Telegram Web Link
Zero One Zero One Tech & Entrepreneurship, in partnership with #BluLabs and #CreativeHub Ethiopia, presents the Summer Success Bootcamp.

✅️ Learn coding (Scratch & Web Development) while fostering an entrepreneurial mindset. Parents can attend too!

If you're registered, you have the option to either offer a free spot to someone in need or bring a sibling and register two people for the price of one spot.

Join us at Creative Hub Ethiopia from #July_22 to #August _2, 2024. Morning and afternoon sessions available for youth aged 13 - 21.

Limited spots—price: 7,999 Birr. Secure your spot here.

📲 Scan the QR code or click this link: https://0101-te.com/bootcamp-reg/ to secure your spot.
#SafaricomEthiopia

የሙዚቃ ተሰጥዖችንን እናሳይ እንጂ?! የ1፟ደቂቃ መወዳደሪያ ሙዚቃችንን እያቀነቀንን ዛሬውኑ ውድድሩን እንቀላቀል! የተደበቀ ተሰጦአችንን ወደ አደባባይ እንጂ?!  ቪዲዮአችንን አሁኑኑ ወደ TikTok እንላክ!

የዲጂታል ሙዚቃ ውድድርን ለመቀላቀል፡
🎥 የአንድ ደቂቃ የራሳችን ሙዚቃ ቪዲዮ በTikTok ላይ እንፖስት
🏷 #1Wedefit እና #የምትኖሩበትከተማ አድራሻ ማስገባት እንዳንረሳ
📲የTikTok ደረገጽ @Safaricomet ታግ እናድርግ

እንዝፈን! እንላክ! እናሸንፍ!

መልካም ዕድል!
#ኬንያ

ባለፈው ሳምንት በኬንያ፣ ናይሮቢ አንድ ፖሊስ ጣቢያ አቅራቢያ በሚገኝ የቆሻሻ መጣያ ስፍራ የተቆራረጠ የሴቶች አካል በማዳበሪያ ተጥሎ ተገኝቷል።

የተቆራረጠው የሴቶች አካል ከተገኘ በኋላም ከ40 በላይ ሴቶችን መግደሉን ያመነ ግለሰብ መያዙን የኬንያ ፖሊስ ዛሬ አስታውቋል።

ባለቤቱን ጨምሮ 42 ሴቶችን መግደሉን ያመነው የ33 ዓመት ተጠርጣሪ የተያዘው በአሰቃቂ ሁኔታ የተገደሉ ቢያንስ የ8 ሴቶች አስከሬን ከተገኘ በኋላ ነው።

ኮሊንስ ካሃሊሲአ የተባለው ይኸው ተጠርጣሪ እኤአ 2022 ጀምሮ ሴቶችን ብቻ እየለየ ሲገድል እንደቆየ ቃሉን መስጠቱን የኬንያ ፖሊስ አስታውቋል።

ተጠርጣሪው በሰጠው ቃል " ውብ የሆኑ ሴቶችን " መግደል እንደሚመርጥ ጨምሮ ተናግሯል።

የወንጀል ምርመራ ዳይሬክቶሬት " ለሰው ልጅ ሕይወት ምንም ደንታ የሌለው ተጠርጣሪን በቁጥጥር ስር አውለናል " ብሏል።

ፖሊስ እንደሚለው ከሆነ ተጠርጣሪውን በቁጥጥር ስር ያዋለው ከገደላቸው ሴቶች ከአንዷ ሞባይል ወደራሱ ስልክ ገንዘብ ከላከ በኋላ ነው።

ተጠርጣሪው ኮሊንስ የሚኖረው የሴቶቹን አስክሬን ሲጥል ከነበረበት የቆሻሻ መጣያ ስፍራ 500 ሜትር ርቀት ላይ ነው።

የዚህ ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር መዋል የተሰማው ባለፉት ቀናት ከቆሻሻ መጣያው ስፍራ የበርካታ ሴቶች የተቆራረጡ አካላት በማዳበሪያ ተጥሎ ከተገኘ በኋላ ነው።

የተገደሉት ሴቶች እድሜያቸው ከ18 እስከ 30 ሲሆን ሁሉም በተመሳሳይ መንገድ ነው የተገደሉት።

ግለሰቡ ወንጀሉን ለምን እንደፈጸመ ፖሊስ እያጣራ ሲሆን የአስክሬን ምርመራም እየተደረገ ይገኛል።

መረጃው የቢቢሲ ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ተጠርጣሪዎችን የመያዝ ኦፕሬሽን መጀመሩ ተሰማ።   በተለያዩ ህጋዊ ያልሆኑ ተግባራት የተሳተፉ አካላት እና ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር ማዋል መጀመሩን ጊዚያዊ አስተዳደሩ አሳውቋል። በትግራይ ከጊዜ ወደ ጊዜ ለመንግስት እና ለህዝብም ድህንነት አስጊ የሆኑ ኢ-ህጋዊ ተግባራት እየተበራከቱ መምጣታቸውን አስተዳደሩ አመልክቷል። ይህን ለመቆጣጠር ኮሚቴዎችን አቋቁሞ በማጣራት…
#Mekelle

መቐለ ከተማ ውስጥ በሚገኙ 14 የመኪና የማደሪያ ቦታዎች (ፓርክ የሚደረግበት) 140 ባለቤትነታቸው ያልታወቁ ተሽከርካሪዎች ማግኘቱ የመቐለ ከተማ ፓሊስ ፅሕፈት ቤት አስታውቋል።

ፖሊስ በመቐለ ከተማ የመኪና ማደሪዎች ድንገተኛ ፍተሻ አድርጎ ነበር።

በዚህም140 ባለቤታቸው ያልታወቁ ተሽከርካሪዎች ሊገኙ እንደቻሉ ገልጿል።

የተገኙት ተሽከርካሪዎች ባለቤትነታቸው ለማወቅ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር የማጣራት ስራ እየተሰራ እንደሆነ አመልክቷል።

" ባለንብረት ነኝ " የሚል አካል ማረጋገጫ ማስረጃ ይዞ መቅረብ ይችላል ተብሏል።

የመቐለ ፓሊስ ከተሽከርካሪ ፣ ብረታብረትና ሌሎች ንብረቶች ጋር ተያይዞ የማጣራት ስራ በመስራት ላይ እንደሆነ ገልጿል።

የሚካሄደው ምርመራ ግኝቶች በየጊዜው ለህዝብ ይፋ እንደሚያደርግ አረጋግጧል።

የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ሐምሌ 4 ባወጣው መግለጫ በክልሉ በቀላል እና ከባባድ ወንጀሎች ተሳትፈዋል ያላቸው ግለሰቦች በቁጥጥር ስር የማዋል ኦፕሬሽን መጀመሩ መግለፁ መዘገባችን ይታወሳል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia            
 
TIKVAH-ETHIOPIA
🔈#የኢትዮጵያ_ቃለ_ሕይወት_ቤተክርስቲያን በኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን የኩሪፍቱ ማዕከል ይዞታ ላይ በቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት እየተወሰደ ነው ያለችው ሕገወጥ እርምጃ እንዲቆም የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ጥሪ አቅርባለች። ቤተክርስቲያኗ በዛሬው ዕለት ስለጉዳዩ ሰፋ ያለ ዝርዝር መግለጫ ልካልናለች። ከመግለጫው መካከል ፦ " በቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ እየተካሄደ…
#Update

“ ሃያ (20) ሄክታሩን አጥረውታል። መጋዘኖችንም እያፈረሷቸው ነው። ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ እንገደዳለን ” - ቤተክርስቲያኗ

የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን፣ 40 በመቶ የሚሆን የኩሪፍቱ ማዕከል ይዞታዋን የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ‘ በጉልበት ሊወስደው ነው ’ ስትል ከሰሞኑን በተደጋጋሚ መግለጫ መስጠቷ ይታወቃል።

ጉዳዩ ከምን ደረሰ ?

ቤተ ክርስቲያኗ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠችው ቃል ፣ “ 20 ሄክታሩን አጥረውታል። መጋዘኖችን እያፈረሷቸው ነው። ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ እንገደዳለን ” ብላለች።

“ ዛሬ (ሰኞ ሐምሌ 8 ቀን 2016 ዓ/ም) ግቢ ውስጥ ገብተው በጉልበት አጥረውታል። መሳሪያ በያዙ ሰዎች እያስጠበቁት ነው ያሉት ” ስትል ገልጻለች።

ይህንን ያሉት አንድ የቤተ ክርስቲያኗ አካል ፣ “ እኛም ዛሬ ለጠቅላይ ሚኒስቴሩም፣ ለኦሮሚያ ክልል ከፍተኛ አመራሮችም ደብዳቤ እየላክን ነው ” ብለዋል።

“ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ጠዋት ነው የላከነው፣ ለአቶ ሽመልስ አብዲሳም ልከናል። ገና ምንም የሰጡት ምላሽ የለም ” ሲሉ አክለዋል።

“ 40 በመቶ ገደማ ይዞታችን ነው ይወሰዳል የተባለው ” ያሉት እኝሁ አካል፣ “ አሁን ግማሹን አጥረዋል። ለሁለት ግለሰቦች ነው ይሰጣል የተባለው ” ነው ያሉት።

በተጨማሪ ፣ በፍርድ ቤትም እግድ እንዲያወርድላቸው እንደጠየቁ፣ የሚጠብቁት ያስገቡትን ደብዳቤ ምላሽ እየጠበቁ እንደሆነ ገልጸዋል።

“ አስቸኳይ ምላሽ የማይሰጠን ከሆነ ሰላማዊ ሰልፍ ወደ መጥራት የምናመራ ይሆናል። በሰላማዊ መንገድ ድምፃችንን እናሰማለን። ሁል ጊዜ ቤተ ክርስቲያን የምትቆመው ከሰላም ጎን ነው። የመረበሽ የማስረበሽ ዓላማ የላትም ” ብለዋል።

ቅሬታ የቀረበበት የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ አልሆነም። ሆኖም በቀጣይ ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ ከሆነ ምላሹን የምናቀርብ ይሆናል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
🔈 #ተጠንቀቁ ወደ ተለያዩ ውጭ ሀገራት " ስራ ነው " በሚል ፕሮሰስ እያደረጋችሁ ያላችሁ ወጣቶቻችን የትም ሀገር ይሁን የምትሄዱት ስራው ምን እንደሆነ እና ለደህንነታችሁም አስተማማኝ መሆኑን አረጋግጡ። " ለስራ ውጭ እንላካችሁ " የሚሉትን ደላሎችንም ሆነ ኤጀንሲዎች ፦ - ስራው ምንድነው ? - በትክክል ድርጅቱ ያለበት ሀገር የት ነው ? - የድርጅቱን ህጋዊነት የሚያሳይ ማስረጃ አሳዩን ! - ባለበት…
🔈#ይነበብ

ወጣቶችን ወስደው ምንድነው የሚያሰሯቸው ?

በኦንላይን ወይም በደላሎች አልያም በኤጀንሲዎች " እዚህ ሀገር ጥሩ ስራ አለ ፤ ክፍያውም ከፍ ያለነው " ተብለው ብዙ ወጣቶች ከተለያዩ ሀገራት ይዘዋወራሉ።

ለአብነት ያህል ወጣቶች ከሚዘዋወሩባቸው ሀገራት መካከል የሳይበር ማጭበበር ( Cyber Scam) ማዕከላት ተብለው ወደ ሚታወቁት ፦
• ማይናማር ፣
• ካምቦዲያ፣
• ላኦስ
• ማይናማር ታይላንድ ድንበር
• ቻይና ማይናማር ድንበር በዋነኝነት ይጠቀሳሉ።

እነዚህ አካባቢዎች ባሉ የተለያዩ ቦታዎች በኦንላይን ማጭበርበር ላይ የተሰማሩ በርካታ ድርጅቶች አሉ።

በእርግጥ መጀመሪያ ላይ ወጣቶቹን " እልካችኋለን " የሚሏቸው ሌሎች በኢኮኖሚና ደህንነት እጅግ ጠንካራ ፣ ጠንካራ ባይሆኑም እንኳን ያን ያህል የከፋ ሁኔታ ላይ ወደማይገኙ ሀገራት ነው።

እዛ ቦታ ከደረሱ በኋላ ግን የሚልኳቸው ወደ ጎረቤት ድሃ እና የህግ ስርዓት ወዳልጠነከረባቸው ሀገራት ይሆናል።

የሚሰራው ማጭበርበር ምንድነው ?

ስራ ብለው የሚልኳቸው መጀመሪያ ፦
- የኦላንይ ግብይት ስራ ማቀላጠፍ
- የኦንላይን ሴልስ ስራ
- የሆቴል እንግዳ ተቀባይ
- የማርኬቲንግ ስራ ... ሌላም ሌላም ነው።

ነገር ግን ስራ አለበት ወደ ተባለው ስፍራ ሲሄዱ የሚሰሩት ስራ መጀመሪያ ላይ ከተነገራቸው ተቃራኒ ነው።

የየራሳቸው ጋንግ አለቆች ባላቸው እጃቸውም ረጅም በሆኑ ሰዎች በሚመሩ የማጨበርበር ተግባር ላይ ወደ ተሰማሩ ድርጅቶች ያስገቧቸዋል።

እነዚህ ሰዎች ስልክ / ኮምፒየተር የሚያቀርቡላቸው ሲሆን በዛም ዓለም አቀፍ የማጨበርበር ስራ ላይ ያሰማሯቸዋል።

🔴 ዴቲንግ 🔴

የመጀመሪያ ስራቸው ከኢንተርኔት ላይ ውብ የሆኑ ሴቶችን / ስኬታማ ሴቶችን / ስኬታማ ወንዶችን ታዋቂ ሰዎችን ፎቶ በማውረድ የውሸት አካውንት መክፈት ነው።

በመቀጠል የሚያጭበረብሩትን ሰው ማናገር ይጀምራሉ። ምናልባትም በቅርብ የሚያውቋቸውን ሰዎችንም ሊሆን ይችላል።

እነዛን ሰዎች ልክ እንደ ኖርማል ሆነው ያለ ማቋረጥ ጊዜ ወስደው ያናግሯቸዋል።

የትኛውንም ጊዜ ይፍጅ ማናገራቸውን ይቀጥላሉ።

ስለ ውሸት ስራቸው፣ ስለ ህይወታቸው እየፈጠሩ ያወራሉ። በዚህ ውስጥ ምንም ምልክት አያሳዩም።

ወደ ፍቅር ከወሰዷቸውና ከጣሏቸው እምነትም ካገኙ በኃላ መጨረሻው ወደሆነው ዓላማቸው ገንዘብ ማስላክ ይገባሉ።

" ለምን እኔ ምሰራው ስራ ላይ ኢንቨስት አታደርም / አታደርጊም " በማለት ለምሳሌ ክሪፕቶ  ላይ ብለው ገንዘብ ይቀበላሉ።

በቃ አለቀ ! ገንዘባችሁ ተበልቶ ይቀራል። በኃላም ብሎክ አድርገው ይሸኟችኋል። ቀጣይ ሌላ ሰው ታርጌት ያደርጋሉ።

ወጣቶቹ ይሄን ካላደረጉ ምናልባትም ኢ-ሰብአዊ ቅጣት ሊፈጸምባቸው ይችላል።

⚫️ በጎ አድራጎት ⚫️

የውሸት ማንነት ፎቶ ተጠቅመው አካውንት ከፍተው (ሴትን በወንድ ወንድ ደግሞ በሴት ማንነት) አንድ ታርጌት ያደረጉትን ሰው ረጅም ጊዜ ያናግሩ እና ለእርዳታ / ለእርዳታ ድርጅታቸው ገንዘብ ድጋፍ እንዲያደርጉ ያሳምኗቸኣል።

እነዛ ሰዎች ላይ እምነት የጣሉባቸው ተጨበርባሪዎች በሀዘን ተሰብረው ገንዘባቸውን ይልካሉ። ቀልጦ ይቀራል። ብሎክ ይደረጋሉ።

🟡 ባለሃብት መምሰል 🟡

የውሸት ማንነት በመፍጠር ፣ ፎቶዎችን በመጠቀም በኦንላይን ሰው ያናግራሉ።

እንዲታመኑ ረጅም ጊዜ ሊወስዱም ይችላሉ።

ሰዎቹ ካመኗቸው በኃላ ገንዘባቸውን በጋራ አፍስሰው ስለሚሰሯቸው ስራዎች በማናገር ገንዘብ ያስልካሉ። ከዛማ ቀልጦ ይቀራል። ብሎክ ያደረጋሉ !

🟤 ደንበኞችን ማነጋገር 🟤

ይህም በተመሳሳይ በሀሰተኛ ማንነትና ስራ ከተለያዩ ሰዎች እያነጋገሩ በማጭበርበር ገንዘብ መቀበል ነው።

ለምሳሌ ፦ እቃ የሚሸጡ አስመስለው ብር ካስላኩ በኋላ የውሃ ሽታ ሆነው ይቀራሉ።

🔵 ' ኮሜንት/ሬት በማድረግ ገንዘብ አግኙ ' 🔵

እነዚ አጭበርባሪዎቹ የውሸት ማንነት ተጠቅመው በቴሌግራም ፣ ዋትስአፕ ወይም በሌላ መንገድ ተጠቅመው የሚያጭበረብሩትን ሰው ማናገር ይጀምራሉ።

" ጎግል ላይ ግቡና ስለዚህ ድርጅት ጥሩ አስተያየት ጻፉ ይከፈላችኋል " ይላቸዋል።

ከዛም የመጀመሪያውን ክፍያ በመፈጸም እምነት ያሳድራሉ።

" ይሄን ያህል ብር ከላካችሁ ይሄን ያህል ታገኛላቹ " በማለት የሰዎቹን ማንነት ይገመግማሉ። እስከዛ ድረስ ግን ገንዘብ መላካቸውን አያቆሙም።

የሚጭበረበረው ሰው ብዙ ብር ካስላኩት በኋላ የውሃ ሽታ ይሆናሉ።


በተጨማሪም ...

እንደ ፖሊስ፣ደህንነት፣ ባንክ ሰራተኛ ፣ እንደ ድርጅት ኃላፊ ሆነው የሚያስመስሉ አጭበርባሪዎችም አሉ።

ስራውን የሚሰሩት ሰዎችም ተጠቂዎች ናቸው።

ስራውን ካልሰሩ አሰቃቂ ጥቃት ሊደርስባቸው ይችላል።

እንደ ባሪያ ለረጅም ሰአትም ያሰሯቸዋል።

እንደ ቅርብ ጊዜ ሪፖርት ፥ በማይናማር፣ ካምቦዲያ፣ ላኦስ፣ ቻይና በመሳሰሉ ሀገራት ከ300 ሺህ በላይ ሰዎች በኦንላይ ማጭበርበር ላይ ተሰማርተዋል።

ስራዎቹንም የሚያሰሯቸው ሰዎች እጃቸው በጣም ረጅም ነው።

#TikvahEthiopia
#CyberScam

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#NationalExam

የተፈጥሮ ሳይንስ የ2016 የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ዛሬ መሰጠት ተጀመረ።

ፈተናው ለሶስት ተከታታይ ቀናት ነው በወረቀት እና በኦንላይን የሚሰጠው።

@tikvahuniversity
⚠️እባካችሁ ተጠንቅቃችሁ አሽከርክሩ ⚠️

ትላንት ለሊት 6:30 አካባቢ በድሬዳዋ አስተዳደር ጀሎ በሊና ቀበሌ ቢርካ አካባቢ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ11 ሰዎች ሕይወት አልፏል።

ከሟቾች በተጨማሪም በ10 ሰዎች ላይ የአካል ጉዳት ደርሷል።

አደጋው የደረሰው ከድሬዳዋ ወደ ሐረር ሰዎችን አሳፍሮ ሲጓዝ የነበረ በተለምዶ “ ዶልፊን ” የሚባለው ሕዝብ ማመላለሻ በተቃራኒ መስመር በኩል ይጓዝ ከነበረ በተለምዶ “ ሲኖትራክ ” ተብሎ ከሚጠራው የደረቅ ጭነት ተሸከርካሪ ጋር በመጋጨታቸው ነው።

(ድሬዳዋ ፖሊስ)

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
TIKVAH-ETHIOPIA
#ExitExam የግል የመውጫ ፈተና ተፈታኞች ውጤት መቼ ይፋ ይሆናል ? የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የ2016 ተመራቂዎች የመውጫ ፈተና ውጤት ሰኔ 21/2016 ዓ.ም ይፋ መደረጉ ይታወቃል። በተመሳሳይ ጊዜ በአንድ ላይ የመውጫ ፈተናውን የወሰዱ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ውጤት ግን እስካሁን ይፋ አልተደረገም። ይህን ተከትሎ የግል ተፈታኞች በርካታ ጥያቄዎችን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አድርሰዋል።…
🔈#የተማሪዎችድምጽ

ባለፈው ወር የተሰጠውን ሀገር አቀፍ የመውጫ ፈተና የወሰዱ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ከፈተናው ጋር ተያይዞ ያላቸውን ቅሬታ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አቅርበዋል።

ተማሪዎቹ ፦

- የመንግሥት እና የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እኩል ፈተናውን ወስደው፣ ውጤት ለምን በተለያየ ጊዜ ተገለፀ ?

- የመንግሥት ተፈታኞች በብዛት ሲያልፉ በርካታ የግል ተቋማት ተፈታኞች ለምን ወደቁ?

- እያንዳንዳቸው አንድ አንድ ነጥብ ያላቸው መቶ ጥያቄዎች ተፈትን 37.92 አይነት ውጤት እንዴት ተመዘገበ ? የAI ስህተት ካለ ይነገረን።

- በጣም ተዘጋጅተን የተፈተንን ሰዎች በዚህ ትኩረት ሳይሰጠው በተፈተነው ፈተና ምክንያት ሞራላችን እንዲነካ እና ተስፋም እንድንቆርጥ ተደርገናል።

- ፈተናው ላይ ትልቅ ውጤትን ያመጣሉ የተባሉ ብዙ ጎበዝ ልጆች እንደተጠበቀው አልሆነም።

- ውጤታችን እንደገና ሊታይልንና የተፈተነው ጥያቄ ከነመልሱ ይፋ ሊደረግልን ይገባል።

... የሚሉ ቅሬታዎች በተፈታኞቹ ተነስቷል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በኢፌዴሪ የትምህርት ሚኒስቴር የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አገልግሎት ዴስክ ኃላፊ የሆኑትን እዮብ አየነው (ዶ/ር) ጠይቋል።

ከውጤት ነጥብ ጋር በተያያዘ ለተነሳው ጥያቄ ኃላፊው ተከታዩን ብለዋል ፦

1ኛ. የጤና ትምህርት ዘርፍ ሁለት ፈተና (ጠዋት ከ100 ከሰዓት ከ100 በድምሩ ከ200) ስለሚፈተኑና ለማለፊያ የሁለቱ ፈተናዎች ውጤት ተደምሮ አማካኝ ውጤት ስለሚያዝ ውጤታቸው በነጥብ ሊቀመጥ ይችላል፡፡

2ኛ. አንዳንድ የትምህርት ፕሮግራሞች ላይ ለምሳሌ ፦ ሒሳብ እና ማርኬቲንግ ማኔጅመንት በተለያዩ ምክንያቶች ተማሪዎች የተፈተኑት ጥያቄ ቁጥር ከመቶ ያነሰ ስለነበር ያገኙት ውጤት ወደ መቶ ሲቀየር በነጥብ ሊቀመጥ ይችላል፡፡

" ውጤት ሲገለፅ የጊዜ መቀዳደም ካልሆነ በስተቀር በሲሰተሙ ላይ ምንም አይነት ችግር እንዳልነበረ " ኃላፊው ገልጸዋል።

የማለፍ ምጣኔን በተመለከተም ፥ " ተፈታኞቹ የተማሩባቸውን ተቋማት እንዲሁም የራሳቸውን ብቃት መመልከት " አለባቸው ብለዋል።

ያስፈተኗቸውን ተማሪዎች 100% ያሳለፉ የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት እንዳሉ ኃላፊው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።


ይህንን ምላሽ የተመለከቱ ተማሪዎች ፥ " ለቅሬታችን የተሰጠው ምላሽ ተገቢ አይደለም ፤ አሁንም ቢሆን ውጤታችን እና የሰራነው በድጋሚ ይታይ " ብለዋል።

በሌላ በኩል ፤ የፋርማሲ ዲፓርትመንት ተማሪዎች ከፍተኛ ቅሬታ እንዳላቸው ተናግረዋል።

ተማሪዎቹ ፥ " ከዚህ በፊት እንደነበረው የጠዋት እና የከሰአት አማካይ (Average) የሚያዝ እንደሆነ በምላሹ ላይ ሰምተናል " ብለዋል።

" ግን ፈተናውን ከጨረስን ከአንድ ቀን በኋላ ፈተናው ችግር አለበት / ተሰርቋል ተብለን በአንድ ቀን ልዩነት እንደገና ፈተና ተቀምጠናል፤ ስንቀመጥም የጠዋቱን ብቻ ነበር አንዴ የተፈተንነው እንጂ የከሰአቱን ሌላ ጊዜ ነው የተባልነው " ሲሉ አስረድተዋል።

" ይህ ሆኖ ሳለ ታዲያ በጠዋቱ ፈተና ብቻ ነው pass and fail የሆነው። ስለዚህ ትምህርት ሚኒስቴር ቃሉን አክብሮ የከሰአቱን ፈተና ከተፈተንን በኋላ ነው አማካይ መያዝ ያለበት " ብለዋል።

ተማሪዎቹ አለን ያሉትን ቅሬታ ይዘን የሚመለከተውን አካል የምናነጋግር ይሆናል።

Via @tikvahuniversity
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#OFC #Ethiopia

" በአንድ ፓርቲ ፍላጎትና ሙሉ ቁጥጥር በሚመራ መንገድ የ120 ሚሊዮን ህዝብ ቁመት የሚሆን ዴሞክራሲያዊ ስርዓት በፍጹም አይፈጠርም !! " - ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና

የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና (ለቪኦኤ ሬድዮ ከሰጡት ቃል) ፦

" ዋና የኢትዮጵያ ችግር ፈጣሪ መንግሥት ነው። ይሄ ምንም ጥያቄ የለውም።

ከፖለቲካ ኃይሎች ጋር ሆነን ፣ከዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡም ጋር ሆነን ሀገር ውስጥም ከሀገር ውጭም ያላደረግነው ነገር የለም።

ዋናው ጉዳይ ስልጣን የያዘው ቡድን ሀቀኛ ፍትሃዊ የሚባለውን ነገር በጭራሽ አይፈልገውም።

' ስልጣን እኛ እጅ ነው ' ተንበርከኩና እኛ ጋር ግቡ ወይም የስልጣን ፍርፋሪ ኑና ውሰዱ ካልሆነ በስተቀር የኢትዮጵያ ህዝብ ከመገዳደል ፖለቲካ ወደ መደራደር ፖለቲካ እንዲገባ አይፈልግም።

ችግሩ ይሄ ነው በአንድ እጅ ማጨብጨብ አይቻልም።

እኛ የምንችለውን ያክል ይሄ ሀገር መሸጋገር የሚችለው ፣ የተሳካ ዴሞክራሲያዊ ሽግግር መምጣት የሚችለው ፣ የተሳካ ሰላም እና መረጋጋት መምጣት የሚችለው ሁሉም የኢትዮጵያ ኃይሎች የተሳተፉበት ፦
- ብሔራዊ እርቅ
- ብሔራዊ ድርድር
- ብሔራዊ ምክክር ሲደረግ ነው እያልን ስንጠይቅ ነበር።

ፖለቲካ እስከሚገባን ድረስ አሁን እየተገፋ ባለበት መንገድ 3 ነገሮች በኢትዮጵያ ምድር መሆን አይችሉም።

1ኛ. ሀቀኛ ሰላምና መረጋጋት አይመጣም ፥ ሰላምና መረጋጋት አሁን እየገፉ ባሉበት መንገድ መምጣት አይችልም። እኛም ኖርን አልኖርን !

2ኛ. በኢትዮጵያ ምድር ዴሞክራሲያዊ አስተዳደር ፣ ዴሞክራሲያዊ ሽግግር ፣ ሀቀኛ ፌዴራላዊና ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ፣ በነጻና ፍትሃዊ ምርጫ ስልጣን ላይ የሚወጣ መንግሥት ፣ የህዝቡን ይሁንታ ካጣ ከስልጣን የሚወርድ መንግሥት መፍጠር አይቻልም።

3ኛ. በአንድ ፓርቲ ፍላጎት ፣ ሙሉ ቁጥጥር በሚመራ መንገድ የ120 ሚሊዮን ህዝብ ቁመት የሚሆን ዴሞክራሲያዊ ስርዓት በፍጹም አይፈጠርም።

አንድ ቀን እነሱም ሰምተው ፤ ችግሩም ደግሞ አስተምሯቸው መስመር ሊይዝ ይችላል።

እኛ እንሞክር ነበር አሁንም ያንኑ ህጋዊ እና ሰላማዊ ትግላችንን እንቀጥላለን።

በሀገሪቱ ግጭት ያባባሰው ስር የሰደደው የፖለቲካ ችግር የሚፈታው በፖለቲካዊ ንግግር ብቻ ነው። "


#OromoFederalistCongress

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#OFC #Ethiopia " በአንድ ፓርቲ ፍላጎትና ሙሉ ቁጥጥር በሚመራ መንገድ የ120 ሚሊዮን ህዝብ ቁመት የሚሆን ዴሞክራሲያዊ ስርዓት በፍጹም አይፈጠርም !! " - ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና (ለቪኦኤ ሬድዮ ከሰጡት ቃል) ፦ " ዋና የኢትዮጵያ ችግር ፈጣሪ መንግሥት ነው። ይሄ ምንም ጥያቄ የለውም። ከፖለቲካ ኃይሎች ጋር ሆነን ፣ከዲፕሎማቲክ…
#OromiaRegion

" ችግሮች እንዲፈቱ ከማድረግ ይልቅ ችግሮቹ እንዲወሳሰቡ እያደረጉ ያሉት እኮ እነሱ ናቸው ( ኦፌኮን ጨምሮ አንዳንድ ፓርቲዎች) " - የኦሮሚያ ክልል መንግሥት

የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት የኮሚኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ኃይሉ አዱኛ (ለቪኦኤ ሬድዮ ከሰጡት ቃል) ፦

" የኢፌዴሪ መንግሥት ግጭቶችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ፣ ያሉትን አለመግባባቶች በሀሳብ ትግል እልባት ለመስጠት ብዙ ጥረቶችን እያደረገ ይገኛል።

ከነዚህ ውስጥ ከሀገሪቱ ታሪክ ፣ ከሀገረ መንግስቱ ግንባታ ጋር ተያይዞ ያደሩ ቅሬታዎች ስላሉ እነዚህ ቅሬታዎች እንዲፈቱ የምክክር ኮሚሽን አቋቁሞ እየሰራ ነው።

በዚህም የኢትዮጵያ መንግሥት ከጠብመንጃ ይልቅ በሀሳብ ትግል እንዲደረግ የሚያደርገውን ጥረት አጠናክሮ ነው የቀጠለው።

ግጭቶች በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱ ከማድረግ አኳያ እኛ የምንታማበት ነገር የለም።

አንዳንድ የፖለቲካ ፓርቲዎች
#ኦፌኮን ጨምሮ የድርሻቸውን ባለመወጣት ፤ ችግሮች እንዲፈቱ ከማድረግ ይልቅ ችግሮቹ እንዲወሳሰቡ እያደረጉ ያሉት እነሱ ናቸው።

አንዱ የኮሚሽኑ ስራ እንዳይሳካ እራሳቸውን በማግለል እየተንቀሳቀሱ መገኘታቸው ነው።

በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የተከሰተውን ግጭት በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት አንደኛ በሀገር በቀል በገዳ ስርዓት አባገዳዎችን ፣ የሃይማኖት አባቶችን ፣ ሃደሲንቄዎችን በማሳተፍ እርቅ እንዲወርድ ብዙ ጥረት አድርገናል። ጥረታችን አልተሳካም።

ሁለተኛ የሶስተኛ ወገኖችን ባሳተፈ መልኩ ችግሩ ይፈታ በሚል ሀሳብ ስለቀረበ ተቀብለን በሁለት ዙር ከዚህ ከአሸባሪው ቡድን (የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊትን ማለታቸው ነው) ውይይቶችን አድርገናል። ሁኔታው በሰላማዊ መንገድ ሊፈታ አልቻለም።

ነገር ግን በአንድ እና ሁለቴ ብቻ ተስፋ የሚያስቆርጥ ሳይሆን ለሰላም ጠንክረን እንሰራለን። "

#OromiaRegionalGovernment
#VOA

@tikvahEthiopia
#Rwanda

በሩዋንዳ በተካሄደ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ፖል ካጋሜ ከፍተኛ በሆነ ድምጽ የማሸነፍ እድል እንዳላቸው ያልተጠናቀቀ ቆጠራ አሳይቷል።

የሀገሪቱ ምርጫ ኮሚሽን በበርካታ የድምጽ መስጫ ጣቢያዎች ላይ ባካሄደው ቆጠራ (79% ቆጠራ) ካጋሜ 99.15 በመቶ ድምጽ ማግኘታቸውን ይፋ አድርጓል።

24 ዓመታትን ሩዋንዳን በፕሬዜዳንትነት የመሩት ፖል ካጋሜ ውጤቱ ለተጨማሪ 5 ዓመታት በስልጣን እንዲቆዩ ያደርጋቸዋል።

ሶስት ብርቱ ናቸው የተባሉ ተቀናቃኞቻቸው ከምርጫ ፉክክሩ ውጭ በሆኑበት ነው ምርጫው የተካሄደው።

በምርጫው የተሳተፉት የአየር ንብረት ጥበቃ ተሟጋች ፍራንክ ሃቢኔዝ እና ጋዜጠኛና ደራሲ ፊሊፕ ምፓይማና ከ1 በመቶ ያነሰ መራጭ ነው ያገኙት።

ከዚህ በፊት በነበረው የአውሮፓውያኑ 2017 ምርጫ ካጋሜ በ98.8 ድምጽ ማሸነፋቸው ይታወሳል።

ፖል ካጋሜ እኤአ 1994 የሩዋንዳ የዘር ፍጅት በኋላ በመሪነት ስፍራ የተቀመጡ ሲሆን ከ2000 በኋላም በፕሬዚዳንትነት ቀጥለዋል።

#BBC #AlJazeera

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
⚠️እባካችሁ ተጠንቅቃችሁ አሽከርክሩ ⚠️ ትላንት ለሊት 6:30 አካባቢ በድሬዳዋ አስተዳደር ጀሎ በሊና ቀበሌ ቢርካ አካባቢ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ11 ሰዎች ሕይወት አልፏል። ከሟቾች በተጨማሪም በ10 ሰዎች ላይ የአካል ጉዳት ደርሷል። አደጋው የደረሰው ከድሬዳዋ ወደ ሐረር ሰዎችን አሳፍሮ ሲጓዝ የነበረ በተለምዶ “ ዶልፊን ” የሚባለው ሕዝብ ማመላለሻ በተቃራኒ መስመር በኩል ይጓዝ ከነበረ በተለምዶ…
⚠️እባካችሁ ተጠንቅቃችሁ አሽከርክሩ ⚠️

በሶማሌ ክልል፣ ቀብሪበያህ ወረዳ ጉዮው በተባለ ቦታ ዛሬ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ6 ሰዎች ሕይወት አለፈ፡፡

በተጨማሪም በ14 ሰዎች ላይ የአካል ጉዳት መድረሱ ተገልጿል፡፡

አደጋው የተከሰተው በሁለት መኪኖች ግጭት መሆኑን ኤፍቢሲ ዘግቧል።

ትላንትና ለሊት 6:30 አካባቢ ላይ በድሬዳዋ  ከተማ ጀሎ በሊና ቀበሌ ቢርካ አካባቢ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ11 ሰዎች ሕይወት ማለፉ ዛሬ ጥዋት መዘገቡ አይዘነጋም።

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#Ethiotelecom #telebirr

ሁለቱን የከተማ መስተዳድሮች ጨምሮ የአብዛኛዎቹ የክልል ገቢዎች ግብር በቴሌብር መክፈል ተችሏል፤ እንኳን ደስ አላችሁ!!

ግብር ለመክፈል መጉላላት ሳይጠበቅብዎ በሥራ ገበታዎ ላይ እንዳሉ በቴሌብር ሱፐርአፕ http://onelink.to/fpgu4m ወይም *127# ባሉበት ቦታ ሆነው በምቾት ይክፈሉ!

ሥራን በክብር
ግብርዎን በቴሌብር !

ቴሌብር - እጅግ ቀላል፣ ፈጣን፣ ምቹ እና አስተማማኝ !

ለማንኛውም ጥያቄ ወይም አስተያየት በ https://www.tg-me.com/EthiotelecomChatBot 24/7 ያግኙን!

#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
2024/09/30 14:33:56
Back to Top
HTML Embed Code: